Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all 2784 articles
Browse latest View live

የፖለቲካ እስረኞች ፍትሕ ሳያገኙ በቀጥሮ እየተንገላቱ ነው

$
0
0

11705269_742488912543436_1050118275188445148_nነኅሴ ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ግድያ ለመቃወም መንግስት በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ሰበብ የታሰሩት እነ ማቲያስ መኩሪያ፣ ፖሊስ በጊዜ ቀጠሮ ወቅት ‹‹የቪዲዮ ማስረጃም አለን›› በማለቱና ተከሳሾቹ ‹‹ቪዲዮው ይቅረብልን፣ የቪዲዮ ማስረጃው ለእኛም የመከላከያ ምስክርነት ይጠቅመናል›› ብለው በመጠየቃቸው፣ ፍርድ ቤቱ የቪዲዮ ማስረጃው መቅረብ እንዳለበትና እንደሌለበት ብይን ለመስጠጥ ለዛሬ ነሃሴ 5 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጠሮ ቢሰጥም ፣ የመናገሻ ፍርድ ቤት በዛሬው ዕለት የማይሰራ በመሆኑ ችሎቱ በአራዳ ፍርድ ቤት በተረኛ ዳኛ ታይቷል፡፡ የልደታ ፍርድ ቤትም ‹‹ጉዳዩ አልተመረመረም፡፡›› በሚል ብይን ለመስጠት ለነሃሴ 18 ቀን 2007 ዓ. ቀጠሮ ሰጥቷል።
ፍርድ ቤቱ ቪዲዮው ላይ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ሲሰጥ የዛሬው ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን ፣ ተከሳሾቹም እየተጉላሉ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ አቤት ብለዋል።
2ኛ ተከሳሽ መሳይ ደጉሰው ‹‹ድሃ ቤተሰብ አለን፡፡ ቤተሰቦቻችን መርዳት እንዳንችል እየተጉላላን ነው›› በማለት ችግራቸውን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል። በዚሁ የክስ መዝገብ ማቲያስ መኩሪያ ፣ መሳይ ደጉሰው፣ ብሌን መስፍንና ተዋቸው ዳምጤ ሲገኙ ከመሳይ ደጉሰው ውጭ ያሉት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ናቸው፡፡
በተመሳሳይ በአራዳ ፍርድ ቤት የአቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው አቶ ማሙሸት አማረም ለነሃሴ 20 ቀን 2007 ዓ.ም. ተቀጥሯል፡፡ አቶ ማሙሸት የአቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለትም ‹‹ምስክሮቹ ስላልተሟሉና ብዙ መዝገቦችም ስላሉ ምስክርነት መስማት አልቻልንም›› ተብሎአል።
የአንድነት አባልና የሚሊዮኖች ድምፅ ጋዜጣ አምደኛ የነበረው እስማኤል ዳውድ አራዳ ፍርድ ቤት ቀርቦ ለነሃሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጥቶበታል።
ፍርድ ቤቱ ‹‹በክረምት ከማይሰሩ የተለያዩ ፍርድ ቤቶች መዝገቦች በመምጣታቸው ምስክርነት መስማት አልቻልንም፡፡ ስራ በዝቶብናል›› በሚል በበርካታ ተከሳሾች ላይ ረዘም ያለ ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን ፣ በሰልፉ ሰበብ የታሰሩ ተከሳሾች ፣ በተለይም ሴቶች እና ቤተሰቦቻቸው የተፋጠነ ፍርድ ልናገኝ አልቻልንም፣ በሚል ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ ሲያለቅሱ ተስተውለዋል ሲል ነገረ – ኢትዮጵያ ዘግቧል።

Source:: Ethsat


ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት የመቶ ብር ኖቶችን እንደጉድ እያተማቸው ነው * መቶ ብር በዛ ኢኮኖሚ ጠነዛ

$
0
0

ethiopia-100birr
አገሪቱ ውስጥ የመቶ ብር ኖቶች መጠን

በ1999 ዓ.ም 7.7 ቢሊዮን ብር
በ2000 ዓ.ም 10 ቢሊዮን ብር
በ2001 ዓ.ም 14 ቢሊዮን ብር
በ2002 ዓ.ም 17 ቢሊዮን ብር
በ2003 ዓ.ም 23 ቢሊዮን ብር
በ2004 ዓ.ም 30 ቢሊዮን ብር
በ2005 ዓ.ም 40 ቢሊዮን ብር
በ2006 ዓ.ም 40 ቢሊዮን ብር
በ2007 ዓ.ም 53 ቢሊዮን ብር

ከሰባት ዓመት በፊት በ99 ዓ.ም፣ በአገሪቱ የነበረው ጠቅላላ የመገበያያ ገንዘብ፣ 12 ቢሊዮን ብር ነበር። ከዚያስ? ከዚያ በኋላ ያለውማ፣ “የተዋጣለት የ‘Inflation’ ታሪክ ነው” ልንለው እንችላለን – ገንዘብ እንዴት እንደሚረክስ የሚያሳይ ታሪክ። በአዲሱ ሚሊኒዬም መግቢያ ላይ፣ 15 ቢሊዮን ብር ከደረሰ በኋላ፣ በዚያው ዓመት መጨረሻ ላይ ወደ ሃያ ቢሊዮን፣ እንደገና በቀጣዩ ዓመት አጋማሽ፣ ወደ 24 ቢሊዮን ብር ተሸጋግሯል።
በቃ፤ ሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው የገንዘብ መጠን በእጥፍ ጨምሯል። ያው፣ ገንዘብ ሲረክስ፣ የሸቀጦች ዋጋ ይጨምራል። ሚስጥር አይደለም። ማለትም… በ2000 ዓም. እና በ2001 ዓ.ም፣ በዋጋ ንረት፣ ኢትዮጵያ የአለም አንደኛ የሆነችው አለምክንያት አይደለም።
ያኔ ነው፣ መንግስት የብር ኖት ህትመቱን ረገብ ያደረገው፣ ከ2001 ዓ.ም አጋማሽ በኋላ፣ ለአንድ ዓመት ያህል፣ ብዙም አልጨመረም። ለዚህም ነው፣ የዋጋ ንረቱ (ወደኋላ ባይመለስም)፣ ቀስ በቀስ መረጋጋት የጀመረው። ግን አልዘለቀበትም። ለምን? መንግስት እንደገና፣ የብር ሕትመቱን ተያያዘዋ።
በአገሪቱ የሚንቀሳቀሰው የብር ኖቶች መጠን፣ ከ26 ቢሊዮን ብር ወደ 39 ቢሊዮን ብር የጨመረው፣ በ18 ወራት ውስጥ ነው – እስከ 2003 ዓ.ም መጨረሻ ላይ። ይሄኛው አመትም እንዲሁ፣ “በመላው አለም ከቀዳሚዎቹ ተርታ የሚጠቀስ የዋጋ ንረት”፣ በኢትዮጵያ የተከሰተበት ወቅት እንደሆነ አስታውሱ። የብር ኖቶች መጠን፣ እንዲያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በሃምሳ በመቶ ሲጨምር፣ ገንዘብ መርከሱና የሸቀጦች ዋጋ ሽቅብ መምጠቁ የግድ ነው።
በተቃራኒው፣ የብር ህትመት ረገብ ሲል ደግሞ፣ የዋጋ ንረቱ ይረጋጋል። ከ2003 ዓ.ም የመጨረሻ ወራት በኋላ፣ ያሉትን 18 ወራት መመልከት ይቻላል። ታተመ፣ ታተመና፤ የአገሪቱ የብር ኖቶች ወደ 46 ቢሊዮን ገደማ ደረሰ – እስከ 2005 መግቢያ ማለት ነው። በዚህ ጊዜ ውስጥ የብር ኖቶች መጠን የጨመረው፣ በ17% ገደማ ነው። ቀላል አይደለም። ግን፣ እንደ በፊቱ በሃምሳ ፐርሰንት ባለመጨመሩ፣ “ትንሽ ተሽሎታል” ልንል እንችላለን። በዚህም ምክንያት፣ በ2003 ዓ.ም ከሰላሳ በመቶ በላይ እያሻቀበ የነበረው የሸቀጦች ዋጋ፣ ቀስ በቀስ እየተረጋጋ ወደ አስር በመቶ እየበረደ መጥቷል።
ከዚያስ?
ከ2005 ዓ.ም መግቢያ አንስቶ፣ እስከ 2006 አጋማሽ ድረስ ባሉት 18 ወራት፣ ምን ተፈጠረ?
የዋጋ ንረቱም ይበልጥ ተረጋጋ። የሸቀጦች ዋጋ መጨመሩኮ አልቆመም። ግን፣ አመታዊው የዋጋ ጭማሪ፣ ወደ ስድስት ወደ ሰባት በመቶ በመውረድ፣ ቀዝቀዝ ብሏል። ለምን? የብር ህትመቱ ይበልጥ ረግቧላ። የገንዘቡ መጠን፣ 51 ቢሊዮን ብር ደርሷል። ግን፣ በ18 ወራት ውስጥ፣ በአራት ተኩል ቢሊዮን ብር (በአስር በመቶ ገደማ) ነው የጨመረው። ከቀድሞው ጋር ሲነፃፀም፣ “ደህና እየተሻለው መጥቷል” ልንል እንችላለን።
በዚሁ እርጋታው አለመቀጠሉ ነው ችግሩ። በ2006 መጨረሻ ላይ፣ የብር ህትመቱ እንደገና አገረሸበት።
ሰሞኑን ብሔራዊ ባንክ ባወጣው ሪፖርት ላይ፣ ባለፈው መጋቢት 2007 ዓም፣ በአገሪቱ ውስጥ ያለው የብር ኖቶች መጠን ምን ያህል እንደሆነ ተገልጿል። 64 ቢሊዮን ብር ደርሷል፣ ይላል ሪፖርቱ።
እውነትም አገርሽቶበታል። ያው… በአንድ አመት ተኩል ጊዜ ውስጥ፣ የብር ኖቶች መጠን፣ እንዲህ በ25 በመቶ ሲጨምር፣… የሸቀጦች ዋጋ እንደ በፊቱ ተረጋግቶ ሊቀጥል አይችልም። ሰሞኑን በማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ የወጣው መረጃም፣ ይህንን ያረጋግጣል።
ካለፈው መስከረምና ጥቅምት ወር ወዲህ፣ የሸቀጦች የዋጋ ንረት ያለማቋረጥ እያሻቀበ መጥቷል። እንዳትሳሳቱ። “የሸቀጦች ዋጋ ያለማቋረጥ እየጨመረ ነው” ማለቴ አይደለም። ጭማሪውንማ ለምደነዋል። መንግስት፣ የብር ህትመት ላይ በደንብ ፍሬን ለመያዝ ፈቃደኛ እስካልሆነ ድረስ፣ የሸቀጦች ዋጋ እየጨመረ መሄዱን አያቆምም። አስቸጋሪው ነገር፣… የጭማሪው ፍጥነት እየባሰበት መምጣቱ ነው። በአመት ውስጥ የሚከሰተው የዋጋ ጭማሪ፣ ከአስር በመቶ በላይ እየሆነ መምጣቱ ነው ፈተናው።
መስከረም ላይ፣ አመታዊው የዋጋ ጭማሪ ከስድስት በመቶ ብቻ እንደነበረ የሚገልፀው የስታትስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ፤ ታህሳስ ላይ ሰባት መቶ፣… የካቲት ላይ ስምንት በመቶ፣… ሚያዚያ ላይ ዘጠኝ በመቶ፣… በሰኔ ወር ደግሞ ከአስር በመቶ በላይ ሆኗል። እንደ “ቀይ መስመር” ተደርጎ የሚታሰበውን ድንበር፣ ጥሶ አለፈ ማለት ነው – ወደ “ደብል ዲጂት” ተሻግሯል።
ሐሙስ እለት የተሰራጩ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ደግሞ፣ በሐምሌ ወር አመታዊው የዋጋ ንረት፣ ብሶበት 12% ደርሷል። የአለም ባንክ እንደሚለውማ፣ የዋጋ ንረቱ ከዚህም በላይ ወደ 15 በመቶ መጠጋቱ አይቀርም ነበር – በአለም ገበያ፣ የነዳጅ ዋጋ ከአምናው ባይቀንስ ኖሮ።
በእርግጥ፣ ባለፉት አመታት እንዳየነው፣ ቅጥ ባጣ የገንዘብ ህትመት ሳቢያ “የዋጋ ንረት” በተባባሰ ቁጥር፣ ጥፋቱ የሚሳበበው በነጋዴዎችና በቢዝነስ ሰዎች ላይ ነው።
ዘንድሮም፣ መንግስት፣ ጥፋቱን በነጋዴዎች ላይ ለማሳበብ መሞከሩ አይቀርም። ነገር ግን፣ ከንቱ ሙከራ ነው። ለነገሩ፣ አብዛኛው ኢትዮጵያዊም፣ ነጋዴዎችን ለማውገዝና ለመወንጀል እጅጉን ይፈጥናል። ጨርሶ፣ መረጃዎችን በወጉ ማየትና ማገናዘብ አያ….

ምንጭ ፡፡ አዲስ አድማስ

የሕወሓት መንግስት ቅንጅትን ለማፍረስ የተባበሩትን አቶ አየለ ጫሚሶን እንደሸንኮራ መጦ ጣላቸው

$
0
0

chamiso ayele
የሕወሓት መንግስት በሚዲያዎቹ በኩል እንደዘገበው ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ቅንጅት) የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የፓርቲውን ሊቀመንበር አቶ አየለ ጫሚሶንና የፓርቲውን የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ አስረስ በትረን ከአመራርና አባልነት ማስወገዱን ገልጿል:: እንደ መንግስት ሚዲያዎች ዘገባ በፓርቲው ስም የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውሳኔ በሚል ደብዳቤ የላኩ ግለሰቦች በህገወጥ ድርጊትና ወንጀል ከፓርቲው የተሰናበቱ መሆናቸውን የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አየለ ጫሚሶ አሳወቁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ችግራቸውን በፓርቲው መተዳደሪያ ደንበ መሠረት እንዲፈቱ አሳሰበ። ይህ የምርጫ ቦርድ ተግባር በአንድነት ፓርቲ ላይ የተለመደ አካሄድ ነው ሲሉ ፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ::

የሕወሓት መንግስት ያደራጃቸው የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በፓርቲው ዋና ፀሐፊ፣የፅሕፈት ቤቱ ኃላፊና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በአቶ ሳሳሁልህ ከበደ ሰሞኑን ለኢህ አዴግ ሚድያዎች በላከው የውሳኔ ማሳወቂያ ደብዳቤ ሁለቱ ከፍተኛ አመራሮች ከፓርቲና ከሥልጣናቸው እንዲወገዱ የተደረገው በፓርቲው ህገ ደንብ መሠረት ከሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መካከል አንደ ሦስተኛው ስብሰባ እንዲደረግ ሲጠይቁ አስቸኳይ ስብሰባ መጥራት ስለሚቻል በዚሁ መሠረት ስብሰባው የተካሄደ መሆኑን ያስረዳል።

በፓርቲው ውስጥ ህገ ወጥ አሠራሮች የተስፋፉበት፣ውጫዊና ውስጣዊ ወንጀሎች እየተበራከቱ የመጡበት ሁኔታ መኖሩን ፣በህጋዊ ፓርቲ ሽፋን ከፓርቲው አቋም ውጪ መንቀሳቀስ የሚሉና ሌሎች ችግሮች ከታዩ በኋላ ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅና ፓርቲውን ለማዳን ሲባል እርምጃው መወሰዱን ያትታል። የስብሰባው ቃለ ጉባኤና ውሳኔም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መላኩንም ያስረዳል።

የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ አየለ ጫሚሶ የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውሳኔ አስመልክቶ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ «በፓርቲው ስም የውሳኔ ሃሳብ በሚል የሚያቀርቡት ግለሰቦች ህገወጥ ድርጊትና ወንጀል ፈፅመው በፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ከሰኔ 28 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ ከአመራርነትና ኃላፊነት የተባረሩ ናቸው» ቢሉም ክርክራቸው ጉንጭ አልፋ ነው የሚሉ በርካታ ናቸው::

አቶ አየለ ጫሚሶ ከሕወሓት መንግስት ጋር የነበራቸው ፍቅር ያለቀ ሲሆን እንደሸንኮራ ተመጠዋል:: እኚህ ፖለቲከኛ የቅንጅትን ትልቅ ትግል ገደል ለመክተት የተባበሩና ለጥቅም ያደሩ በመሆኑ ዛሬ እንደሸንኮራ ተመጠው ወያኔ ባዘጋጃቸው ሰዎች ቢጣሉም የሚቆረቆርላቸውም የለም የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ::

መንግስት በሕዝብ የተመረጠው ቴዲ አፍሮን በስነጥበብ ዘርፍ ለመሸለም ፍላጎት እንደሌለው በይፋ አሳየ

$
0
0

teddy afro
(ዘ-ሐበሻ) በየዓመቱ የሚካሄደና ዘንድሮም ለ3ኛ ጊዜ ነሐሴ 30 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል በሚከናወነው ‹የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት› በየዘርፉ የተመረጡ የመጨረሻዎቹ አምስት ዕጩዎችን መንግስት ልክ እንደምርጫው አጭበርብሮ ራሱ የሚፈልጋቸውን ሰዎች አስቀመጠ:: ካለፈው ታህሳስ ወር ጀምሮ በተሰጠው የሕዝብ ጥቆማ የዓመቱ በጎ ሰው በሚል በስነጥበብ ዘርፍ ዝነኛው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ምርጫን ቢያገኝም መንግስት በምርጫው እንደማጭበርበር እንደለመደው በፖለቲካዊ ውሳኔ ከ እጩዎች ዘንድ እንዳይካተት መደረጉ ተጋልጧል:: ከታኅሣሥ ወር ጀምሮ በተሰጠው የሕዝብ ጥቆማ መሠረት ታሪካቸውና ሥራቸው ተሰብስቦ፣ በበጎ ሰው ሽልማት የምርጫ ሂደት ኮሚቴ የተመረጡት 45 ዕጩዎች ናቸው ብሎ መንግስት ካስቀመጣቸው ሰዎች መካከል ሁሉም መንግስት ራሱ እንዲሸለሙልኝ እፈልጋለሁ ያላቸውን እንዳጨ የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል:: ቴዲ አፍሮ በስነጥበብ የዓመቱ በጎ ሰው ዘርፍ የበርካታ ሕዝብ ድምጽን ቢያገኝም ከ እጩዎች ዝርዝር እንዲወጣ ተደርጓል::

ዘንድሮ መንግስት 9 ሰዎችን በሕዝብ ምርጫ እሸልማለሁ ቢልም ቅሉ ምርጫው ለመንግስት ፖለቲካ ቅርበት ያላቸው ሰዎችን የሚያካትት እንጂ ትክከለኛው የሕዝብ ጥቆማ እንዳልሆነ ታማኝ ምንጮች ይናጋራሉ::

ሕወሓት የሚመራው መንግስት በሕዝብ የተጠቆሙ ሰዎችን ትቶ በራሱ መንገድ ሕዝብ መረጣቸው ብሎ ያስቀመጣቸው ሰዎች ዝርዝራቸው የሚከተለው ነው፡፡

በ2007ዓም በልዩ ልዩ ዘርፎች ዕጩ የሆኑ በጎ ሰዎች

በሳይንስ ምርምር ዘርፍ ዕጩዎች
1. ፕ/ር ኢ/ር አበበ ድንቁ (አአዩ)
2. ኬሚካል መሐንዲስ ጌታሁን ሄራሞ
3. ዶክተር አበበ በጅጋ
4. ፕሮፌሰር አሥራት ኃይሉ
5. ዶ/ር ይርጉ ገ/ሕይወት (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል)

በሥነ ጥበብ ዘርፍ ዕጩዎች
1. አቶ አለ ፈለገ ሰላም
2. እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ
3. አቶ ተስፋየ አበበ(የክብር ዶክተር)
4. ሰዓሊ ታደሰ መስፍን
5. አባተ መኩሪያ
በበጎ አድራጎት ዘርፍ ዕጩዎች
1. ወ/ሮ አበበች ጎበና
2. አቶ አስመሮም ተፈራ /ሲኒማ ራስ አካባቢ የተቸገሩትን የሚረዳ/
3. ስንታየሁ አበጀ (የወደቁትን አንሱ) እንጦጦ ማርያም አካባቢ)
4. አቶ አስፋው የምሩ /የአሠረ ሐዋርያት ት/ቤት መሥራች/ ዊንጌት አካባቢ
5. ትርሐስ መዝገበ

በቢዝነስና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ ዕጩዎች
1. አባ ሐዊ /አቶ ገብረ ሚካኤል (በትግራይ ክልል ለአብርሃ ወአጽብሐ አካባቢ ገበሬዎች ሥራ የፈጠሩ ገበሬ)
2. ሰላም ባልትና
3. አዋሽ ባንክ
4. ካፒቴን ሰሎሞን ግዛው
5. ካልዲስ ቡና
በቅርስና ባሕል ዘርፍ ዕጩዎች
1. አቶ ዓለማየሁ ፋንታ
2. አቶ ሀብተ ሥላሴ ታፈሰ
3. አቶ ዓለሙ አጋ
4. EMML /HMML(የኢትዮጵያ የብራና መጻሕፍት ማይክሮ ፊልም ድርጅት)
5. ማኅበረ ቅዱሳን

በማኅበራዊ ጥናት ዘርፍ ዕጩዎች
1. ፕ/ር ሪቻርድ ፓንክረስት
2. ደሳለኝ ራሕመቶ
3. ዶክተር ፈቃደ አዘዘ
4. ፕሮፌሰር ሺፈራው በቀለ
5. ፕሮፌሰር በላይ ካሣ

በጋዜጠኛነት ዘርፍ ዕጩዎች
1. አቶ መዓርጉ በዛብህ
2. አቶ ያዕቆብ ወልደ ማርያም
3. አቶ ነጋሽ ገብረ ማርያም
4. ታምራት ገብረ ጊዮርጊስ(ፎርቹን ጋዜጣ)
5. ቴዎድሮስ ጸጋየ

በስፖርት ዘርፍ ዕጩዎች
1. አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው
2. መምህር ስንታየሁ እሸቱ (ከበቆጅ ብዙ አትሌቶች እንዲወጡ ያደረገ መምህር)
3. መሠረት ደፋር
4. ኢንስትራክተር ሽፈራው እሸቱ
5. ዶክተር ወ/መስቀል ኮስትሬ

መንግሥታዊ ኃላፊነትን በብቃት በመወጣት ዘርፍ ዕጩዎች
1. አቶ ግርማ ዋቄ(የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩ)
2. አቶ መኮንን ማን ያዘዋል
3. አቶ ሽመልስ አዱኛ
4. ዐማኑኤል የአእምሮ ሕክምና ሆስፒታል
5. ኢንጅነር ስመኘው በቀለ

ኃይለማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚኒስተርነታቸው ይቀጥላሉ ተባለ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በኦህዴድ; በብ አዴን እና በሕወሓት ውስጥ በተፈጠረው የስልጣን ሽኩቻ እየታመሰ የሚገኘው የኢሕአዴግ መንግስት በመጪው መስከረም ወር በሚመሰረተው “አዲሱ” መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝን ቦታውን ይዘው እንዲቆዩ እንደሚያደርግ የድርጅቱ የቅርብ ሰዎች ለዘ-ሐበሻ አስታውቀዋል::
hailemariam
በአሁኑ ወቅት በሶሥቱ ትላልቅ ፓርቲዎች ውስጥ የተፈጠረው አለመተማመን ሃይለማርያም በቦታቸው እንዲቆዩ እንደኢያደርጋቸው የሚገልጹት ምንጮች በተለይም በብ አዴን እና በ ኦህዴድ ውስጥ ተገቢ የሚባል ጥያቄ የሚጠይቁ አባላትን በሙስና ለማሰር ሃሳብ እንዳለ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ተናግረዋል::

ህወሃት፣ ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን በያዝነው ወር ድርጅታዊ ጉባኤያቸውን በተናጠል በማካሄድ እያንዳንዳቸው ዘጠኝ አባላት ያሏቸውን የሥራ አስፈፃሚ አባላትን የሚመርጡ ሲሆን እነዚህ አባላትም በያዝነው ወር መጨረሻ ወይንም በመስከረም ወር መግቢያ በመቀሌ ከተማ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የኢህአዴግ ጉባዔ ላይ የግንባሩን ሊቀመናብርት ይመርጣሉ ተባሏል:: የኢሕ አዴግ ሊቀመንበርም ሃይለማርያም ደሳለኝ ሆነው እንደሚቆዩና ሆኖም ግን ሌሎች ድርጅቱን ብዙ ዓመት አገልግለዋል የተባሉ ባለስልጣናት እንደሚሸኙ ተገልጿል::

የጠቅላይ ሚኒስተርነቱን ቦታን ሕወሓቶች አሁንም የሚፈልጉት ሲሆን የራሳቸውን ሰው ለማስቀመጥ ከላይ ታች እየተሯሯጡ ይገኛሉ:: ሆኖም ግን እርስ በ እርሳቸው መግባባት ስላልቻሉ ኃይለማርያም እንዲቀጥሉ ምክንያት ይሆናል ሲሉ ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል::

ጥቂት ስለ አቶ መለስ…የክፋት ጭንቅላት መስራት ካቆመ 3 አመቱ = በክፋት የተጨመቁ መሃይማን ግዞት ቀጥሏል

$
0
0

(ምንሊክ ሳልሳዊ)

መለስ ዜናዊ ከጅምሩ በክፋት የሰለጠነ መሆኑ እሙን ነው:;ድርጊቶቹ ሁሉ ይመሰክራሉ::አስተዳደጉ እንኳን ብናየው ከቀሪው ኢትዮጵያዊ ላይ ከፍተኛ የሆነ የጥላቻ ተረት ተረት እየተነገረው ያደገ ሲሆን በእድገት ዘመኑ እናትና አባቱ ብሎም የቅርብ ዘመዶቹ ሲናገሩ የሚሰማው የጣሊያንን ደግነት እና የኢትዮጵያውያንን ሃጢያተኝነት በተለይ የንጉሰነገስቶችን እና የአማራን ጥላቻ ሲሰበክ ያደገ የሰላቶ አገልጋዮች የባንድ ልጅ መሆኑ ይታወቃል::እንደዚህ አይነት ግለሰብ ለኢትዮጵያ ደግ ያስባል ለኢትዮጵያውያን መልካምነትን ይመኛል ማለት ከዘበትም በላይ በድርጊት የታየ ነው::ታሪክን የኋሊዮሽ ካየን በባንዳ ቤተሰብ ውስጥ ያደጉ ሰዎች እስከዛሬ ስለሃገር እና ስለሕዝብ የማያስቡ የጀርባ ቅማሎች ሆነው እያየናቸው ነው::

11231209_1623159974621065_3459709504333964141_n

በባንዳ ቤተሰብ ውስጥ የነጮችን የበላይነት ሲሰበክ ያደገው መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያውያን ላይ ያለው ጥላቻ ካደገ በኋላ ወደ መሃል አገር በሚያየው የኢትዮጵያውያን ደግነት እና ጨዋነት እንዲሁም ፍቅር ከመማረክ ይልቅ በቅናት እና ባደገበት ጥላቻ ተመርኩዞ የበታችነት ስሜቱ ስላጠላበት ትምህርቱን ጥሎ መሰደዱም ሌላኛው ባዶነቱን ያሳያል::በረሃም ገብቶ ለኢትዮጵያውያን ያልተኛው መለስ ዜናዊ በአላማ የማይለዩትን የተማሪ ቤት አጋሮቹን የሆኑትን የኢሕአፓ አባላት በመፍጀት እና በማስፈጀት ለሞት ለእስር እና ለስደት ዳርጓቸዋል::በበረሃ ቆይታው ከፍተኛ ወንጀሎችን በመስራት ከተባባሪዎቹ ከነስብሃት ነጋ ጋር በመሆን ወደ ከፍተኛ እርከን የደረሰው ይህ ሰው እጁ ከበለሃ ጀምሮ በደም የተነከረ ለአገር ይጠቅማሉ የተባሉ በርካታ ታጋዮችን ያጠፋ ሲሆን አብዛኛዎቹ ታጋዮች ሊጠፉ የቻሉት ኢትዮጵያዊ ከሚል የሃሳብ መደርደሪያ በመነሳታችው መሆኑ አንዱ ምክንያት ሲሆን በአስተሳሰብ ልዩነት አሊያም በልጠው የተገኙትን በማስገደል እና እንዲሰደዱ በማድረግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል::

መለስ ዜናዊ ሱዳን ላይ ተቀምጦ አንድ ጥይት ሳይተኩስ በልጅነቱ ከጓደኛው ጋር ሲደባደብ የተፈነከተውን ጠባሳ ይዞ ጥይት መቶኝ ነበር በማለት ከፍተኛ በሃሰት የተሞላ ጀግንነት እና ጀብደኝነት ሲያወራ የነበር የሃሰት ሰው ነበር::ማንበብ የሚወደው የማኪያቬሊዝም ፍልስፍና ተከታይ የሆነው መለስ ዜናዊ ከበረሃ በኋላ በሃገር ድረጃ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ከፍተኛ ወንጀሎችን ብመላው ኢትዮጵያውያን ላይ ፈጽሟል::ትዘርዝሮ የማያልቅ የፖለቲካ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ወንጀሎችን የፈጸመው መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያውያን ካለቤተሰብ በትኗል አስገድሏል አሰድዷል አስሯል በአንድ አገር ውስጥ መሪ ነኝ ከሚል አንድ ባለስልጣን የማይጠበቅ ሁኔታ በዜጎች ላይ ከፍተኛ ታሪክ ይቅር የማይለው ከሱ በፊት የነበሩ መንግስታት ያልፈጸሙትን በገሃድ እና በሕቡእ ከባባድ ወንጀሎች ፈጽሟል::የመለስ ዜናዊ ወንጀሎች ተዘርዝረው አያልቁም::በአለም አቀፍ ደረጃ ቱጃር ከሚባሉት የአገር መሪዎች ግንባር ቀደም የነበረው መለስ ዜናዊ የሃገራችንን አንጡረ ሃብት ርሕራሄ በሌለው ሁኔታ ከነሚስቱ እና አሾክሻኪዎቹ ጋር በመሆን ዘርፏል::

የመለስ ዜናዊን ወንጀል ተንቶ ለመጻፍ እጅግ ብዙ ጊዜ ይወስዳል::በስልጣን ዘመኑ አንድ ቀን ሃገሬ ሳይል “ይህቺ ሃገር…” ምናምን እንዳለ ሕዝብን እየተሳደብ ሲያፈናቅል እና ሲያሸማቅቅ የሞተው ይህ ከይሲ የሱን ፈለግ የተከተሉ እና በክፋት የተጨመቁ ባለስልጣናት እና በነፈሰበት የሚነፍሱ አጋሮቻቸው በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ተቀምጠው እየገደሉ እያሰሩ እያሳደዱ እና እየዘረፉ በመኖር ላይ ይገኛሉ ::እነዚህ አምባገነን የማፊያ ቡድን መንግስታዊ አሸባሪዎችን ከኢትዮጵያ ምድር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት ሁላችንም በጋራ ሆነን ከትግሉ ጋር ተቀላቅለን እጅ ለእጅ በመያያዝ በሃገር ውስጥ እና በዳር አገር የተጀመረውን ትግል ዳር በማድረስ ለድል በመብቃት ነጻነታችንን እና መብታችንን ማስከበር ይጠበቅብናል::የመለስ ዜናዊን የሙት መንፈስ እና የአምባገነን የወያኔ ጉጅሌዎችን ማጥፋት የምንችለው እያንዳንዳችን ስለ ነጻነታችን በምንከፍለው መስእዋትነት እና የዜግነት ግዴታ መሆኑን አንዘንጋ::‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች በእያንዳንዳቸው የ15 ሺህ ብር ዋስ ተጠየቀባቸው

$
0
0

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ከምርጫው ማግስት ከአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች እያንዳንዳቸው 15 ሺህ ብር ዋስ ተጠየቀባቸው፡፡ አመራሮቹ ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ አራት ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ፖሊስ በሽብርተኝነት ወንጀል እንደጠረጠራቸው ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ ፖሊስ ‹‹ለግንቦት 7 አባላትን እየመለመሉ ይልካሉ፡፡ ኤርትራ ድረስ ሄደው ስልጠና ወስደዋል፡፡›› የሚል ክስ አቅርቦባቸው የነበር ቢሆንም ለክሱ ምንም አይነት ማስረጃ ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡ አመራሮቹ በበኩላቸው የታሰሩት በሰላማዊ ትግል ጠንካራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ በመሆናቸው፣ በተለይም በምርጫው ወቅት ፓርቲያቸውን በማስተዋወቅና ህዝብን በማደራጀት ጠንካራ ስራ በመስራታቸው ገዥው ፓርቲ የወሰደባቸው በቀል መሆኑን ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡ ከመታሰራቸው በፊት የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ከፖለቲካው እንዲርቁ ሲያስጠነቅቁዋቸው እንደቆዩም አስታውቀዋል፡፡
ፖሊስ ላቀረበው ክስ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ዛሬ ነሃሴ 6/2007 ዓ.ም ከምርጫው ማግስት እየታደኑ ከታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች መካከል 8ቱ እያንዳንዳቸው የ15 ሺህ ብር ዋስ አቅርበው እንዲፈቱ ወስኗል፡፡ ከምርጫው በኋላ ታስረው በዛሬው ዕለት እያንዳንዳቸው 15 ሺህ ብር ዋስ ከፍለው እንዲወጡ የተጠየቀባቸው፡-
1. ልዑልሰገድ እምባቆም
2. ፋንታሁን ብዙአየሁ
3. መንግስቴ ታዴ
4. አበረ ሙሉ
5. አዳነ አለሙ
6. ሞላ የኑስ
7. ስማቸው ምንይችል
8. አበባው አያሌው ናቸው፡፡
ዛሬ ፍርድ ቤቱ በ15 ሺህ ብር ከፍለው ይውጡ ካላቸው በተጨማሪ በአማራና በደቡብ ክልል በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ታስረው እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተለይም ከተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎች ታድነው ከተያዙ በኋላ ባህርዳር ከተማ ውስጥ ታስረው የሚገኙት የፓርቲው አመራሮችና አባላት ከፍተኛ ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

አለቃዎ ሳይሆን ቅን ህሊናዎ የሚያዝዎትን በመፈፀም መልካም ዜጋ ይሁኑ!- አርበኞች ግንቦት 7 

$
0
0

መልካም ዜጋ ማለት ምን ማለት ነው?

ginbot 7ይህን ጥያቄ ለመመለስ በርካታ መጻሕፍት መፃፍ ይቻላል፤ መሠረተ ሀሳቡን ግን በጥቂት ዓረፍተ ነገሮች ማቅረብ ይቻላል።

መልካም ዜጋ ኢፍትሃዊ ተግባር ሲፈፀም “እኔ ምናገባኝ?” አይልም። መልካም ዜጋ “ያባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ”፤ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶም አይብቀል”፤ “እያለህ ካልሆነ ከሌለህ የለህም” እና በርካታ መሰል ምሳሌዎችን አይሰማም። መልካም ዜጋ በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ ቢሆን ከነፃና ቅን ህሊናው ጋር ታርቆ ይኖራል።

የህወሓት አገዛዝ፣ መልካም ዜጋ ማለት የመንግሥት ሥልጣን የያዘን ማንኛውም አካል ማክበርና በታማኝነት ማገልገል ተደርጎ እንዲተረጎምለት ይሻል። ፍትህ የሚያዛባ መንግሥትን መቃወም የመልካም ዜጋ አቢይ ተግባር መሆኑ የዘመናችን ወጣት እንዳይገነዘብ ያደርጋል። በተለይ ባለሙያዎች የሚያገለግሉትን አገዛዝ ባህርይ እግምት ውስጥ ሳያስገቡ የተቀጠሩበትን ሥርዓት በታማኝነት ማገልገል የዜግነት ግዴታቸው አድርገው እንዲወስዱት ይወተውታል።

ኦስካር ግሮኒንግ ( Oskar Groening)የዘጠና አራት ዓመት ሽማግሌ ጀርመናዊ ነው። በጀርመን የሂትለር አገዛዝ ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ንፁሃን የተፈጁበት አሽዊትስ ካምፕ ውስጥ የሂሳብና ጽህፈት ሠራተኛ ነበር። ኦስካር ግሮኒንግ አንድም ሰው አልገደለም፤ አንድም ሰው አልገረፈም። እሱ ሂሳብ ነው የሠራው። ሆኖም በደል ሲፈፀም አይቶ “ምናገባኝ” ብሎ አልፏልና ከብዙ ዓመታት በኋላ ተከሶ በቅርቡ የ4 ዓመታት እስር ተፈርዶበት በሁለት እግሮቹ መቆም በማይችልበት በ 94 ዓመቱ በእርጅናውና በመጦሪያው ዘመን ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ፊት ተዋርዶ እስር ቤት ወርዷል።

በአንፃሩ ኦስካር ሽንድለር (Oskar Schindler) በጀርመን ናዚ ወቅት ሂትለር ይመራው የነበረው የናዚ ፓርቲ አባልና ሰላይ ነበር። ሆኖም ግን የሥርዓቱን ኢሰብዓዊነት ሲረዳ እዚያው የናዚ ፓርቲ ውስጥ ሆኖ አለቆቹ ያዘዙትን ሳይሆን ቅን ህሊናው ያዘዘውን በምስጢር መሥራት ጀመረ፤ በዚህም የ 1200 ሰዎችን ሕይወት ታደገ። ከጦርነቱ በኋላ ኦስካር ተከብሮ የኖረ በርካታ የክብር ስሞችና ሽልማቶች የተሰጠው በመልካም አርዓያነቱ የሚጠቀስ ሰው ሆነ።

በአገራችንም በአምስት ዓመታቱ የፋሽስት ወረራ ወቅት ስመ ጥር የውስጥ አርበኞች ነበሩ። ከነፃነት በኋላ ባንዶች እንኳን በውስጥ አርበኝነት ለመጠራት ያደርጉት የነበረውን እሽቅድድም ልብ በሉ።

በህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴግ፣ ደህዴግ እንዲሁም አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ ያላችሁ ወገኞች ኦስካር ግሮኒንግን ወይንስ ኦስካር ሽንድለርን መምሰል ትፈልጋላችሁ? በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት ውስጥ ያላችሁ ወገኖቻችን ነገ የምትዋረዱበትን ሥራ መሥራት ነው የሚበጃችሁ ወይስ ዛሬ ከህሊናችሁ ጋር ታርቃችሁ እየኖራችሁ ነገ ደግሞ ልጆቻችሁና የልጅ ልጆቻችሁ የሚኮሩበትን ተግባር መፈፀም ትፈልጋላችሁ? በአገዛዙ የስለላ ድርጅቶች ውስጥ ያላችሁ ወገኖች ስማችሁን በመልካም ማስጠራት አትሹምን?

ልቦና ያላችሁ ወገኖቻችን ሆይ! መልካም ዜግነት ሎሌነት አይደለም። መልካም ዜግነት ለቅን ህሊና ታማኝ መሆን ነው። መልካም ዜግነት ሲመች በገሀድ፤ ሳይመች በምስጢር ኢፍትሃዊነትን መዋጋት ነው።

አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በማናቸውም መንገድ በአገዛዙ የፓለቲካ፣ የጦርና የፓሊስ ተቋማት፤ በስለላም ይሁን በሌላ የሲቪል ሙያ የተሰማራችሁ ወገኖቻችን የታዘዛችሁትን ሳይሆን ቅን ህሊናችሁ የሚጠይቃችሁን በመሥራት ኢፍትሃዊ፣ ፋሽስታዊና ዘረኛ የሆነውን የህወሓት አገዛዝን እንድታዳክሙ ጥሪ ያቀርብላችኋል። በአገዛዙ ውስጥ ሆናችሁ እያለም የምትሠሩት ለሀገርና ለትውልድ የሚጠቅም በርካታ ሥራ አለ። የአገዛዙን ምስጢራዊ ሰነዶች ለአርበኞች ግንቦት 7 እንዲደርስ ማድረግ፤ አሊያም በማኅበራዊ ሚዲያዎች (ለምሳሌ ፌስ ቡክና ቱተር) ማሰራጨት ትልቅ ዋጋ ያለ ሥራ ነው። የህወሓት ፀረ-አገር እና ፀረ-ሕዝብ ፕሮጀክቶችን ማሰናከል ሌላ ትልቅ ሥራ ነው። በነፃነት ታጋዮች ላይ የሚደረጉ ዱለታዎችን ማክሸፍ ሕይወት አድን ሥራ ነው። ድርጅቶቹ ውስጥ ሆኖ ድርጅቶቹን ማዳከም የመልካም ዜግነት ግዴታ መወጣት ነው።

በሥርዓቱ ውስጥ ሆነው ኢፍትሃዊነትን ለማጋለጥ እና ሥርዓቱን ለማዳከም ለሚጥሩ ወገኞች አርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ ክብር አለው፤ ደህንነታቸው እንዲጠበቅም የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል። ፀረ ኢትዮጵያ እና ፀረ ሰው የሆነውን የህወሓትን ሥርዓት ለመጣል እና በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲ፣ እኩልነትና የሀገር አንድነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን ለማጽናት ከሥርዓቱ ውስጥም ውጭም የሚደረገውን ትግል እናፋፍም።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!


የወለደችውን የ1 ወር ህጻን ልጅ ገደለች የተባለች ኢትዮጵያዊት በዱባይ ተያዘች

$
0
0

girum
ግሩም ተ/ሀይማኖት
የተባበሩት አረብ ኤምሬት.. ሻርጃ ውስጥ የወለደችውን የአንድ ወር ህጻን ገድላ በኮርኒስና ኮንክሪት ውስጥ የደበቀችው ኢትዮጵያዊት መያዟን ካሊጅ ታይምስ ዘገበ። ጨካኝ…ባላት ኢትዮጵያዊት ላይ Mother kills love child and stuffs body in box በሚል ርዕስ ካልጅ ታይምስ ዘግባውን አቅርቧል።
የኤማሬት ቤተሰቦች ጋር የምትሰራው ገዳይ..የገዳይ ፍቅረኛና ሌላ ሴትም በሻርጃ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት ትናንት ማክሰኞ ነው። (ሌሊት በመሆኑ የጻፍኩት ከትላንትና ወዲያ ማክሰኞ ብል ይቀላል)
ፖሊስ በስጠው መግለጫ ይፋ እንዳደረገው ከሆነ ዝም ብሎ ሳይሆን በቁጥጥር ስር ያዋላቸው በዲ ኤን ኤ ምርመራ ትክክለኛ እናት መሆኗን አረጋግጦ ነው።

የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የመጨረሻ መጽሃፍ –መጽሃፍ ቅዱሱን ተነጠቀ!!

$
0
0

eskinder2

(ዳዊት ከበደ ወየሳ እንደዘገበው)

ሃሳቡን በጽሁፍ ስላቀረበ “አሸባሪ” ተብሎ 18 አመት የተፈረደበት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፤ በእስር ቤት ውስጥ በከፍተኛ ጫና እየደረሰበት መሆኑ ተገለጸ። ምንም ነገር ማንበብም ሆነ መጻፍ ተከልክሏል። በአንድ ለሊት እስከሶስት ግዜ ክፍሉ እየመጡ፤ ከእንቅልፉ በመቀስቀስ ፍተሻ ያደርጉበታል። ይህ ሁሉ የሚደረገው ደግሞ ከህግ እና ህገ መንግስቱ ተጻራሪ በሆነ መንገድ ነው።

ለምሳሌ – በህገ መንግስቱ አንቀጽ 21 ላይ፤ “የህግ እስረኛ መብት ሊጠበቅ ይገባል።” ይላል። አንድ ታሳሪ ሰብአዊ ክብሩም መጠበቅ እንዳለበት ይዘረዝራል። ይህ ብቻ አይደለም። በዚሁ አንቀጽ ቁጥር 2 ላይ “ማንኛውም እስረኛ ከሚቀርበው ሰው ጋር መገናኘት ይችላል” ይልና መብቱን በዝርዝር ሲገለጽ- ከትዳር ጓደኛው፣ ከቅርብ ዘመዶች፣ ጓደኞች ከሃይማኖት አማካሪው፣ ከሃኪሙ እና ከህግ አማካሪው ጋር የመገናኘት መብት እንዳለው ብቻ ሳይሆን፤ ስለጾም እና ጸሎት ለመማከር ቢፈልግ የሃይማኖት አባት ማነጋገር እንደሚችል ተደንግጓል።

በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ ግን ራሳቸውን ከህገ መንግስቱ በላይ ያደረጉ የወህኒ ቤቱ አዛዦች ሰብአዊ መብቱን የሚጋፉ ድርጊቶች በተደጋጋሚ ሲፈጽሙበት ቆይተዋል። ይህም በጨለማ ቤት ውስጥ ከማሰር ጀምሮ ቤተሰብ እና ጓደኞቹ እንዳይጠይቁት እስከማድረግ ድረስ ይዘልቃል። በተለይም ከቅርብ ግዜ ወዲህ ገብረወልድ የተባለ ደህንነት በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ ተመድቦበት፤ በቁም እንዲሰቃይ እያደረገው ነው። በቀን እና በለሊት በማንኛውም ግዜ ጋዜጠኛ እስክንድር ወደታሰረበት ክፍል በመግባት ያዋክበዋል፤ የሚጠቀምበትንም ቁሳቁስ ይወስድበታል።

ለምሳሌ – እስረኞች እዚያው ከሚሰሩትና ገዝተው ከሚጠቀሙባቸው ቁሳቁሶች መካከል እዚያው ግቢ ውስጥ የሚሰራው መቀመጫ አንዱ ነው። ይህን መቀመጫ ከጋዜጠኛ እስክንድር ክፍል ውስጥ ወስደውበታል። እንዲህ ያለ ተራ ተግባር ነው እየተፈጸመ ያለው። ከእስር ቤት አካባቢ የደረሰን መረጃ እንደሚያስረዳው፤ መቀመጫ ወንበሩን ከጋዜጠኛው ላይ ከወሰዱበት በኋላ፤ በእስር ክፍሉ ውስጥ የሚገኘውን ባልዲ ገልብጦ፤ እንደወንበር ይጠቀምበታል። “ይህን ዘገባ ሲመለከቱ ደግሞ፤ ይህቺኑ ባልዲ ሊወስዱበት ይችላሉ” ብለውናል ዘገባውን ያደረሱልን ግለሰቦች።

ይህን እንደምሳሌ ገለጽን እንጂ፤ በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ ከዚህ በላይ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲደርስበት ነበር፤ አሁንም እየደረሰበት ነው። በአሁኑ ወቅት ምንም አይነት መጽሃፍ ወይም ወረቀት እንዲኖረው አይፈቀድለትም። ባለፈው ሳምንት ክፍሉን የበረበረው ገብረወልድ ሲያስጠነቅቀው፤ “እስክሪብቶ እንኳን ይዘህ እንዳይህ አልፈልግም።” ሲል ነበር የዛተበት። ሌላው ቀርቶ እስክንድር ያነበው የነበረውን የመጨረሻ መጽሃፍ – መጽሃፍ ቅዱሱን ጭር ወስደውበታል። ይህን መጽሃፍ ቅዱስ በእስር ላይ በነበረበት ወቅት ባለቤቱ ሰርካለም ፋሲል የሰጠችው ነበር። ከምንም ነገር በላይ ግን ከአምላኩ ጋር የሚገናኝበት፤ በጸሎት ግዜ የማይለየውን መጽሃፍ ቅዱስ የወሰዱበት የጋዜጠኛውን ቅስም ጭምር ለመስበር ቢሆንም፤ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ግን አሁንም በመንፈሰ ጠንካራነት ከሚታወቁት እስረኞች መካከል አንዱ ነው።

ኢትዮጵያ በህገ መንግስቷ ላይ እንደተገለጸው ከሆነ የአለም አቀፍ ሰብአዊ መብቶችን ትቀበላለች። ሆኖም በጋዜጠኛ እስክንድር ላይ የሚደርሰው ግፍ ግን የሰው ልጅ ሊሸከመው የሚከብድ ነው። ትላንት ለሌሎች ኢትዮጵያውያን መብት መከበር ይቆረቆር እና ይጽፍ የነበረው ጋዜጠኛ ህክምና ጭምር ተከልክሎ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው። ይቅርታ ጠይቆ እንዲወጣ ተጠይቆ ፈቃደኛ ባለመሆኑጥርስ ተነክሶበታል። እንደኢትዮጵያ አለም አቀፉን የሰብአዊ መብት አያያዝ የፈረሙ አገሮች የእስረኞችን ሰብአዊ ክብር ይጠብቃሉ። እስረኞች እንደየሃይማኖታቸው መጽሃፍ ቅዱስም ሆነ ቅዱስ ቁርአን እንዳያነቡም ሆነ እንዳይኖራቸው አይከለከሉም፤ በኢትዮጵያ ግን እየሆነ ያለው ከዚህ በተቃራኒ ነው። (በዚህ አጋጣሚ የቤተ ክርስቲያን ሰዎች – የጋዜጠኛው መጽሃፍ ቅዱስ እንዲመለስለት ጠቅላይ ሚንስትሩን እንዲጠይቁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን)

በአሁኑ ወቅት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በታሰረበት ክፍል ውስጥ፤ እሱን ጨምሮ አምስት እስረኞች አሉ። ከነሱም ውስጥ “መንግስትን በሃይል ወይም በመፈንቅለ መንግስት ለመገልበጥ ሙከራ አድርጋችኋል” ተብለው ሞት የተፈረደባቸው ጌታቸው ብርሌ እና መላኩ ተፈራ፤ ከመኢዴፓ ክንፈሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) እና በከፍተኛ ሙስና የታሰረው የጉምሩኩ ገብረዋህድ አብረው ነው የታሰሩት።

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ከታሰረ በኋላ፤ ሃብት እና ንብረቱን – ገንዘብ እና ቤቱን ሳይቀር መንግስት አግዶበታል። የወላጆቹን ንብረት እንዳይሰበብ ሆኗል። በሚሊዮን ይቆጠር የነበረውን እና እናቱ በባንክ አካውንታቸው ያስቀመጡት ገንዘብ ከፍርድ ቤት እግድ ውጪ እንዳይንቀሳቀስ ተደርጓል። እናቱ በህይወት በነበሩበት ወቅት፤ ክሊንካቸውን እንዲዘጉ ከተደረጉ በኋላ ንብረታቸውን አዘርፍታል። አራት ኪሎ የሚገኘው ቤታቸው ተወስዶባቸው ሆቴል ውስጥ ነበር የሚኖሩት። በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ፤ የእስር ብቻ ሳይሆን የግል መኖሪያ ቤቱ እና ንብረቱ ጭምር እግድ ወጥቶበታል። ይሄ ሁሉ ሆኖ ግን ከሁለት አመት በፊት፤ የመጨረሻ ውሳኔ ሲሰጠው፤ “እኛ ሁላችን እናልፋለን። ልጄ ናፍቆት እክንድር አድጎ፤ አንድ ቀን ንብረታችንን ያስመልሰዋል።” የሚል ምላሽ ለፍርድ ቤቱ መስጠቱ ይታወሳል።

ከዚህ በታች ያወጣነው ለፍርድ ቤቱ የተጠየቀው የእግድ ደብዳቤ ነው። በደብዳቤው ላይ እንደተገለጸው፤ 1ኛ ንፋስ ስልክ ላፍቶ የሚገኘው G+2 መኖሪያ ቤት፤ ከእናቱ በውርስ ያገኘው የካ ወረዳ የሚገኘው ትልቅ ቪላ ቤት እንዲሁም ልጁን ናፍቆት እስክንድርን ትምህርት ቤት ያመላልሱበት የነበረው አቶዝ መኪና በባለቤቱ በወ/ሮ ሰርካለም ተመዝግቦ እንደሚገኝ ደብዳቤው ገልጾ፤ በመንግስት እንዲወረስ ጥያቄ ቀርቧል።

በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ በወረዳው አመራር ላይ በተወረወረው ቦምብ 2 ልጆች ሞቱ * አመራሩና ባለቤታቸው ቆስለዋል

$
0
0

news
የደህሚት ድምጽ እንዘገበው በደቡብ ወሎ ዞን፤ ቦረና ወረዳ ውስጥ ሓምሌ 4/2007 ዓ/ም ወደ ወረዳው አመራሩ በተወረወረው ቦምብ ምክንያት 2 ልጆች መገደላቸው ተገለፀ።

በአማራ ክልል፤ ደቡብ ወሎ ዞን፤ ቦረና ወረዳ ውስጥ ሓምሌ 4/2007 ዓ/ም ከሌሊቱ 5 ሰዓት ላይ በወረዳው አመራር በአቶ መሓመድ ረሽድ ላይ በተወረወረው ቦምብ 2 ልጆች መሞታቸውና ራሱና ባለቤቱም ጭምር ክፉኛ በመቁሰላቸው ምክንያት ደሴ ሆስፒታል እያተካሙ መሆናቸውና እስካሁን ድረስም ድርጊቱ የፈፀመው አካል እንዳልተያዘ ለማወቅ ተችሏል።

በአሁኑ ግዜ በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የስርዓቱ ባለስልጣናት በህዝቡ ላይ በሚያደርሱት ከፍተኛ ችግር ምክንያት ህዝቡ በአስተዳድሪዎቹ ላይ የበቀል እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ይታወቃል።

አለምነህ ዋሴ ለምን ከራድዮ ፋና ከዜና መጽሔት መሪነት እንደተነሳ ይናገራል (የሚደመጥ)

$
0
0

አለምነህ ዋሴ ለምን ከራድዮ ፋና ከዜና መጽሔት መሪነት እንደተነሳ ይናገራል (የሚደመጥ)

Alemeneh

ፍርድ ቤቱ ለሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የሰጠው ዋስትና በፖሊስ ታገደ

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

11855873_752610074864653_9011892683978376437_nከምርጫው ማግስት ከአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በፖሊስ ተይዘው ነሃሴ 6/2007 ዓ.ም እያንዳንዳቸው በ15 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ ተጠይቀው የነበሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዋስትናቸው በአቃቤ ህግና በፖሊስ መታገዱን የፓርቲው የምዕራብ ጎጃም ዞን አስተባባሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ፖሊስ በአመራሮቹ ላይ ላቀረበው ክስ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ነሃሴ 6/2007 ዓ.ም ከምርጫው ማግስት እየታደኑ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ 8 የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን እያንዳንዳቸው የ15 ሺህ ብር ዋስ አቅርበው እንዲፈቱ የወሰነ ሲሆን ሁለቱ ወዲያውኑ ወጥተዋል፡፡ ይሁንና የዋስትናው ገንዘብ እስኪሞላላቸው እስር ቤት የቆዩት 6ቱ አመራሮች ትናንት ነሃሴ 7/2007 ዓ.ም የክልሉ አቃቤ ህግና ፖሊስ ለማረሚያ ቤቱ ባቀረቡት ጥያቄ ዋስትናቸው መታገዱ ታውቋል፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ዋስትናቸው የታገደው ገንዘቡን ካስያዙ በኋላ መሆኑም ታውቋል፡፡ እንዲከፍሉ የተጠየቁትን ገንዘብ ካስያዙ በኋላ ዋስትና የተከለከሉት አመራሮች፡-

1. ልዑልሰገድ እምባቆም
2. ፋንታሁን ብዙአየሁ
3. መንግስቴ ታዴ
4. አዳነ አለሙ
5. ስማቸው ምንይችል
6. አበባው አያሌው ናቸው

የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተ መንግስት (ክፍል ሦስት) –የሌ/ጀነራል ፃድቃን እና የሌ/ጀነራል አበበ ድብቅ ገመና

$
0
0

ሌተናል ጀነራል ፃድቃን ገ/ተንሳይ

ፃድቃን ገ/ተንሳይ ኤርትራዊ ከሆኑት ወላጆቹ ስራየ አውራጃ ሰገነይቱ ተወልዶ አድጎ ልክ እንደ ሳሞራ የኑስ ወደ ትግራይ የመጣው በስደት ነው፡፡
ከወላጆቹ ጋር ከኤርትራ ተሰዶ ማይጨው የመጣው በ1955 ዓ.ም ነበር፡፡ ወደ ደደቢት በረሀ አምርቶ ህወሓትን የተቀላቀለው የ12ኛ ክፍል ትምህርቱን በማቋረጥ ከመቀሌ ኮብልሎ ነው፡፡
Interview with Lt. General Tsadkan Gebretensae – SBS Amharic
ፃድቃን ገ/ተንሳይ ከእነ ሳሞራና ሌሎች የህወሓት ድኩማን ጀነራሎች በወታደራዊ ዕውቀቱ የተሻለ እንደሆነ ይወራለት እንጂ ማንነቱ በትክክል ሲፈተሽ በደደቢት በረሀ ከወሰዱት እዚህ ግቢ የማትባል የአንድ ወር ወታደራዊ ትምህርት በስተቀር ምንም አይነት እውቀት የሌለው፣ በውጊያም እንደ መለስ ዜናዊና ሳሞራ የኑስ እልምያለ ፈሪ እና በየትኛውም ጦርነት ላይ ተዋግቶም ሆነ አዋግቶ የማያውቅ እንደሆነ እሱን በቅርበት የሚያውቁት ሀቁን ይመሰክራሉ፡፡
አነሩ መለስ ዜናዊ ድመቶችን በዙሪያው ሰብስቦ ነብር መስሎ ለመታየት ለ21 ዓመታት ሲፍጨረጨር እንደታየው ሁሉ ወጠጤው ፃድቃን ገ/ተንሳይም በግልገሎች መካከል ቆሞ ሰንጋ መስሎ ለመታየት ሞክሯል፡፡

በ1971 ዓ.ም ዓብይ ወዲ እና ዓዲ ኮኾብ እንዲሁም በተጨማሪ በ1973 ዓ.ም ሀውዜን ላይ በተደረጉት ውጊያ መሰል መጠነኛ መቆራቆሶች ፃድቃንን ከድንጋይ ስር ተደብቆ በፍርሀት ሲርበተበት በአይኖቹ በብረቱ እደተመለከተው የቀድሞው የህወሓት ነባር ታጋይ ገ/መድህን አርአያ ይናገራል፡፡

በመሆኑም ሦስት ጊዜ በተደጋጋሚ ፈርቶ ከጦር ሜዳ የሸሸው ፃድቃን ገ/ተንሳይ ለአምስት ወራት መታሰሩን ከህወሓት ዶሴ ላይ ሰፍሮ የሚገኘው የኋላ ታሪኩ ያስረዳል፡፡ ነገር ግን ከመለስ ዜናዊና ከስብሀት ነጋ ጋር ባለው የጠበቀ ወዳጅነትና ቅርርብ የእስር ጊዜውን ካጠናቀቀ በኋላ በለስ ቀንቷቸው መላ አገሪቱን እስከ ተቆጣጠሩበት 1983 ዓ.ም ድረስ በኮሚሰርነት ተመድቦ ቆይቷል፡፡ ቢሆንም ዳር ቆሞ ሲመለከት ኖረ እንጂ አንድም ጊዜ ተሳስቶ ጦርነት አልመራም፡፡

ፃድቃን ገ/ተንሳይ ከበረሀ ጀምሮ ፈፅሞ በማይግባባውና እጅግ በጣም ይጠላው በነበረው ሀየሎም አርአያ ግድያ ከመለስ ዜናዊ፣ ስብሀት ነጋ እና አርከበ ዑቁባይ በተጨማሪ እጁ እዳለበት መቶ በመቶ የተረጋገጠ ሀቅ ነው፡፡

ፃድቃን ገ/ተንሳይ ከኤርትራ ጋር በተደረገው ውጊያ እሱ ባወጣው መቶ በመቶ የተሳሳተ የጦር ስልት ምክኒያት በ10 ሺህዎች የሚቆጠሩ የደሀው የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆች ፆረና ላይ ያለአግባብ በከንቱ ረግፈው ቀርተዋል፡፡ ሬሳቸው እንኳን የሚለቅመው ጠፍቶ በፆረና ተራሮች ላይ ተዘርተው አፅማቸው ተልከስክሶ አሁንም ይገኛል፡፡ መሀይሙ ጀነራል ፃድቃን የቀየሰው የጦር ንድፍ መቶ በመቶ ሲበለሻሽና ከፍተኛ እልቂት ሲደርስ ከሱ በታች ያሉ ሌሎች ጀነራሎችን አስከትሎ ከአከባቢው ሸሽቷል፡፡
ፃድቃን ገ/ተንሳይ በጡረታ ስም ከሰራዊቱ ይገለል እንጂ በስልጣን ዘመኑ በዘረፋ ያካበተው ከፍተኛ ሀብት ሳያንሰው ኤታማጆር ሹም በነበረበት ጊዜ ያገኘው የነበረው ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ሳይሸራረፍ ሙሉ በሙሉ ተከብሮለት በእጅጉ በተንደላቀቀ ህይወት ውስጥ ይገኛል፡፡

ሌተናል ጀነራል አበበ ተ/ኃይማኖት ወይንም ጆቤ

መቀሌ የተወለደው አበበ ተ/ኃይማኖት ህወሓትን የተቀላቀለው በ1968 ዓ.ም ሲሆን ልክ እንደማናቸውም የህወሓት ጀነራሎች የአንድ ወር ወታደራዊ ስልጠና ከወሰደ በኃላ የሐለዋ ወያኔ ባዶ ስድስት ወይንም የትግራይ ጓንታናሞ ኃላፊ ሆኖ በቀጥታ ቡምበት ላይ ተመደበ፡፡
የታጋዮች ቀራኒዮ የነበረውና ዕልፍ ዓዕላፍ ንፁሀንን ህይወት ቅርጥፍ አድርጎ የበላው ያ አደገኛ ወህኒ ከቡምበት ተነስቶ ወደ አጽርጋት ሱር ከተዛወረበት 1969 ዓ.ም እስከ 1974 ዓ.ም ኃላፊው አበበ ተ/ኃይማኖት ነበር፡፡
abebe tekelehaimanot
ብስራት አማረ፣ ታደሰ መሰረት፣ ተስፋዬ መረሳ፣ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል፣ ተስፋዬ አፅብሃ፣ ዘአማኑኤል ለገሰ፣ አበበ ዘሚካኤል፣ ዘርዓይ ይህደጎ፣ ሐሰን ሽፋ እና ክንፈ ገ/መድህን በዋነኝነት ከአበበ ተ/ኃይማኖት በተጨማሪ ሐለዋ ወያኔ ወይንም ባዶ ስድስት በተባለው አደገኛ ወህኒ ውስጥ በየጊዜው በሚታሰሩ ታጋዮች ላይ ሰቆቃና አሰቃቂ ግድያ ሲፈፅሙ የኖሩ ናቸው፡፡

አበበ ተ/ኃይማኖትና ሌሎችም ሰቆቃና አሰቃቂ ግድያ ፈፃሚ የህወሓት ታጋዮች ተጠሪነታቸው ለመለስ ዜናዊ፣ ስብሀት ነጋ እና አባይ ፀሐዬ ነበር፡፡
አበበ ተ/ኃይማኖት ወይንም ጆቤ የሐለዋ ወያኔ-ባዶ ስድስት ወህኒ ቤት ኃላፊ ሆኖ በሰራባቸው ዓመታት ውስጥ በግፍ በታሰሩ ንፁሀን ታጋዮች ላይ እንዲፈፀሙ ካደረጋቸው በርካታ የማሰቃያ ወይም የ”ቶርቸር” ድርጊቶች መካከል ሴቶችንም ጭምር ርቃን ገላቸውን ከግንድ ጋር በማሰር ለረጅም ጊዜ ፀሀይና ብርድ እንዲፈራረቅባቸው ማድረግ፣ ገልብጦ የእግር መዳፍን መግረፍ፣ ከ16 ኪሎ ግራም በላይ የሚመዝን አሽዋ ከወንዶች ብልታቸው ላይ ከሴቶች ደግሞ ጡታቸው ላይ ማሰር፣ በፈላ ውሀ መቀቀል፣ በጋለ ብረት መቀመጫን ማቃጠል፣ ጭንቅላትን ወደታች ዘቅዝቆ ማንጠልጠል፣ ባዶ እግርን በሾህ ላይ እንዲራመዱ ማድረግና ከፍተኛ ክብደት ያለው ብረት ወይንም ድንጋይ አሸክሞ ለረጅም ጊዜ ማቆም ዋና ዋና ዎቹ ናቸው፡፡

እነኚህ የማሰቃያ ወይንም “ቶርቸር” አይነቶች ዛሬም በየእስር ቤቱ በስራ ላይ እተተገበሩ ይገኛሉ፡፡ ማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ የህወሓት ደህንነቶች ሴቶችን በወር አበባቸው ሳይቀር ልብሶቻቸውን አስወልቀው ዕርቃናቸውን አቁመው በሀፍረተ ስጋቸው እየተሳለቁ የሚመረምሯቸው መሆኑ በቅርቡ የተረጋገጠ ሀቅ ነው፡፡
አበበ ተ/ኃይማኖት በሱር የሐለዋ ወያኔ ወይም ባዶ ስድስት ኃላፊ በነበረበት ወቅት የወልቃይት ህዝብ በገፍ እየታፈሰ እንዲረሸንና በጅምላ እዲቀበር በማድረግ ዘር ማጥፋት ፈፅሟል፡፡

አበበ ተ/ኃይማኖት ከአደገኛው እስር ቤት ኃላፊነቱ በ10 ሺህዎች በሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ሰቆቃና ጭፍጨፋ ከመፈፀምና የገበሬውን ሰራዊት ማርኪሲዝምና ሌኒንዝም ርዕዮተ ዓለም ከማስተማር በዘለለ ለአንድ ጊዜ እንኳን ውጊያ ላይ አልተሳተፈም ፡፡ ልክ እንደ ሳሞራ እና ፃድቃን እሱም ለጀነራልነት የበቃው ለእነ መለስ ዜናዊና ስብሀት ነጋ ባለው ታማኝነትና አጎብዳጅነት ብቻ ነው፡፡

አገራችንን ረግጠው በኃይል ለመግዛት ከቻሉ በኋላም እንኳን ሊኮፈስባት በገንዘብ የገዛት የህግ ባችለር ዲግሪው ከሙያው ጋር የማትገናኝ በመሆኗ እሱንም እንደሌሎቹ የበረሃ ጓዶቹ የህወሓት ጀነራሎች የጦር ማሃይምነት ድቅድቅ ጨለማ ውጦት ቀርቷል፡፡

አበበ ተ/ኃይማኖት ወይም ጆቤ ልክ እንደ ሳሞራ የኑስ የወጣለት ሴሰኛ በመሆኑ የበረሃ ጓዶቹን ሚስቶች ሳይቀር በማባለግ ይታወቃል፡፡ የአየር ኃይል አዛዥ በነበረበት ወቅት አየር ኃይል ጠ/መምሪያ ቢሮ የምትሰራውን የሜ/ጀነራል መሃሪ ዘውዴን ባለቤት በማባለጉ “ባለቤቴን ማባለጉ አልበቃ ብሎ ባልሽን ወደ አንዱ ጦርነት ስለምልከው እና ስለሚሞት ልጅ ውለጅልኝ እያለ ባለቤቴን ቁምስቅሏን እያሳያት ነው፤” ሲል መሀሪ ዘውዴ ክንፈ ገ/መድህን በተገደለበት የህወሓት ከፍተኛ መኮንኖች ስብሰባ ላይ ከሶታል፡፡ ከእሱ በኋላ የአየር ኃይል አዛዥ የሆነውን ሜጀር ጀነራል ሞላ ኃ/ማሪያምን ሚስቱን ቢሰጠው የጀነራልነት ማዕረግ ትከሻው ላይ እንደሚያስርለት ነግሮት ሞላም በጉዳዩ ተስማምቶ የሁለት ልጆቹን እናት ለአበበ ተክለ ኃይማኖት በማከራየት ከኮሎኔልነት ጀነራል በመሆን ህልሙን አሳክቷል፡፡ በመጨረሻም የሞላ ኃ/ማሪያም ትዳር በአበበ ተ/ኃይማኖት ምክንያት ሊፈርስ ችሏል፡፡

አበበ ተ/ኃይማኖት የአየር ኃይል አዛዥ በነበረበት ወቅት አየር ኃይል የቁልቁለት ጉዞ በሸርተቴ የተጓዘ ሲሆን የራሽያን ጀነራሎች በአማካሪነት ስም አምጥቶ ቀዳዳውን ለመሸፈን ተፍጨርጭሯል፡፡

ብ/ጀነራል ተጫኔ መስፍንንም ከእስር ቤት አውጥቶ አማካሪው አድርጎታል፡፡

ከሴሰኝነት በተጨማሪ የህወሓት ዋነኛ መለያዎች የሆኑት ዘረኝነትና ሌብነት አበበ ተ/ኃይማኖት ላይም በጉልህ ይታዩ ነበር፡፡ በመሆኑም አየር ኃይሉን አንድ አይነት ቋንቋ በሚናገሩ የአንድ አካባቢ ሰዎች ሞልቶታል፤ እስኪበቃውም መዝብሮታል፤ አስመዝብሮታል፡፡

አበበ ተ/ኃይማኖት በአንድ ወቅት በአሉዌት ሄሊኮፕተር ተሳፍሮ ወደ ጋምቤላ ሲሄድ ካላበረርኩ ብሎ አብራሪውን በማስቸገሩ አብራሪው ቦታውን ለቆለት ተቀብሎ አሉዌት ሄሊኮፕተሯን ልክ እንደ እምቧይ ከምድር አፍርጧታል፡፡ በተጨማሪም አበበ ተ/ኃይማኖት ሲጋራ፣ ዊስኪ እና ሴት ለማስመጣት በየከተማው ሄሊኮፕተር ይልክ ነበር፡፡
አበበ ተ/ኃይማኖት ምንም እንኳን ዛሬ በስጋ ከህወሓት የተነጠለ ቢመስልም በመንፈስ ግን ጨርሶ አልተለየም፡፡ በ1993 ዓ.ም የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ከሁለት ሲሰነጠቁ በአንጃነት ተፈርጀው የተባረሩት የቀድሞ ታጋዮች እንዲመለሱ ተወስኖ ጥሪ ሲደረግላቸው አበበ ተ/ኃይማኖትንም አካተውት ወደ ባንዳዎች ስብስብ ለመመለስ እና በባንዳነቱ ለመቀጠል ስምምነቱን ገልጿል፡፡

የምድር ኃይሉ እና የአየር ኃይሉ ቁንጮ የነበሩት ሁለቱ የህወሓት ጀነራሎች አበበ ተ/ኃይማኖት እና ፃድቃን ገ/ተንሳይ ከመከላከያ ሰራዊቱ ሲወገዱ በህወሓት መንደር አንዳች ለውጥ አለመታየቱ የሰዎቹን ሚናየለሽ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ የጀነራልነትን ማዕረግ ለበሱት እንጂ ከጀነራልነቱ ማዕረግ ጋር የሚመጣጠን ወታደራዊ ዕውቀት የሌላቸው ቦታ ብቻ የያዙ ባዶ ዕቃዎች መሆናቸውን ያረጋግጣል፡፡

ግንቦት 8 ቀን 1981 ዓ.ም ተሞክሮ በከሸፈው መፈንቅለ መንግስት ተሳታፊ የነበሩት ጀነራሎች መረሸን ግን ከአንድ ዓመት በኋላ ደርግን ለውድቀት ዳርጎታል፡፡

የአፋር መስተዳደር አዲስ ጊዜያዊ ርዕሰ መስተዳደር ሾመ

$
0
0

afar

አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው:

በኢህኣደግ ሰርዓት እረጂም ዓመታት በክልል መሪነት በማገልገል ሪከርድ የሰበረው ብቼኛ ኣገልጋይ ኣቶ እስማዒል ዓሊ ሲሮ ባለፈው ምረጫ ለፈደራል ፐርላማ መወዳደራቸውን ተከትሎ ዛሬ ኣዲስ መሪ ተሾሟል።
ዛሬ የተሾሙት ኣቶ ኣዋል ዓርባ ዑንዴ ከምርጫው ቀደም ብሎ ከግብሪና እና ገጠር ልማት ቢሮ ወደ ምክትል ረዕሰ መስተዳደር በማምጣት የተሾሙ ሲሆን ኣሁን ደግሞ ከዛሬ ጀምሮ የክልሉ ጊዜያዊ ፕረዝዳንት ሆኖው ይቆያሉ ተብሏል።
በኣሁኑ ወቅት በኣጣቃላይ በኢህዴግ መሪዎች ዉስጥ ያለውን ኣለመግባባትን ተከትሎ የኣፋር ክልል ካድረዎች ዉስጥም ክፍተኛ የሆነ ኣለመግባባት ኢየታየ ነው።
በነግራችን ላይ የኣፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ( ኣብደፓ) በነገው ዕለት ጣቅላላ ጉባኤ ያድርጋል ትብሎ ይጠበቃል።
በዚህ በነገው ሰብሰባ የክልሉ ምክትል ፕርዝድንት፣ የክልሉ ምክሪቤት ኣፌጉባኤ እና የፓርቲ ኃላፊ ይምረጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ወትርዉም ብሆን የኣፋር ክልል መሪ የሚመረጠው በህወሃት ጣልቃ ገብነት ሲሆን ኣሁን በጊዜዊነት የተሾሙት ኣዋል ዓርባ በክልል መሪነት ይቀጥሉ ኣይቀጥሉ ኣይታወቂም።
ኢህአዴግ ህወሀት ባለፉት ሁለት ኣስርት ዓመታት የብሔር ብሔርሰቦችን መብት ኣክብሬያለሁ በሚል ሽፋን በኣፋር ህዝብ ላይ ያደርሰው በደሎች ኢንኳን ጉልቻ መቀያየርን ቀርቶ እራሱ ኢህአደግ ብቀየሪም ታሪክ ይቅር የማይለው የመግደል፣የማፋናቀል፣የማሰር እና በሃብታቸው እንዳይጠቀሙ በማድረግ የፈጸመው በድሎች በኣፋር ክልል የህወሀት ተቃዋሚዎች እንዲበረከቱ ምክንያት ሆነዋል።
በኣሁኑ ወቅት በኣፋር ክልል ወጣቶች ብዙ የትደራረበ ጥላጫ ለኢህአደግ መንግንስት እንዳላቸው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየግለጹ ሲሆን ለምሳሌ ያህል መንግስት በክልሉ ህዝብን በማፋናቀል እየሰራ ያለው ልማት ተብዮው በኣፋር ኣርብቶ ኣደሮች ህይዎት ላይ ያስከተለው ችግር ቀላል ኣይደለም።
እይዉነት ለመናገር የኣፋር ህዝብ ካሁን በፊት ባልፉት ሰርዓቶች በዚህ ሁኔታ ኣልራበም።
በተለይ በምስራቅ የክልሉ ኣክባቢ በኣዋሽ ወንዝ ዳር ይኖሩ የነበሩ ኣርብቶ ኣደሮች ተፈናቅለው መሬታቸው በሙሉ ለመንግስት የስኳር እርሻ ተከለዋል።
የዚህ ዉጤት እነሆ ዛሬ በህዝብ ላይ ክፊተኛ ረሃብ አስከትሎ የኣለም ኣቀፍ ሚዲያዎች መንጋገሪያ ሆኖ ይገኛል።
በኣፋር ክልል እየሞቱ ያሉት ከብቶች ብቻ ኣይደለም፣ ሰዎቹም እየሞቱ ነው።
ኢስካሁን ባለኝ መረጃ መሰረት በዱብቴ ወረዳ ፣ ዳትባሃሪ ኣከባቢ በራሃብ ና በጥም እንዲሁም የቆሸሸ ዉሃ ጠጥተው
የስምንት ህጻናት ህይዎት ኣልፈዋል።
በሚሌ፣ በኦንዳ ፎኦ አከባቢም ከብቶቻቸው ያለቁባቸው ነወሪዎች እራሳቸው ያጠፉ እንዳሉ ሰሚቼያለሁ።
ሌላው ድግሞ በሰሜን የክልሉ ኣከባቢ ከዳሎል ኢስከ ማጋሌ ወረዳ ያለው የትግራይ መሬት ነው በማለት ነዋሪዎችን በማጋጨት ብዙ ኣፋሮች በወያኔ ሚልሻዎች ተገድልዋል።
በባራህሌ ወረዳ የሚገኘው ኣሞሌ ጨው ለኣንድት የትግራይ ሃብታም ካልሰጠሁ በማለት የባራህሌ ወረዳ ኣፋሮችና ወያኔ ከተፋጠጡ ወራት ተቆጥረዋል።
በዳሉል ወረዳ ኣብዛኛው መሬት በዋያኔ ተጠቃሚነት ለውጭ ኣገር ድሪጅቶች የተሰጠ ሲሆን የቀረው መሬትም በቅርብ ለፖጣሽ ኣምራቶች ተሰጥቶ ህዝብ ገና ካሁን በኋላ ልፈናቀል መሆኑን የኣፋር ክልል የወያኔ ኣገልጋይ ተሰናባቹ እስማዕል አሊ ሲሮ ባለፈው ሳምንት በኢቢሲ በሰጡት መግለጫ የገለጹ ሲሆን ኣሁን በኣዲሱ በዳሉል ወረዳ ለፖጣሽ የተሰጠው መሬት ስፋቱ ከሶስት መቶ ሲልሳ ኣምስት በላይ ስከዌር ኪሎ ሚትር መሆኑን በካምፓኒው ዲህረ ገጽ ኣምቢበውለሁ።
ሌላውና ቀዳሚው የኣፋር ክልል የጨው ሃብት ባለበት የሆነችው ኣፍደራ ሲትሆን በኣፍደራ የጨው መሬት የለለው የወያኔ ባለስልጣን፣የወያኔ ጀነራል የለም።
ኢንዲሁም ባለፈው ሳምንት በኣስመራ ታስረዋል የተባለው የኤረትራ የጻጥታ ሀላፊ ( ሚነስተር ) በኣፍደራ የጨው መሬት ኣላቸው፣ የቀድሞው የትግራይ ክልል መሪ ኣቶ ፀጋይ በርሄን ጨምሮ ኢያንዳንዳቸው የህወሀት መሪዎች በኣፍደራ የጨው መሬት ኣላቸው።
ሌላው ዶቢ ዓስቦ ( የዶቢ ጨው ሲሆን ዶቢ የሚባለው በኣፋር ክልል ኢትዮጲያ ከጀቡቲ በሚያዋስን ቦታ ላይ የሚገኝ የጨው መሬት ነው።
ይህ መሬት ሙሉ በሙሉ የኣንድ ባለሃብት ሆኖ ይሚገኝ ሲሆን እርሱ ማሀመድ ሁመድ ይባላል።
በኣፋሮች ዶቢ ዓስማሀማድ በሚል ቅጽል ሲሙ ሲታወቅ በህወሀት የተለመደው ልማታዊ ባለሃብት የሚል ማዓረግ ተስጦታል።
ለነገሩ ልማታዊ ባለሃብት ማለት የወያኔ ደጋፊ የሆነ ባለሃብት ማለት ኣይደል ?
ትርጉሙ በተዘዋዋሪም ብሆን ይህ ብሆን ነው እንጂ ልማታዊማ ብሆን ሲንት ህዝብ በራሃብ ኢና በዉሃ ጥም እየሞተ እያየ እንዳላየ የሚያልፍ ሃብታም ልማታዊ ባለሃብት ሲባል ምን ትለውለህ ?
የብሔር ብሔረሰቦች መብት ኣስክብረናል በሚል ሽፋን የብሔር ብሔርስቦችን ባህሎች፣ሃይሞኖቶች፣ሃብቶችና ክርሶች እያጠፋና እዘረፈ ያለው ህወሀት በኣፋር ክልል ያለው እውነታ ግን ዜሮ ዜሮ ነው።
ለምሳሌ፦ በየኣጋጣሚው ባህላዊ ጨፈራ በተለቭዥን ከማሳየት የዘለለ የተከበረ መብት የለም ።
ኣራት ነጥብ

ይህ ግጥም የጻፈው ገጣሚ ስሙን እንዳይገለጽ የጠየቀን ሲሆን የኣሊጋራብ ጥቁር ነቢር በሚለው ቅጺል ስሙ ትጠቅመናል።

ጥቅት ሆዳሞች።።።።

ጥቅት ሆዳሞች ህዝብን ስያታልሉ
በሰመ ልማት ኪሳቸው እየሞሉ
አገር አደገች ብለው ድረቅ ብለው ይውሻሉ
እባካቹሁ ሰዎች አንድ ነገር በሉ
አፋር አፋር የኢትዮጲያ አይን የኢትዮጲያ ክብር
የሰው ዘር መገኛ ታሪካዊ ምድር
ሉሲ እኮ አለች የቅርብ ጊዜ ምስክር
ተፅፎ አይልቂም ስንት ብየ ሊዘርዝር
ከዳሉል ጀምሮ፣ ባራሕሌ፣ ኮናባ፣
ኤረብቲ ፣ማጋሌ፣ አበኣላ፣ ስትገባ
ክርስ መሬቶቹዋ በማዕድን ተውባ
አገሬ ተሰቃየች በድህነት ተረባ
ጨው፣ ፖጣሹ፣ ወርቅ፣ የተከበረ ድንጋይ፣
በውስጧ ተቀበረው የሄ ሁሉ ስቃይ
የት ያለ እድገት ነው በአይን የማይታይ
እነ ሲሮ የሚጮሁት የወያነ አገልጋይ
ዞን አራት ካሉዋን፣ ያሎ፣ ቴሩ
የማዕድን ሀብታችን ተጠንው በመረመሩ
ማእቀብ ተደርጎበት እንዳይቆፈሩ
የአብዴፓ መሪዎች ለሆዳቸው ያደሩ
አንዱ የሄ ነው ከድብቅ አጀንዳቸው፣ ከሚስጥሩ
ዞን አምስትም እንደዚሁ፣ ዞን ሶስት ጋቢ ራሱ፣
ዞን አንድም እደዚሁ አውሲ ራሱ፣
ህዝብን እያጋጩ እርስ በርሱ
አገር እንዳይለማ በህብረት እንዳይርሱ
በላሌ፣ በሰዳዓ፣በሆራ፣በኬኬ እየዘለሉ ማጫወት
በቴልቪዢን መስኮት ደጋግሞ ማሳየት
በዚሁ ከሆነ የተጠበቀው መብት
ዶሮን ሊያታልሏት በማጫኛ አሰረዋት
ቋንቋችን ባህላችን ከትንጥ የቆየ ነው
ህጋችን ደንባችን የአፋር ማድዓ ነው
አዲስ ነገር የለም አሁን ያገኘነው
አዲስ ነገር ቢኖር የቀኝ አገዛዝ ነው
የህዝብ ጥያቄ አንድና አንድ ብቻ ነው
ፊተጥ፣ ዴሞክራሲ፣ሰፍኖ በልማት ማደግ ነው
መሪያችን ስሆን እኛ የመረጥነው
በቋንቋቸው፣ በስማቸው አፋሮች
በእጅ አዙር የሌላ አገልጋዮች
አቅም የሌላቸው ድንቆሮ መሀይሞች
ህዝበባችን አጠፉት የአብዴፓ መሪዎች
ሐጂ ሱዩም፣ አንበጣ እስማዕል ሲሮ
ሌላ መሪ አላቸው በድብቅ በሰተጓሮ
ተትእዛዝ የሚያስተላሊፍ አጀንዳው ዘርዝሮ
ገብረፂዮን ወያኔ ከፈደራል ቢሮ
የተማረ አልወጣም ከዚህ ሁሉ ወጣት
ወራሽ ሰለታጣ ነው እንዴ፧ ሲሮን የሚያምኑት
ህዝባችን እያየ አይናቸው የጨፈኑት
ዝም ብለን አናይም እየጠፋ አገራችን
አኩ ኢብን አፋር ብቅ አለ ከጎናችን
በአብዴፓ መርዝ የደነዘዘ አካላችን
በቃ ተነሱ ብሎ ቀሰቀሰን ከእንቅልፋችን
አኩ ኢብን አፋር አኩ ኢብን አፋር
የመጀመሪያ ጀግና የመጀመሪያ ደፋር
በአብዴፓ የተዘጋው የነፃነት በር
ከጎኑ እንሰለፍ ይህን ህብረት ለመስበር
ገጣሚ
፨ የአሊ ጋራብ ጥቁር ነብር ፨

13/ 08 /2015
ፊትህ ለኢትዮጲያ ህዝብ
ክብር ለነፃነት ተጋዮች
ውርደት ለወያኔ


ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 77 (PDF)

$
0
0

ከረዢም አመታት በፊት የተጀመረው የባህርዳር ሞጣ ብቸና መንገድ አሁንም ችግር እየፈጠረ መሆኑ ተነገረ

$
0
0

Motta 2012 week1 044-ከአመታት በፊት ተጀምሮ በማዝገም ላይ ያለው የባህርዳር ሞጣ ደጀን መንገድ አሁንም በንግድ እንቅስቃሴያቸው ላይ ከፍተኛ ችግር እየፈጠረባቸው መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ በትራንስፖት ቢሮ የትራንስፖርት አገልግሎት የስምሪት ተተኪ የስራ ሂደት ውስጥ የሚገኙ ባለሙያ እንደተናገሩት መንገዱ በተደጋጋሚ በመበላሸቱ እና ለረዢም ጊዜ ባለመሰራቱ ህብረተሰቡ መቸገሩን ገልጸው፤ለመንገድ ስራ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤቶች ስራውን እንዲያጠናቅቁ በተደጋጋሚ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ቢጻፍላቸውም ስራውን ለማጠናቀቅ አልቻሉም።
ባለሙያው በተጨማሪ እንደተናገሩት የስራውን መጠናቀቅ ተከታትሎ ለማስፈጸም ሃላፊነቱን የወሰደው የፌደራል ትራንስፖርት ሚኒስቴር የህዝቡን ተደጋጋሚ ቅሬታ ሰምቶ እንዳልሰማ መሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግር እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
ከአዲስ አበባ በቡሬ ባህርዳር አሁን የሚያገለግለው የአስፓልት መንገድ 565 ኪሎ ሜትር ሲሆን ከአዲስ አበባ በሞጣ ባህርዳር ግን አንድ መቶ ኪሎ ሜትር የሚቀንስ በመሆኑ ነጋዴዎች የሸቀጥ ጭነታቸውን በሞጣ በኩል በመጫን በትራንስፖርት መቀነስ ምክንያት የሚኖረውን የኑሮ ውድነት በመጠኑ ለማገዝ የሚያስችል የንግድ እንቅስቃሴ ለመፍጠር የሚችሉበትን ዕድል እንዳላገኙ ነጋዴዎች ይናገራሉ፡፡
በተለይ ከደጀን ብቸና በሚወስደው መንገድ ብቸና ከተማ አካባቢ የሚገኘው የሰዋ ወንዝ ድልድይ ባለፈው የክረምቱ ወራት ወቅት መሰበሩ በርካታ ችግሮችን እንዲያሳልፉ መገደዳቸውን የሚናገሩት የብቸና ከተማ ነዋሪዎች፣ የዚህ መስመር የአስፓልት መንገድ ለምን በተያዘለት ጊዜ እንደማይጠናቀቅ ሁሌም እንደሚገረሙ ተናግረዋል፡፡
ከደጀን ፈለገ ብርሃን ያለው የመንገድ ፕሮጀክት ሳትኮን በሚባል ሃገር በቀል የመንገድ ስራ ተቋራጭ እየተከናወነ ቢገኝም የጥራቱ ጉዳይ አሳሳቢ ከመሆኑና በአካባቢው የተሰሩት ድልድዮች ከማነሳቸው የተነሳ በስራቸው ጎርፍ ማሳለፍ አቅቷቸው በላያቸው ላይ እየፈሰሰ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ያሰማሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሳምሶን ወንድሙ ከሁለት አመት በፊት ባደረጉት ገለጻ ከደጀን ፈለገ ብርሃን ድረስ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት በቶሎ እንደሚጠናቀቅ አስታውሰው፥ ከዘማ ወንዝ እስከ ባህርዳር ድረስ ያለው የመንገድ ፕሮጀክትም በ2006 ይጀመራል በማለት በነሃሴ ወር 2005 ዓ.ም ቃል ቢገቡም የመንገድ ስራው ፐሮጀክት በዚህ አመት ተጀምሮ በመጓተት ላይ መሆኑን ቅሬታ አቅራቢዎች ይናገራሉ፡፡
የሳትኮን ባለቤት አቶ ሳሙ ኤል ተኽላይ የሰራተኞችን ደመ ዎዝ ለወራት በመ ከልከልና በማ ሰቃየት፣የመ ኪ ና ክራይ በወቅቱ ባለመ ክፈልና ስራን በማጓተት በተደጋጋሚ ቢከሰሱም፣ ገዢ ው ፓ ርቲ ለሁሉም ፕሮጀክቶቻቸው ከለላ በመ ስጠት ከተጠ ያቂነት ነጻ ሲያደርጋቸው መ ቆየቱን ታዛቢዎ ች ይናገራሉ፡፡
ሳትኮን ኮንስትራክሽን በህውሃት መንግስት ታቅፈው በአዲስ አበባ በስፋት ከሚንቀሳቀሱ የህወሃት ደጋፊ የሪልስቴት ባለሃብቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በርካታ የግንባታ ስራዎችን ያለ ጨረታ ይወስዳል። አምባሳደር ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ አካካየ ሪልስቴት፣ክንዴ ሃጎስ ሪልስቴት፣ ተክለብርሃን አምባዬ ሪልስቴት፣ ጊፍት ትሬዲንግ፣ ሲቲ ዋይድ ኢንጂነሪንግ፣ አሴ ትሬዲንግ፣ ስብሃቱ እና ቤተሰቡ ትሬዲንግ ከህወሃት ጋር በቅርብ የሚሰሩ የሪል ስቴት ኩባንያዎች ናቸው።

Source:: Ethsat

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ለጋንቦ ወረዳ አሁንም ውጥረቱ እንደተባባሰ የቪዲዪ ማስረጃ ደርሶናል (ቢቢኤን)

$
0
0

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ለጋንቦ ወረዳ አሁንም ውጥረቱ እንደተባባሰ የቪዲዪ ማስረጃ ደርሶናል (ቢቢኤን)

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ለጋንቦ ወረዳ አሁንም ውጥረቱ እንደተባባሰ የቪዲዪ ማስረጃ ደርሶናል (ቢቢኤን)

“አንገነጠልም –ትግላችን የኦሮሞ ሕዝብ ውሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ማድረግ ነው”–ብ/ ጀነራል ኃይሉ ጎንፋ ከአስመራ (የሚደመጥ)

$
0
0

ከሁለት ሳምንት በፊት አራት የኦነግ ድርጅቶች ወደ አንድ መምጣታቸውን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል:: ይህን ተከትሎ ከአውስትራሊያ የሚሰራጨው ሲቢኤስ ራድዮ ብ/ጄ ኃይሉ ጎንፋ፤ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር – ኦነግ (በአባ ነጋ ጃራ የሚመራው) ምክትል ሊቀ መንበር፤ ስለ ኦነግ ዳግም መሰባሰብ አንጋግሯቸዋል:: ጀነራሉ ተበታትነን ምንም አናመጣም ብለዋል:: “ኦነግ የሚለውን ስያሜ በባለቤትነት እኔ ነኝ ብሎ የሚወስደው ማን ነው?” ለሚለው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል:: ያድምጡት::

General

ከህዝብ ጆሮ እና አይን የተደበቁ የዲያስፖራ ቀን ትችቶች –ልዩ ፕሮግራም በሳዲቅ አህመድ (ቢቢኤን ሬዲዮ)

$
0
0

ከህዝብ ጆሮ እና አይን የተደበቁ የዲያስፖራ ቀን ትችቶች
“መላኒየም አዳራሽ በሰላ ትችት ስትናወጥ፣ በመዋሸት የሚታወቁት የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከማፍጠጥና ከመንቆራጠጥ በስተቀር አማራጭ አልነበራቸዉም”
እንደ ታዳሚዎች አገላለጽ
ልዩ ፕሮግራም በሳዲቅ አህመድ
(ቢቢኤን ሬዲዮ)
[jwplayer mediaid=”45895″]
Sadik Ahemed Journalist

Viewing all 2784 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>