Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all 2784 articles
Browse latest View live

በተቃዋሚ ድርጅቶች ላይ የሚደረገው ማዋከብ ይቁም፣ የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ አሁኑኑ ይፈቱ

$
0
0

ማክሰኞ ኅምሌ 1፣ 2006 ( July 8፣ 2014) shengoየህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ በህጋዊነትና በሰላማዊ መንገድ  የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ድርጅቶች አመራር አባላት ከሆኑት ውስጥ አቶ ሀብታሙ አያሌውንና አቶ ዳንኤል ሽበሽን ከአንድነት  ፓርቲ፣ አቶ የሽዋስ አሰፋን ከሰማያዊ ፓርቲ እንዲሁም አቶ አብረሀም ደስታን ከአረና ፓርቲ ማሰሩን ተረድተናል።  የተጠቀሱት ግለሰቦች በሀገራችን ውስጥ ያለው የመብት መረገጥ፣ የፍትህ መጥፋት፣ የህግ የበላይነት አለመኖር ፣ ግፍ  ስቃይና መከራ እንዲያበቃ ምሳሌ የሆነ ትግል በሰላማዊ መንገድ ሲያካሂዱ የቆዩ ለመሆናቸው እጅግ ብዙ መረጃ መጥቀስ  ይቻላል።  [ሙሉውንለማንበብእዚህይጫኑ]

 

 

 


ተበላ! ጀርመን በላችው! (VOA Amharic)

$
0
0

VOA Amharic ጎ…………ል! ጀርመን 1 አርጀንቲና 0 – ሃያኛው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ግጥሚያ ተጠናቀቀ፡፡ ጀርመን አርጀንቲናን በፍፃሜ ግጥሚያ ለሁለተኛ ጊዜ ድል ነሣች፡፡

6D963441-D16E-4DE3-97F9-05306B641415_w268ጀርመን አርጀንቲናን በፍፃሜ ግጥሚያ ለሁለተኛ ጊዜ ድል ነሣች፡፡ ጨዋታው በተጨማሪ የጨዋታ ጊዜ በተቆጠረች ግብ 1 ለባዶ አለቀ፡፡

በሪዮ ዴ ጃኔይሮው ማራካና ስታዲየም የተካሄደው ጠንካራ ሊባል የሚችል ትንቅንቅ የታየበት ጨዋታ ዋናው የግጥሚያ ጊዜ /ዘጠና ደቂቃው/ የተጠናቀቀው፣ ብዙ የግብ አጋጣሚዎች ተፈጥረው የነበረ ቢሆንም፣ ያለምንም ግብ ባዶ ለባዶ በሆነ ውጤት ነበር፡፡

ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰዓት ዘልቆ በ112ኛው ደቂቃ ላይ 19 ቁጥር ለብሶ የሚጫወተው ማሪዮ ግዮትዘ በድንቅ አስተላለፍ የአርጀንቲናን በረኛ አሳልፎ መረብ ላይ ያስቀመጣት ኳስ የጨዋታውም ለብርቱው የጀርመን ቡድንም በዚህ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያዋም የመጨረሻዋም ግብ ሆነች፡፡

ጎ……………………….ል! ጀርመን የዓለም ዋንጫን ለአራተኛ ጊዜ ወሰደች፡፡

በዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ታሪክ ጀርመን 4 ጊዜ አሸንፋ አምስት ጊዜ ያሸነፈችውን ብራዚልን እየተከተለች ነች፡፡

በዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ታሪክ ውስጥ እአአ በ1954 ዓ.ም ልክ የዛሬ ስድሣ ዓመት ስዊትዘርላንድ አዘጋጅታው በነበረው 5ኛው የዓለም ዋንጫ ላይ ጀርመን ሃንጋሪን 3 ለ 2 አሸንፋ የመጀመሪያውን ዋንጫዋን ወስዳለች፡፡

ከዚያም እአአ በ1974 ዓ.ም እራሷ /የያኔዋ ምዕራብ ጀርመን/ አዘጋጅታው በነበረው 10ኛው የዓለም ዋንጫ ላይ ለፍፃሜ ከሆላንድ ጋር ተገናኝታ 2 ለ 1 አሸነፈች፡፡

እአአ በ1990 ዓ.ም /የዛሬ 24 ዓመት/ ጣልያን ባዘጋጀችው 14ኛው የዓለም ዋንጫ ልክ እንደዛሬው ጀርመንና አርጀንቲና ተገናኝተው፤ ልክ እንደዛሬው ጀርመን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋ ዋንጫውን አስቀረች፡፡

ዛሬ፣ ዕሁድ – ሐምሌ 6/2006 ዓ.ም /በኢት.የዘ.አቆ/ የሪዮ ዴ ጃኔሮው ማራካና ስታዲየም ላይ ጀርመን የዛሬ ሃያ አራት ዓመቱን ታሪክ ደገመች፡፡

የማርዮ ግዮትዘን ጎል ለማየት ከታች የተቀመጠውን ማገናኛ ይጫኑና ይከተሉ፤ http://www.espnfc.com/video/latest-videos/600/video/1948633?&ex_cid=espnapi_affiliate_Google_World_Cup_Video

 4C51EB3A-1295-4F54-A984-6743FA99F22F_w640_sየጀርመኑ ባስቲያን ሽቫይንሽታይገር ከአርጀንቲናዎቹ ሉካስ ቢህሊያና ሊዮኔል ሜሲ ጋር የነበረው ፍጥጫ – ሪዮ ዴ ጃኔይሮ – ማራካና ስታዲየም፤ ዕሁድ – ሐምሌ – 6/2006 ዓም

Hiber Radio: “ጠንክረን በጋራ መታገል እንጂ ማልቀስ የሚያስፈልግበት ወቅት አይደለም”–የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እህት እስከዳር (ቃለምልልስ)

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ሐምሌ 6 ቀን 2006 ፕሮግራም

ቃለ መጠይቅ ከአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እህት እስከዳር ጽጌ ጋር ስለ ወንድሟ አፈና እና ወቅታዊው በሆነው ጉዳይ አጠር ያለ ውይይት አድርገናል። <<...ጠንክረን በጋራ መታገል እንጂ ማልቀስ የሚያስፈልግበት ወቅት አይደለም ...>>(ሙሉውን ያዳምጡት)

ሕወሃትና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያገኘው የማሰቃየት እርምጃዎቹ (ልዩ ዘገባ)

<<...ሰማያዊ ፓርቲ ከመግለጫውም በፊት አስቀድሞ መሪዎቹ ቢታሰሩ የተተኪ አመራር ጉዳይን ተወያይቶበታል...ከህሊና ወቀሳ ለመዳን እያንዳንዱ ይህን ስርዓት ለመታገል የሚችለውን ጠጠር ይወርውር...>>

አቶ ወረታው ዋሴ የሰማያዊ ፓርቲ የፋይናንስ ሀላፊ

<...ስርዓቱ ማንንም ነው የሚይዘው ለመታሰር ወይ ላለመታሰር ወሳኞቹ ስልታኑን የያዙት ሰዎች ናቸው...አሁን አቶ መለስ እንደነበሩበት ጊዜ ማስመሰሉም ብልጠቱም ቀርቷል። ስርዓቱ አብዷል አሜሪካ ጸበል ትወስደው ካልሆነ...> ደራሲና ፖለቲከኛ አስራት አብርሃም በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ካደረግንለት ቃለ መጠይቅ የተወሰደሙሉውን ያዳምጡት)

ሕወሃት በኣለም አቀፍ የአሸባሪነት መዝገብ ያሰፈረው የአፈና ተግባሩና ከ38 ዓመት በፊት ከታፈኑት የውጭ ሰዎች የጋዤጠኛው ምስክርነት(ልዩ ጥንቅር)

የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ (ልዩ ዘገባ)

ሌሎችም አሉ

ዜናዎቻችን

የአቶ አንዳርጋቸው ባለቤት በእንግሊዝ የስለላ ድርጅት ላይ ቅሬታቸውን ገለጹ

የህወሃት ካድሬዎች የህወሃት ባንዲራ ለተቃውሞ ሲቃጠል የትግራይ ባንዲራ ተቃጠለ ማለታቸው ተቀባይነት እንደሌለው ተገለጸ

ሰማያዊ ፓርቲ መሪዎቹ በአገዛዙ የእስር ሰለባ ቢሆኑ በተተኪ አመራር ጉዳይ እየመከረ ነው

የኦጋዴን ነጻ አውጭ የአገዛዙን ወታደራዊ አሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታወቀ

ሙስሊሙ ማህበረሰብ በስልጣን ላይ ባለው አገዛዝ የደረሰበትን የመብት ረገጣ እንዳይዘነጋ ተጠየቀ

የኢህአዴግ አገዛዝ አገሪቱን ወደ ፍጹም አምባገነን አገዛዝ እየመራት ነው ተባለ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

የዶ/ር ነገደ ጎበዜ አዲስ መጽሐፍ

$
0
0

dr_negede_two“…ይህንን የትግሉን ህዝባዊ ገፅታ ችላ ብለን እነዚህን ሚሊዮኖች የሚያካትት ህዝባዊ የትግል ማእበል ለመቀስቀስ፣ መቀስቀስ ብቻ ሳይሆን ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ የሚያስችለን የጋራ ስትራቴጂ አውጥተን ካልተንቀሳቀስን በስተቀር “በእኛና  በእነሱ” መሃከል በተወሰነ የትግል ክፈፍ ከብረት ድስትና ከሸክላ ድስት ፍልሚያ፤ ሸክላ በአሸናፊነት ይወጣል በሚል የአጉል  ህልም ዓለም ውስጥ ነን ማለት ይሆናል፡፡” ዶ/ር ነገደ ጎበዜ-  [ሙሉውንለማንበብእዚህይጫኑ]—-

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጲያውያን እኔም እንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ በሚል ታላቅ ሕዝባዊ ውይይት አደረጉ

$
0
0
Pቅዳሜ ጁለይ 12/2014 በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አዘጋጅነት ሁላችንም እንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን በሚል አላማ በኖርዌ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የደንነት ሀይሎች መታፈንና ለአምባገነኑ የወያኔ መንግስት ታላልፈው መሰጠታቸውን በተመለከተ ወደ ፊት ምን ማድረግ እንዳለባቸው ከተለያዩ ከተሞች በመሰባሰብ በኖርዌ ኦስሎ ለአምስት ሰዓታት የፈጀ ውይይት ሲያደርጉ ውለዋል::
ሕዝባዊ ውይይቱ ከቀኑ 15: 00 ሰአት ላይ የተጀመረ ሲሆን ቁጥራቸው በርከት ያሉ ኢትዮጵያኖች የአቶ እንዳርጋቸው ምስል ያለበትና ሁላችንም እንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን የሚል ጹሁፍ የተጻፉበትን ቲሸርት በመልበስ ለስብሰባው ድምቀት የሰጡት ሲሆን ለአቶ አንዳርጋቸው ያላቸውንም የትግል አጋርነት አስማስክራዋል እነዚህን ቲሸርቶች የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ የበርገን ቅርንጫፍ በራሳቸው አነሳሽነት የሰሩ ሲሆን የድጋፍ ድርጅታችን ወጪውን በመሸፈን ለተሰብሳቢው በነጻ ኣድሏል።
ስብሰባውን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ሕዝብ ግንኙነት አላፊ አቶ አቢ አማራ በሃያ ሶስት አመታት በወያኔ ጨካኝ አገዛዝ በግፍ ለተገደሉትና በግፍ ለሚሰቃይዩ ወገኖቻችን የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማስደረግ አስጀምረውታል በመቀጠልም አቶ ዮሀንስ አለሙ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ ሊቀመንበር በስብሰባው ላይ የተገኛውን ሕዝብ እንኮን ደህና መጣችሁ በማለትና በማመስገን ፐሮግራሙን በንግግር የከፈቱት ሲሆን አቶ ዮሀንስ በንግግራቸው የወያኔ መንግስት በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ባደረሰው አፈና ግንቦት 7 የክተት አዋጅ ማስተላለፉን ጠቅሰው አንባገነኑ የወያኔ መንግስት በአሁን ሰአት በሀገር ቤት በሰላማዊ ትግል እየታገሉ ባሉ ታጋዮች ላይ ሳይቀር እስር እያደረሰባቸው እንዳለ በማመልከት ሰሞንኑን እንኮን የሰመያዊ፣ የአንድነት፣ የአራና የፖለቲካ ድርጅት ከፍተኛ አመራሮች ለስር ተዳርገዋል ብለዋል::
ስለሆነም ህዝባችንን ለእስር እያደረገ ያለውን አገዛዝ ለመቃወም ሁሉም በአንድነት መሰባሰብ እንዳለበት አጠንክረው በመናገር በአሁን ሰአት የአቶ አንዳርጋቸው በወያኔ መታፈንና መታሰር መላውን ኢትዮጵያ ዳር እስከ ዳር እያንቀሳቀሰውና ሕዝቡም እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ በማለት በስፋት እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ ጠቅሰው በአሁን ሰአት ትግሉ የግንቦት 7 ብቻ አይደለም ይህን ትግል በዚሁ አንድ ሆነን መቀጠል እለብን ብለዋል::
በመቀጠል አቶ ደባስ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አባል የአቶ አንዳርጋቸውን ከወጣት እድሜያቸው ጀምሮ ያለውን የፖለቲካ አካሄድ አቶ እንዳርጋቸው ጽጌ ማን ነው ? በሚል ርእስ የአቶ አንዳርጋቸውን የትግል ጉዞ የሚዳስስ ዘገባ ሰፋ ባለ ትንታኔ በጹሁፍ ያቀረቡ ሲሆን በስብሰባው ላይ የኢሀፓ ፣ የአርበኞች ግንባር፣ የሸንጎ ፣የስደተኛው ማህበር ተወካዮች እና ሌሎችም ሰዎች በየተራ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የየድርጅቷቹም ተወካዮች የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በወያኔ መታፈንና ለእስር መዳረግን በተመለከተ የድርጅታቸውን አቋም ለተሰብሳቤው ያስረዱ ሲሆን የሁሉም ፖርቲ ተወካይች በአቶ አንዳርጋቸው መታፈንና ለእስር መደረግ ማዘናቸውን ገልጸው ሁሉም በአንድነት በመተባበር በማንኛውም የትግል እንቅስቃሴ የወያኔንን መንግስት ማስወገድ እንዳለባቸው አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል::
በየፕሮግራሞቹ መሀል ግጥሞችና ሌሏችም ፕሮግራሞች ቀርበው የመጀመሪያው ዞር ተጠናቋል::ከ30 ደቂቃ የእረፍት የሻይ እና የቡና ፕሮግራም በኋላ የሁለተኛው ክፍለ ጊዜ ፕሮግራም በተያዘለት ጊዜ ተጀምሮ የፕሮግራሙን ተሳታፊዎች ያሰተፈ ፕሮግራም በአቶ አብዱ የሱፍ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ስታቫንገር ቅርንጫፍ ምክትል ሊቀመንበር ከግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪን ካብራሩ በኋላ ለተሰብሳቢው ለውይይት በማቅረብ በኖርዌ የምንኖር ኢትዮጵያኖች ይህን የትግል ጥሪ ለማስፈጸም ምን እናድርግ በማለት ለውይይት አቅርበው የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች በአቶ ዮሀንስ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ ሊቀመንበር አወያይ አማካኝነት በስፋት ተወያይተውበታል ::
ተሰብሳቢውም በብዙ ነገሮች ከተወያዩ በኋላ ይሄ ግንቦት 7 ያወጣውን የመጀመሪያ እንከን የትግል ጥሪ ተግባራዊ በየቦታው አለም አቀፍ ታክስ ፎርሶች እየተቋቋሙ እንዳለና በኖርዌይም ይህንኑ ጥሪ ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉንም የፖለቲካ ድርጅቷች ያካተተ ታክስ ፎርስ እንዲቋቋም ተወስኖል:: በመቀጠልም በተሰብሰቢዎች በተመረጡ ሰዎች የተጻፋ ባለ ስድስት አሃዝ የተሰብሳቢው የአቋም መግለጫ ለጉባሄው በጹሁፍ ቀረቦል:: ተሰብሳቢው ያወጣው የአቋም መግለጫ
1. ሁላችንም አንዳርጋቸው ወይም አንድ አርጊያቸው ነን ስንል ለነፃነት፣ ለእኩልነት፣ ለፍትህና ለዲሞክራሲ በሐገራችን ኢትዮጵያ ለማስፈን የሚከፈለውን መስዋእትነት ሁሉ ለመክፈል ዝግጁዎች ነን ማለታችን ነው።
2. የተለያዩ የፖለቲካና ሲቪክ ማህበራት የሚያደርጉትን መጠላለፍ እንዲቀርና በጋራ ወይም አንድ በመሆን እንዲሰሩ ግፊት እናደርጋለን።
3. ለሚቀርብልን ሐገርን የማዳን ጥሪ ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን።
4. የየመን መንግስት ከአለም አቀፍ ህግ ጋራ የሚፃረር ስራ በመስራት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ለወያኔ አሳልፎ በመስጠት የሰራውን ወንጀል ለዓለም አቀፍ ህግ የማቅረብ ስራ በጋራ እንደምንሰራ።
5. የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በወያኔ መታፈን ትግሉን የበለጠ እንደሚያጠናክረውና ወደ ውጤት እንዲያመራ የበኩላችንን አስተዋፅኦ እናደርጋለን።
6. ወያኔ የተለያየ ምክንያት በመፍጠር ኢትዮጵያውያንን እስርቤት ማስገባቱን እንዲቀርና የታሰሩትን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ እንጠይቃለን በማለት የአቋም መግለጫ አውጥተዋል ።

በመጨረሻም አቶ ዳንሄል አበበ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ምክትል ሰብሳቢ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ የአቋም መግለጫ ለተሰብሳቢው በጹሁፍ ያሰሙ ሲሆን በንግግራቸውም አቶ እንዳርጋቸው ጽጌ ለኢትዮጵያ አንድነትና ነጻነት የቋሙ የነጻነት ታጋይ ናቸው እኔም እንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ የምንል ሁሉ ለሃያ ሶስት አመታት ህዝብን በዘረኝነት የከፋፈለውን ወያኔን በቃ ልንለው ይገባል ካሉ በኋላ በኢትዮጵያ ከመቸውም ጊዜ በላይ አፈና፣ ግድያው፣ እስራቱ መጨመሩን በመናገር ይኼን ጨቋኝና አፋኝ ስርአት ለማስወገድ እንነሳ በማለት ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን በመጨረሻ እኔ እንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ እናንተስ በማለት የፕሮግራሙን ተሳታፊ በመጠየቅ ፕሮግራሙ በተያዘለት ሰዓት ከምሽቱ 20:00 ተጠናቋል ::

እኛ ሁላችንም እንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን!!!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ

እየነጋ ነው! (እስከመቼ)

$
0
0

እስከመቼ

ሐምሌ ፪ ቀን፤ ፳፻፯ ዓመተ ምህረት 7/9/2014
eske.meche@yahoo.com )

Abrha-Desta-Yeshiwas-Assefa-Daneil-Shibeshi-Habtamu-Ayalewአሁን ደግሞ ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳንዔል ሺበሽ፣ አብረሃ ደስታን አሰሩ። አንዳርጋቸው ፅጌን የማሠራቸው ዜና ገና አቦሉ ሳይጠጣ እኒህን ደገሙ። ለምን? አጭሩ መልስ እየነጋ ስለሆነ ነው። ኢትዮጵያዊ ሆኖ የእኒህን ታጋዮች ማንነትና ተግባር የማያውቅ የለም፤ ቢያንስ በትግሉ ዙሪያ ያለነው ኢትዮጵያዊያን። ታዲያ መንጋቱ እኮ፤ የአውራ ደሮውን ጩኸት፣ የጎኅን መፈንጠቅ፣ የጨለማውን መገፈፍ ይጠይቃል። ይህ ደግሞ በገዛ ፈቃዱና ቁጭ ብለው ስለጠበቁት የሚሆን አይደለም። የመሬትን በፀሐይ ዙሪያ መሽከርከር ተፈጥሯዊ ግዴታ ተከታይ ነው። በጭቆና የሚማቅቅ ሕዝብ፤ ለነፃነቱ መነሳቱና ከመካከሉ ቆራጦቹ ጧፍ ሆነው ከፊት መቅለጣቸው ግዴታ ነው። ይህ ነው የኒህ ቆራጥ ታጋዮች ሕይወት ትርጉሙ። እንደኛው ቤተሰብ፣ ንብረትና ምቾት አልጠሉም። ለወገንና ለሀገር ሠጡት። የሕይወታቸውን ትርጉም፤ በጣሊያን ጊዜ ከፋሽስቶች ለመጋፈጥ ከየመንደሩ በባዶ እግራቸው፤ ከመላ ኢትዮጵያ ጫፍ እስከጫፍ ወጥተው እንደቀሩት አርበኞቻችን፤ የኔ ሕይወት ለነገዋ ኢትዮጵያ ሕልውና ይሁን ብለው ያለማመንታት፤ ፀረ-ኢትዮጵያ የሆነውን ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራውን መንግሥት በመቃወማቸው እስር ቤት ገቡ። ከኛ የተለዩ ልዩ ፍጡር ሆነው አይደለም። እንደኛ አባትና እናት፣ እህትና ወንድም፣ አክስትና አጎት፣ ባለቤትና ልጆች ያሏቸው ናቸው። ሰው ናቸው። አርበኛ ያደረጋቸው ተፈጥሯዊ ልዩነታቸው ሳይሆን፤ ለሕይወታቸው የሠጡት ትርጉም ነው። የብዙኀኑን የኢትዮጵያዊያን ሕይወት የኔ ብለው፣ ስቃያቸውን እነሱ ተሸክመው፣ ለሕዝቡ ጭዳ ሆነው ተሰለፉ። እንደነ አንዱዓለም አራጌ፣ እስክንደር ነጋ፣ ርዕዩት ዓለሙ፤ ሰግዶ ማደርን አልፈልግም ብለው፤ አረዓያችን ሆኑ። እንዲነጋ ምን ማድረግ አለብን።

አይቀሬው ንጋት እየመጣ ነው። የኛ ኃላፊነት ብዙና የተቆላለፈ አይደለም። እኒህ ቆራጦች የነገሩን ምንድን ነው? ፍርሃትን፤ ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራው መንግሥት ቀምቶናል። ከኛ በኩል ፍርሃት ቦታ የለውም። የኢትዮጵያዊያን ጠላት የሆነው ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራው መንግሥት በፍርሃት ተውጧል። ምስክርነቱ፤ ማንንም የሚፈራውንና በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነት አለው የሚለውን ግለሰብ ሁሉ እያሠረ ነው። እኒህ ጀግኖች የታሠሩት የዚህ ወይንም የዚያ ድርጅት አባል ስለሆኑ አይደለም። ከሕዝቡ ጋር ስለወገኑ ብቻ ነው። ለዚህ ፀረ-ኢትዮጵያ መንግሥት፤ ማንኛውም ከሱ ቁጥጥር ውጪ የተደራጀ ክፍል ጠላቱ ነው። እናም የዚህ ወይንም የዚያ ድርጅት አባል መሆን አይደለም የመታሰሪያ ወንጀሉ፤ ከሕዝቡ ጋር የቆመ መሆኑ ብቻ ነው። የሚያስበረግገውና የሚያንቀጠቅጠው የሕዝብ ወገን የሆነ ማንኛውም ድርጅት ነው። ታዲያ ድርጅቶች በሙሉ አንድ ዓላማ እስከያዙ ድረስ፤ ሕዝቡ አሁን ነው ትግሉ ወደፊት መሄድ ያለበት እስካለ ድረስ፣ ንጋቱ በር አያንኳኳ እስከሆነ ድረስ፤ ተልዕኳችንን አንድ አድርገን ሌቱን እናንጋው።

ምንድን ነው የአሁን ጥያቄ? ይፈቱልን ብሎ ልመና አይደለም። ይህ በታሠሩት ቆራጦች ዓይን ጥቃት ነው። ይህን ብናደርግ ለገዥው ቡድን ኩራት ነው። እንኳን ያሠራቸውን ሊፈታ፤ የሚቀጥሉትን ታሳሪዎች እያዘጋጀ ነው። እነሱም ሆኑ መታሠራቸው፤ ጧፍ ሆኖ መንገዱን መሪያችን እንጂ፤ የመንገዱ ማብቂያ አይደለም። ገና የራሱን ጥላ ለማሠር የሚሯሯጥ ጠላት ነው ያለን። አጥንት ቆጠራውን ለገዥው ክፍል እንተውለት። እሱም እንኳ ለአጥንት ቆጠራው ቦታ እንደማይሠጠው አብርሃ ደስታን በማሠር አሳይቶናል። አብርሃ ደስታ በትግራይነቱ፣ ትግሬዎች እየተጠቁ ነው ብሎ የተደራጀ ነበር። አልሆነም። ኢትዮጵያዊነታችንን እንጎናጸፈው። በኢትዮጵያዊነታችን ይኼን ፀረ-ኢትዮጵያ መንግሥት እንታገለው። ሁላችንን ሊያስተባብሩን የሚችሉ አራት የትግል ዕሴቶች አሉን።

፩ኛ፤     የኢትዮጵያዊያን ሉዓላዊነት                                    ፪ኛ፤     የኢትዮጵያ ሀገራዊ አንድነት
፫ኛ፤     የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲያዊ መብቶች        ፬ኛ፤     በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት

እኒህ ናቸው የታጋዮችን አንድነት የሚጠይቁ የትግል ዕሴቶቻችን። በነዚህ ዙሪያ ሁላችን መጠማጠም አለብን። የየድርጅቶች ታሣሪዎች መሆናችንን ለነፃነቱ ጊዜ እንተወውና፤ ለኢትዮጵያዊያን በሙሉ፣ ለሀገራችን አንድነት፣ በየእስር ቤቱ ለሚማቅቁ ጀግኖቻችንና አሁን በየዕለቱ ለሚታገቱት ቆራጥ ኢትዮጵያዊያን አርበኞቻችን አንድነታችንን እናጠንክር። ይህ ወደ ድል ይወስደናል። እነዚህን ሁሉን አቀፍ የሆኑ አራት ነጥቦች በሚያኩ ዙሪያ ሀገራዊ አጣዳፊ ጥሪዎች ሰሞኑን ድረገፆቻችንን አሙቀውታል። ጥሪዎቻችሁ ወደ መሰባሰቡ እንዲያመራ ፈልጋችኋል በማለት፤ ጥሪዎችን በተደጋጋሚ ያደረጋችሁ ግለሰቦች፤ እኛው ጀማሪዎች እንሁን የሚል ጥሪ በማስቀደም እንድንገናኝ ይኼው በ ( eske.meche@yahoo.com ) እገኛለሁ።

ሰኔ 25 / 2006 ዓ/ም ታትሞ በወጣው ኢትዮምህዳር ጋዜጣ ከዓረና ሊቀመንበር አቶ ብርሃኑ በርሀ የተደረገ ቃለ መጠይቕ

$
0
0
Berhanu-Berhe-Arena-second-Chair-Person-of-Arena-Tigray

Berhanu-Berhe-Arena-second-Chair-Person-of-Arena-Tigray

ዓረና የምርጫ መቀስቀሻ አጀንዳዎቹ መሰረቱና መነሻው የመድረክ ማኒፌስቶ ነው የሚሆነው ፡፡የመድረክ ሚኒፌስቱ የታወቁ  ናቸው ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ሊታዩ የሚገባቸው ካሉ በመድረክ የሚወሰኑ ስለሚሆኑ ያኔ የሚገለፁ ናቸው የሚሆኑት ፡፡ በዓረና  ደረጃ ከክልሉ አጠቃላይ ሁኔታ ግምት ውስጥ የሚገቡ ጉዳዮች ካሉም በቅርቡ በሚሰበሰብ ማእከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ  የሚወሰኑ ናቸው፡፡ ዞሮ ዞሮ በፖለቲካ ነፃነትና በመንግስት ፖለቲካዊ ኢ ወገናዊነት ፣በነፃ ምርጫና በሕብረ ፓርቲ ስርዓት ችግሮች፣  በመሬት ይዞታ ጉዳይ፣በኢንበስትመንትና በቡዝነስ ዙርያ ፣ በኢኮኖሚ ፖሊሲውና ብድህነት ቅነሳ፣ በአሰተዳደር ብልሹነት ጉዳዮች  የሚያጠነጥን ሳይሆን አይቀርም ፡፡ -— [ሙሉውንለማንበብእዚህይጫኑ]——

የግለሰብ ነፃነት ሲገፈፍና መብቱ ሲረገጥ በለሆሳስና በዝምታ ማለፍ ውጤቱ ሽንፈት ይሆናል፦

$
0
0

ዘረኛው የወያኔ ቡድን የሥልጣን ርካቡን በጠመንጃ ኃይል ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ስለደረሰው ግፍ፤ሥቃይና መከራ እንዲሁም አገሪቱን በቋንቋና በጐሣ ሸንሽኖ ህልውናዋን እየተፈታተነ ለመሆኑ በልዩ ልዩ አጋጣሚዎች በተደጋጋሚ ተገልጿል።

የዚህን ጠባብ ብሄረተኛ ቡድን እኩይ ተግባር በቡድንም ሆነ በተናጠል በብዕራቸው የተዋጉ፤በድርጅት ዙሪያም ተሰባስበው ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ትግል ያካሄዱ ኢትዮጵያውያን በነቂስ እየተለቀሙ ለእሥር ተዳርገዋል።ከፊሉንም ቤት ይቁጠረውና የደረሱበት ሳይታወቅ እንደወጡ ቀርተዋል።

ሰሞኑንም ይህ መንግሥት ነኝ ባይ ጠባብ ብሄረተኛ ቡድን ከየመን መንግሥት ጋር በመመሳጠር ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብትን ድንጋጌ ጥሶ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የግንቦት ሰባት የፍትህ፤የነጻነትና የዴሞክራሲያው ንቅናቄ መስራች አባልና የንቅናቄውን ዋና ጸሐፊ በማገት ጠልፎ እንደ አንድ ነጻ ዜጋ በየትኛውም አገር የመዘዋወር መብታቸውን ረግጦ በማፈን ወደ ኢትዮጵያ ውስዶ እያሰቃያቸው ይገኛል።

መብቴ ተረገጠ፤ ነፃነቴ ተደፈረ፤በሀገሬ ጉዳይ የመናገር፤የመጻፍና የመደራጀት ዜግነታዊ ሕልውናየ ተጣሰ…ወዘተ ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከምን ጊዜውም በላይ ይህ የሰሞኑ በወንድማችን ላይ የተፈፀመው ድርጊት አስቸኳይ መልስ የሚጠይቅ ፈተና ከፊቱ ተደቅኖ ይገኛ

ል።ይህን ፈተና ለመጋፈጥ የማይሻ ሁሉ የዘረኛውና የጠባብ ብሄረተኛው የወያኔ መንግሥት ጋሻ ጃግሬ ወይንም ከዚህ ወንበዴ ቡድን ተጠቃሚ የሆነ ብቻ ነው።

በሁለተኛው የዓለም ጦርነት መባቻ ላይ የሂትለርን አገዛዝ አጥብቆ የሚያወግዝ ማርቲን ኒሞለር የተባለ ጀርመናዊ የፕሮቴስታንት ቄስ በወቅቱ ሰፍኖ የነበረውንና ናዚስቶች ደረጃ በደረጃ ይፈጽሙ የነበረውን ግፍና መከራ አስመልክቶ የተናገረውን ያስታውሷል፦ይኸውም

“የናዚ አገዛዝ በመጀመሪያ በሶሻሊስቶች ላይ ሲዘምት ምንም አልተናገርኩ ምክንያቱም እኔ ሶሻሊስት ስለአልነበርኩ ።ቀጥለውም በትሬድ ዩኒየን ላይ የግፍ በትራቸውን ሲሰነዝሩ አልተናገርኩም።ምክንያቱም እኔ ትሬድ ዩኒየኒስት አልነበርኩምና። ከዚያም በኋላ በይሁዶች ሲነሱ ዝም አልኩ ምክንያቱም እኔ ይሁዲ አልነበርኩምና።በመጨረሻም ወደ እኔ መጡ ሆኖም ግን ስለ እኔ የሚናገር የቀረ ማንም አልነበረም።”

አሁንም ይህ በአንድ ታጋይ ኢትዮጵያዊ ላይ የተፈጸመውን ዘግናኝ ድርጊት መግለጫ በማውጣት ፤ሰልፍ በመሰለፍ ብቻ ልንወጣው አይቻለንም።በመሆኑም እኛ በኮሎምቦስ ኦሀዮ የምንገኝ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰው በደል በዝምታና በለሆሳስ ልናስተናግደው በጭራሽ አይቻለንም።ይህ ዓይነት መረን የለቀቀ ግፍ ተራ በተራ በእያንዳንዱ የተቃዋሚ ድርጅት መሪዎችና የዴሞክራሲ ጠበቃዎች ላይ ከመድረሱ በፊት በድርጅት መጠናከርንና በመረጃ ልውውጥ ውጤታማ ሆኖ መገኘት አስፈላጊ እንደሆነ የወቅቱ አጠቃላይ ሁኔታ ስለሚያሳይ ለእውነተኛ የኢትዮጵያ ልጆች የሚከተለውን ጥሪ አቅርበናል።

vየየመን መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ የፈጸመችው አሳልፎ የመስጠት ክህደትን ማጋለጥ። የእንግሊዝ መንግሥት የዜጋዋን መብት ለመታደግ በመጀመሪያው ረድፍ መገኘት ስላለባት የሚፈለገውን ሁሉ ስልት በመጠቀም ለጉዳዩ ትኩረት እንድትሰጥበትጫና ማድረግ።

 

vበውጭ አገር የሚገኘው ኢትዮጵያዊ በያለበትና በሚገኝበት ሥፍራ የተገኘውን አጋጣሚ ሁሉ ተጠቅሞ ለተወካዮች ምክር ቤትና ለሴነተሮች ለማሳወቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ።አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የእንግሊዝ ዜጋ መሆናቸው እየታወቀ የየመን መንግሥት ዓለም አቀፉን የሰብዓዊ መብት ሕግጋትን ፤ የኮመን ዌልዝ ኔሽንን ፓክት ጥሶ ለዘረኛው መንግሥት አስልፎ የሰጠበትን ምክንያት አጥጋቢ ምላሽ ከሁለቱም መንግሥታት እንዲሰጥ አበክረን እንጠይቃለን።

 

vየወያኔ የዜና አውታሮች የሚያሰራጩትን ነጭ ወሬ የሚያስተጋቡ ግለሰቦች እንዳሉ ይታወቃል። እነዚህ ግለሰቦች  በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚያሰራጩት ወሬ እርባና ቢስ ቢሆንም የአንድነት ኃይሉን የሚጎዳ በመሆኑ ከዚህ ጸረ-ሕዝብ ተግባራቸው መቆጠብ ይኖርባቸዋል። በሌላም በኩል በየአካባቢያችን የሚገኙ የዘረኛው መንግሥት ሰላዮች፤ደጋፊዎችም ሆነ ተባባሪዎች የቆሙበት ዓላማ ርካሽ ሀገርንና ወገንን የሚጎዳ በመሆኑ በመረጃ ላይ  የተደገፈ ተግባራቸውን በማረጋገጥ ከማህበራዊ ግንኙነት ማግለል በእነርሱ በኩል የሚከናወኑ ማናቸውንም ነገሮች ቦይ ኮት ማድረግ።

 

 

vየአንድነት ኃይሎ ተበታትኖ መገኘቱ ለጥቃት በር እንደከፈተ ይታመናል በመሆኑም ሁኔታው ትግላችንንም እየጎዳው የጠባብ ብሄረተኛውን የወያኔን እድሜም እያራዘመው በመገኘቱ የአንድነት ኃይል ነን ብለው የሚያምኑ የፖለቲካ ድርጅቶችም ሆኑ ንቅናቄዎች በአስቸኳይ በመገናኘት የኢትዮጵያ አንድነት የተቃዋሚ ኃይልን መመስረት ይገባቸዋል።የዚህ የኢትዮጵያ አንድነት ኃይል መመሥረት ለመንግሥታትም እንደ አማራጭ ኃይል ሆኖ ስለሚቀርብ ይህንኑ ዓላማ ገቢራዊ ለማድረግ የየድርጅቶችም ሆነ የየስብስቦቹ መሪዎች ከዚህ በፊት በባዶ ጉዳይ የሚያናቁራቸውን ሁሉንም ነገር ከበስተጀርባቸው በመተው ለአዲስ ትንሳኤና የድል ጉዞ እንዲነሱ ታፍራና ተከብራ በኖረችውና በእኛ ዘመን ለውርደት በተዳረገችው ታላቋ ሀገራችን በኢትዮጵያ ስም እንጠይቃለን።

 

vበወንድማችን ላይ የተፈፀመውን ኢ-ሰብአዊ ድርጊት በጥሞና ተመልክተን መደረግ ስለሚገባው ልዩ ልዩ የትግል እንቅስቃሴ ስልቶችን የሚነድፍ፤ የሚያጠናና በተግባር የሚተረጉምና የሚመራ ውጤታቸውንም የሚገመግም፤ ራሱን የቻለ በስደት ላይ የሚገኘውን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚያሳትፍ አንድ ለስደተኛው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ማዕከል መፍጠር እንደሚገባው እናምናለን።የዚህ ማዕከል መፈጠር በተለያየ መልክ ጸረ-ሕዝብ የሆነው ህወሃት በተቃዋሚ ኃይሎች ላይ የሚያደርሰውን በደል፤ ሰቆቃና መከራ በባለቤትነት ወስዶ መምራት ይሆናል።ይህንን ሀሳብ ግምት ውስጥ በማስገባት ዳብሮ አንድ ውጤት ላይ እንዲደርስ አበክረን እንጠይቃለን።

 

ኢትዮጵያ ለዘላዓለም ትኑር!!

 

በአሸባሪውና ጠባብ ብሄርተኛው ወያኔ ከርሰ መቃብር ላይ ህዝባዊት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ትግትነባለች!!!

 

Ethiopians in Columbus Ohio

 

Free andargachew tsige LG


የመኢአድና አንድነት ውህደት አመቻች ኮሚቴ የባንክ አካውንቱን ይፋ አደረገ

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት

የመኢአድና አንድነት ውህደት አመቻች ኮሚቴ ስራውን በቅልጥፍና እና በትጋት እየተወጣ መሆኑን ለፍኖተ ነፃነት የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በዚህም መሰረት ለጉባኤው መሳካት ይረዳ ዘንድ መላው ኢትዮጵያውያን እንዲተባበሩ ጥሪ በማድረግ የባንክ አካውንቱን ይፋ አድርጓል፡፡
የባንክ አካውንት ቁጥር UDJ A/C 47
የባንክ አካውንት ቁጥር AEUP SP 235

udJ&AEUP

ፖሊስ እነ ሐብታሙ አያሌውን ፍ/ቤት አቅርቤያለሁ አለ

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት

ፓርቲውና የታሳሪ ጠበቆች መቼ፣ እንዴትና የት እንደቀረቡ ምንም መረጃ እንሌለ አረጋግጠዋልHabtamu abrhayeshiwas daniel

 

ዛሬ ሀምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም የፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት የአራዳ ምድብ ፍ/ብሔር ችሎት ሀምሌ 6 ቀን 2006 ዓ.ም በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ኃላፊ ኮማንደር ተክላይ መብራቱ ታሳሪዎቹን ይዘው እንዲቀርቡ ቢያዝም ኃላፊው ታሳሪዎቹን ሳይዙ ቀረቡ፡፡
ችሎቱ በ3፡30 ተሰይሞ ተከሳሽ ክሱ እንደደረሳቸው ዳኛው ጠየቁ፡፡ ክሱ በንባብ ከተሰማ በኋላ የጽሑፍ ምላሽ እንዳላቸው ሲጠየቁ፣ በጽሑፍ መልስ አላመጣሁም በቃል መልስ እሰጣለሁ በማለት ምላሻቸውን ከዚህ እንደሚከተለው በቃል ሰጥተዋል፡፡


ተከሳሾቹ በሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በወጣ የመያዣ ትዕዛዝ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም እንደተያዙና ሐምሌ 2 ቀን 2006 ዓ.ም ፍ/ቤት ቀርበው ቀጠሮ እንደጠየቁባቸውና በህጉ መሰረት መብታቸው ተጠብቆ እንዳለ ገልጸው ጠበቆቹ ከደንበኞቻቸው ጋር ረቡዕ እና ዓርብ መገናኘት እንደሚችሉ የመጡበት ቀን ግን መገናኘት በማይቻልበት ቀን በመሆኑ ነው ያልተገኙት በማለት ለፍ/ቤቱ አስረድተዋል፡፡


የከሳሽ ጠበቆች አቶ ተማም አባቡልጉ እና አቶ ገበየሁ ይርዳው በበኩላቸው ይህ በቃል የተሰጠው ምላሽ በሰነድ ያልተደገፈ ማስረጃ የሌለው በመሆኑ የተከበረው ፍ/ቤት ውድቅ እንዲደረግልን እንጠይቃለን፡፡ ወደ ማዕከላዊ በመሄድ ደንበኞቻችንን ለማናገር እስረኞች አስተዳደር ብናናግርም የፀረ ሽብር ኃላፊውን አናግሩ የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን ኃላፊውን ማናገር አልቻልንም በቀጠሮ መጥተን እናናግራቸው ብንልም በቀጠሮ ሊያገናኙን ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ የኛ ጠበቃ ጓደኞች ደንበኞቻቸውን ሲያናግሩ አይተናል እኛ ደንበኞቻችንን እንዳናናግር ተደርገናል፣ አድልዎ ተደርጎብናል፡፡ ምንም እንኳ ሀገሪቷ በወታደራዊ ዕዝ ሥር ብትሆን እንኳ የእስረኞች የእኩልነት መብት አይገፈፍም፡፡ ሌላው የፀረ ሽብር ኃላፊው እንዳመኑት በሳምንት ሁለት ቀን ረቡዕና ዓርብ ብቻ ከእስረኞች ጋር መገናኘት ይችላሉ ያሉት የህግ ጥሰት ነው፣ ለምን በሥራ ቀናቶች ሁሉ መጠየቅ አለባቸው ይህ ህገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ታሳሪዎቹን ፖሊስ ይዞ እንዲቀርብ ያዘዘ ቢሆንም የፍ/ቤቱን ትዕዛዝ አክብሮ ታሳሪዎቹን አላቀረበም፡፡ በአቤቱታችን መሰረት ደንበኞቻችን ህጉ ተጠብቆ በህጉ መሰረት ያልተያዙ በመሆኑ አሁኑኑ ከእስር እንዲለቀቁልን፤ ይህ የማይሆን ከሆነ በዋስትና እንዲለቀቁልን ክቡር ፍ/ቤቱን እንጠይቃለን፡፡ የእስር ቦታቸው ተቀይሮ ወደ ተሻለ ጣቢያ ተዛውረው በጠበቃ፣ በወዳጅ ዘመዶቻቻ እንዲጎበኙ እንዲደረግ ክቡር ፍ/ቤት እንጠይቃለን፡፡ በማለት የከሳሽ ጠበቆች ለፍ/ቤቱ አስረድተዋል፡፡


በመጨረሻም ፍ/ቤቱ የመያዣ ትዕዛዝና ፍ/ቤት ያቀረቡበትን ሰነድ የማዕከላዊ የፀረ ሽብር ዲቪዚዮን ኃላፊ ተክላይ መብራህቱ ሐምሌ 10 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ በ 4፡00 ሰዓት ይዘው እንዲቀርቡ አዟል፡፡


የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ከሥራ ሰዓት ውጪ ማታና ጠዋት ታሳሪዎችን እንደሚያቀርቡ መዘገቧ ይታወሳል፡፡

 

 

የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት ተቃዋሚዎችን በማፈን የኢትዮጵያን የነጻነት ትግል አያስቆምም!

$
0
0

07/15/2014

 

ሰሞኑን ከዱባይ ወደ አስመራ በመጓዝ የነበሩትን የግንቦት 7 ድርጅት ዋና ጸሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ብትራንዚት ላይ የመን ከተማ ሰንዓ የአየር ማረፊያ እንዳሉ በየመን የጸጥታ ሀይሎች ታፍነው ለትግራይ ነጻ አውጭ ግንብር (ወያኔ) ተላልፈው እንደተሰጡና አሳዛኝና ከስብእና ውጭ ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው እንደሆ እየሰማን ሰንብተናል። በየመን መንግስት ተባባሪነት፣ በትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የተፈጸመባቸውና  እየተፈጸመባቸው ባለው ግፍ፣ ድብደባና ሲቃይ ልሳን ግፉዓን አጥብቆ ያወግዛል። ለመሆኑም በውጭ ሀገር ታፍኖ መወሰድ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም እንዳልሆኑ ለሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊን በሙሉ ማስታወስ እንወዳለን።  የትግራይ  ነጻ አውጭ ድርጅት የትግራይን  የመስፋፋትና ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዓላማ እንቅፋት ይሆኑኛል የሚላቸውን በሱዳን በስደት ላይ የነበሩትን ያሉትን  የወልቃይት የጠገዴንና የአርማጭሆ አርበኞች፣ ድንበር ጠባቂዎች ከሱዳን የጸጥታ ሀይል ጋር በመተባበር  በ1981 ዓ/ም ህዳር 5 ጀምሮ እስከ አሁኗ ደቂቃ ድረስ እየታፈኑ ተወስደው ጠፍተዋል፡፡ለምሳሌ ያህል

1. ሻለቃ ጌታቸው ይርጋ

2. ሻለቃ አጣናው ዋሴ (80 አመት አዛውንት በ2009 … ማእከላይ እስር ቤት በደረሰባቸው ጉዳት አረፉ)

3. አቶ ናሩ ገብረህይወት      4. አቶ መከታው አዛናው

5. አቶ አበጀ ፈለቀ            6. አቶ መላኩ ንጉሴ

7. አቶ ዘውዱ አልጣህ        8. አቶ ፈንቴ ገብሬ

9. አቶ ሀጎስ ጌታሁን          10. አቶ አስራደ በየነ ….ይቀጥላል

ሰሞኑንም ለሱዳን የጸጥታ ሀይሎችታስረው(ታፍነው) ለትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት እንዲሰጡ የሚፈለጉ ሰዎች ስም ዝርዝር የተሰጠ እንዳለ ማስረጃ ደርሶናል። ይህንን ህገ ወጥ ተግባርም አበክረን እናወግዛለን፡ እንቃወምም አለን።

ወድ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፤

የኢትዮጵያ ህዝብ ግፍና በደል ጽዋው ሞልቶ እየፈሰሰ ነው። ሀገር ውስጥ መኖር አልተቻለም፤ ውጭም በተለይ በኢትዮጵያ አጎራባች አገሮች ውስጥ በስደት ለመኖር አስቸጋሪ የሆነብት አጣብቂኝ ውስጥ ደርሰናል። ሀገርና መደበቂያ ያጣ ሆኖ መኖር እስከመቸ ነው? አይበቃንም!

ሀገርንና ወገንን ለማዳን አሁኑኑ በጋራና በአንድነት መነሳት የግድ ይላል!

ልሳነ ግፉዓን

voice of victims

በሃገሪቱ ሰሜናዊ እና ስሜን ምስራቅ ድንበር ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል

$
0
0

በሃገሪቱ ሰሜናዊ እና ስሜን ምስራቅ ድንበር ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል። #Ethiopia  የወያኔ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና ከባድ መሳሪያዎች ተወልውለው በድንበሩ ዙሪያ ተኮልኩለዋል።

የአንዳርጋቸው ጽጌ መያዝ ፡ የግንቦት ሰባት ጥሪ እና የትሕዴን ሰራዊት መመረቅን ትከትሎ በሃገሪቱ ሰሜናዊ እና ሰሜን ምስራቅ ድንበር ላይ ከፍተኛ ውጥረት መንገሱን ለሰሜን እዝ ቅርብ የሆኑ የሰራዊቱ ምንጮቻችን በደረሱን መረጃ አስታውቀዋል።እንዲሁም በአፋር ክልል ውስጥ ክፍተኛ ደህንነቶች በማፍሰስ ሕዝቡን እየሰለሉት መሆኑ ሲታወቅ ከፍተኛ አመጽ በክልሉ እንዳይነሳ ወያኔ መስጋቱ ታውቋል።

newsወያኔ ተጠባባቂ ጦሩ ላይ እምነት ስለሌለው የትግራይ ተወላጅ የሆኑትን ብቻ በተለያዩ ወረዳዎች በመሰብሰብ አስፈላጊውን መመሪያ የሰጠ ሲሆን በሁምራ ክዚህ በፊት ሰልጥነው የሰፈሩ እና መኖሪያቸውን እዛው ያደረጉ የወያኔ ልዩ ተጠባባቂ ጦር አባላት በነፍስ ወከፍ አዳዲስ ላውንቸር ክላሽንኮቭ እና ከበርካታ ጥይቶች ጋር እንደትድላቸው ታውቋል። እንዲሁም በትግራይ ውስጥ የሰለጠኑ ሚሊሻዎች ከነትጥቃቸው ድንበር አከባቢ ከዚህ ቀደም መሬት ተሰቷቸው የሰፈሩትም ለዚሁ ግዳጅ እንዲዘጋጁ ተደርገዋል።ታንኮች መድፎች እና ከባባድ መሳሪያዎች ወደ ድንበሩ በመጠጋት አስፈላጊውን አሰሳ እያደረጉ ሲሆን የ24 ሰአት ልዩ ጥንቃቄ የተሞላበት ወታደራዊ የቁጥጥር ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ምንጮቹ ጠቁመዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዲስ መልክ በጎንደር በጎጃም እና በሰሜን ሸዋ ነዋሪዎችን መሳሪያ ማስፈታት ሊጀመር መሆኑ የታወቀ ሲሆን ይህም የሚያምለክተው አማራው ከግንቦት ሰባት ጋር ይሸፍታል የሚል ስጋት ስላላቸው መሆኑ ታውቋል። በዚህ ዙሪያ ተከታታይ መረጃዎችን ይቀርባሉ።

 

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ካፒቴን ተሾመ ተንኮሉ በአቶ አንዳርጋቸው እገታ ዙሪያ ተናገሩ

$
0
0

ከከፍተኛ አሰልጣኝና አብራሪ ካፖቴን ተሾመ ተንኮሉ ጋር በተለይ ከአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጠለፋና ሊደርስባቸው ከሚችል ስቃይ ጋር በተያያዘ የተደረገ ቆይታ ከመለከት ራድዮ ቫንኮበር ጋር።

ካፒቴን ተሾመ ተንኮሉ በአቶ አንዳርጋቸው እገታ ዙሪያ ተናገሩ

ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና ከአንድንት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

$
0
0

የውህደት እንቅስቃሴአችን በተሳካ ሁኔታ ቀጥሏል!!

ለውህደቱ መሳካት ጥረት እና ድጋፍ እያደረጉ ላሉ ኢትዮጵያውያን  ምስጋና እናቀርባለን

እንደሚታወቀው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የቅድመ ውህደት ስምምነት ፊርማ ካኖሩ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት ውህደቱን ምሉዕ ለማድረግ የጋራ ኮሚቴ በማቋቋም እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡

ይሄው ውህደት አመቻች ኮሚቴ በስምምነት ሰነዱ በተቀመጠው መሰረት ለማጠናቀቅ ቀን ከሌሊት እየሰራ ሲሆን የሁለቱ አንጋፋ ፓርቲዎች ውህደት የተሳካ እንዲሆን ትንሽ ግዜ መጨመር አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል፡፡ በተለይም ለውህደቱ መሳካት የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን ሰፊ በመሆኑ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ደጋፊዎቻችን የአቅማቸውን ድጋፍ ለማድረግ በስምምነት ሰነዱ የተቀመጠው የውህደት ግዜ ላይ ሁለት ሳምንት መጨመር እንደሚያስፈልግ ታምኖበታል፡፡

ስለዚህ ጉባኤ ጠሪ ኮሚቴው ባደረገው ግምገማ የሁለቱ ፓርቲዎች የውህደት ግዜ ሓምሌ 19 እና 20 እንዲሆን ተስማምቷል፡፡ ከዚህ ውጭ ግን የሁለቱ ፓርቲዎች ረቂቅ ደምብና ፕሮግራም ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቀቀ ሲሆን የጉባኤ ተሳታፊዎች የውህደቱን ግዜ በጉጉት እየጠበቁ ይገኛሉ፡፡ በመጨረሻም ሁለቱ ፓርቲዎች ተዋህደውና ሌሎች ፓቲዎች ወደ መሰባሰብ መጥተው የተጠናከረ የተቃውሞ ሃይል እንዲፈጠር ብርቱ ድጋፍ ላደረጉ ኢትዮጵያውያንና የውህደት አመቻች ኮሚቴው ስራ የተቀላጠፈ እንዲሆን ድጋፍ እያደረጉ ላሉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርባለን፡፡

በመቀጠልም እስከ ውህደቱ ፍፃሜ ድረስ በሀገር ውስጥና በውጭ አገር እየተደረገ ያለው ድጋፍ እንደሚቀጥል በመተማመን ለውህደቱ ድጋፍ የምታደርጉ ኢትዮጵያውያን፡-

üመኢአድ፤ አቢሲንያ ባንክ፤ ቦሌ ቅርንጫፍ፤  የባንክአካውንትቁጥር፡- AEUP – SP 235 

ü  አንድነት፤ አቢሲንያ ባንክ፤ ጠመንጃያዥቅርንጫፍ የባንክአካውንት፡-  UDJ –  A/C 47

በኩል እንድታስገቡ የውህደት አመቻች ኮሚቴው አገራዊ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ስንተባባር እናሸንፈላን!!

                                     ሐምሌ 9 ቀን 2006 ዓ.ም

                                             አዲስ አበባ

udJ&AEUP

በሃረማያ ዩኒቨርሲቲ ዓመፅ ተጀመረ…!!!

$
0
0

mqdefaultየሃረማያ ዩኒቨርሲት የድህረ ምረቃ ተማሪዎች የመመረቅያ ፅሑፍ ክፍያ ከዕጥፍ በላይ በመጨመሩ ዓመፅ ኣስነስተዋል።

ተማሪዎቹ ከትናንት በስትያ ሰኞ ሓምሌ 7 /2006 ዓ/ ም ክፍያው 3000ብር እንደሆነ ከዩኒቨርስቲው ሬጅስትራር የተፃፈ ደብዳቤ የተሰጣቸው ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው ሃሳቡ በመቀየር ክፍያው ወደ 8700 ብር ከፍ በማድረግ በቦርድ ለጥፎዋል።

ተማሪዎቹ ተሰባስበው ወደ ዩኒቨርሲቲው ሃላፊዎች የሄዱ ሲሆኑ ክፍያው ከዕጥፍ በላይ እንዲሆን የተደረገበት ወሳኔ ኣግባብነት እንደሌለውና ወደ ቀድመው መጠን ካልተስተካከለ እንደማይመዘገቡ ኣሳውቀዋል።

እንደምጫችን ኣገላለፅ ከሆነ ክፍያው ባንዴ ከእጥፍ በላይ እንዲሆን የትደረገው የመንግስት ሰራተኞች ደምወዝ ጭማሪ ተደርገዋል የሚል እንደሆነ ኣረጋግጠዋ።

የሁኒቨርስቲ ኣስተዳደር በጉዳዩ ኣስቸኳይ ስብሰባ እያካሄደ እንደሆነም ለማወቅ ተችለዋል።

ሃረማያ ዩኒቨርስቲ ልማታዊ መንግስታችን ስግብግብ ዩኒቨርሲት ብሎ ታፔላ እንደሚለጥፍለት ይጠበቃል።

“ስግብግብ ነጋደዎች” ነው…! ያለው በኢቲቪ እየተናገረ የሰማሁት ኣንዱ ቱባ ባለስልጣን።

ዓመፁ በኣግባቡ ይፈታ ይሆን? ወይስ እንደ ተለመደው መቺ ሃይል ይላካል…?

 

Source- freedom4ethiopian.wordpress


ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ የምርመራ መዝገቡ መዘጋቱ ሕገወጥ አካሄድ መሆኑ ተገለጸ

$
0
0

-‹‹አሁን ታስረው የሚገኙበት ሁኔታ ሕገወጥና አደገኛ ነው›› የተጠርጣሪዎች ጠበቃ

zone 9999በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በክስ ላይ የሚገኙት ሦስት ጋዜጠኞችና ስድስት ጦማርያን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ፖሊስ ‹‹ምርመራዬን ስለጨረስኩ መዝገቡ ይዘጋልኝ›› በማለት መዝገቡ እንዲዘጋ ማድረጉ ሕጉን ያልተከተለና አደገኛ መሆኑን ጠበቃቸው አስታወቁ፡፡

ተጠርጣሪ ጋዜጠኞች ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሳዬና ጦማሪያንና የሕግ መምህር ዘለዓለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃኔ ሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የሚቀርቡበት ዕለት ነበር፡፡ እንደወትሮው ሁሉ የተጠርጣሪዎች ቤተሰቦች፣ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ጋዜጠኞች፣ ጓደኞቻቸውና የተለያዩ የችሎት ታዳሚዎች በጠዋት ማልደው በፍርድ ቤት ግቢ የተገኙ ቢሆንም፣ እስከ ቀኑ 5፡30 ሰዓት ድረስ ፖሊስም ሆነ ተጠርጣሪዎቹ ወደ ችሎቱ አልመጡም፡፡ ከ5፡30 ሰዓት በኋላ ሌሎች ፍርድ ቤት የሚቀርቡ ተጠርጣሪዎቹና ፖሊስ ችሎት ቆይተው ሲወጡ፣ የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ አመሐ መኮንን፣ ደንበኞቻቸው ፍርድ ቤት መቅረብ አለመቅረባቸውን ለማጣራት የዕለቱን ተረኛ ዳኛ ለማነጋገር ገቡ፡፡ ጠበቃው ስለደንበኞቻቸው ፍርድ ቤቱን ሲጠይቁ፣ ፖሊስ ምርመራውን መጨረሱን በማሳወቅ መዝገቡ እንዲዘጋለት ጠይቆ መዘጋቱን ሲያስረዳቸው፣ ‹‹እንዴትና በምን ሁኔታ?›› የሚል ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ከመዘጋቱ ውጪ ምንም ምላሽ ሊያገኙ አለመቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

እስረኛ ፍርድ ቤት ሳይቀርብ የምርመራ መዝገቡ ሊዘጋ እንደማይችል የሚናገሩት ጠበቃ አመሐ፣ ተጠርጣሪዎቹ ከሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ በእስር ላይ መሆናቸው፣ በሕግ አግባብ በፍርድ ቤት ምንም ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ በመሆኑ ድርጊቱ ሕገወጥና አደገኛ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

ፖሊስ ምርመራውን ካጠናቀቀ ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ይዞ በመቅረብ ለፍርድ ቤቱ ማስረዳትና ክስ እስከሚመሠረትባቸው ድረስ በዋስ እንዲቆዩ ወይም የሕግ ሥርዓቱ በሚፈቅደው መሠረት ስለሚቆዩበት ሁኔታ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ መስጠት እንደነበረበት አስረድተዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ባልሰጠበት ሁኔታ ተጠርጣሪዎቹ ባሁኑ ወቅት የት እንዳሉ እንደማይታወቅ የሚናገሩት ጠበቃው፣ በወንጀል ሕጉና በሕገ መንግሥቱ በተጠሰው አካልን ነፃ የማውጣት መብት (ሐቢየስ ኮርፐስ) ክስ ሊመሠርቱ እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡

በሌላ የምርመራ መዝገብ የተካተቱት ጦማሪያን ማህሌት ፋንታሁን፣ አቤል ዋበላና በፈቃዱ ኃይሉ ደግሞ ፍርድ ቤት መቅረብ የነበረባቸው ሐምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. የነበረ ቢሆንም፣ ተጠርጣሪዎቹም ሆኑ መርማሪ ፖሊስ ሳይቀርቡ መቅረታቸውን ጠበቃው ጠቁመዋል፡፡

ዘጠኙም ተጠርጣሪዎች ‹‹የመብት ተሟጋች ነን›› ከሚሉ የውጭ ኃይሎች ጋር በሙሉ ሐሳብና ገንዘብ በመስማማት ሕዝብን የማተራመስ፣ አገርንና መንግሥትን የማፍረስ ዘገባ በኢንተርኔትና በተለያዩ ድረ ገጾች ያልሆነ መረጃ ሲያስተላልፉ ተገኝተዋል በሚል ፖሊስ ሚያዝያ 17 እና 18 ቀን 2006 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር እንዳዋላቸው መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ለሁለት ጊዜ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቆ ከተፈቀደለት በኋላ፣ በሦስተኛው የፍርድ ቤት ቀጠሮ የተጠርጣሪዎቹ ጉዳይ ውስብስብና ድርጊቱም የሽብርተኝነት ድርጊት መሆኑን በመጥቀስ፣ ለተጨማሪ ምርመራ 28 ቀን እንዲፈቀድለት የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉን በመጥቀስ ተፈቅዶለት መመርመር ላይ መሆኑን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ 78 ቀናት ሞልቷቸዋል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

በአንድነት ፓርቲ ክስ የቀረበበት የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል መልስ ሰጠ

$
0
0

-ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት አቅርቤያለሁ ብሏል

‹‹ግብረ ኃይሉ ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ስለማቅረቡ ማስረጃ አላቀረበም›› የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ

UDJየተጠረጠሩበት ወንጀል ግልጽ ሳይደረግላቸው ከመታሰራቸው በተጨማሪ በሕገ መንግሥቱ ‹‹ዜጎች ተጠርጥረው በታሰሩ 48 ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለባቸው የሚገልጸውን ድንጋጌ ተላልፏል››

በሚል በአንድነት ፓርቲ ክስ የተመሠረተበት፣ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ የጋራ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይል፣ ሐምሌ 8 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርቦ ምላሽ ሰጠ፡፡

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ የፓርቲው ምክር ቤት አባል አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአረና (ትግራይ) ፓርቲ አመራር አቶ አብርሃ ደስታና የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ የሽዋስ አሰፋ፣ ግልጽ ባልሆነ ምክንያት በፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውና በ48 ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ ተገልጾ ክስ መመሥረቱ ይታወሳል፡፡ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ፍትሐ ብሔር ችሎት ሐምሌ 4 ቀን 2006 ዓ.ም. የተመሠረተበትን ክስ በሚመለከት፣ ግብረ ኃይሉ ሐምሌ 8 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ተገኝቶ ሁሉንም ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ማቅረቡን አስረድቷል፡፡

ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው ዝም ብሎ ሳይሆን ከፍርድ ቤት ማዘዥያ አውጥቶ መሆኑን የፀረ ግብረ ኃይሉ ተወካይ ፖሊስ አስረድቶ፣ የተመሠረተበት የሐቢየስ ኮርፐስ (አካልን ነፃ ማውጣት) ክስ ተገቢ አለመሆኑን ገልጿል፡፡

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ ተማም አባቡልጉ እንደተናገሩት፣ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉ ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት አቅርቤያለሁ ባለበት ቀን እስከ ምሽት 11፡30 ሰዓት ድረስ ፍርድ ቤት ግቢ ውስጥ ሲጠብቁ ቢቆዩም ሊቀርቡ አልቻሉም፡፡

የሕግ አማካሪ ሊያገኙ ሲገባ መቼና በስንት ሰዓት እንደቀረቡ ሳይታወቅ ‹‹ቀርበዋል›› መባሉ ተገቢ ባይሆንም፣ ስለመቅረባቸውም ቢሆን ፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉ ለፍርድ ቤቱ ያቀረበለት ማስረጃ እንደሌለ ተናግረዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ አንድ ሳምንት ያለፋቸው ቢሆንም፣ የሕግ አማካሪም ሆነ ቤተሰቦቻቸው እስካሁን እንዳላገኟቸው አቶ ተማም አስረድተዋል፡፡ ጠበቃ በእስር ላይ የሚገኙ ተጠርጣሪ ደንበኞቹን ማግኘት የሚችለው በሳምንት ሁለት ቀናት ብቻ እንደሆነ በማዕከላዊ እስር ቤት መወሰኑ አግባብ አለመሆኑንም አቶ ተማም ተቃውመዋል፡፡

በተፈቀደው ቀን ጠበቃ ማዕከላዊ እስር ቤት ሄዶ ደንበኛውን ሊያስጠራ ወደ ፖሊሶች ጠጋ ሲል ‹‹ማንን ነው የፈለጉት?›› የሚል ጥያቄ በፖሊሶች መቅረቡ ጥሩ ቢሆንም፣ ጠበቃው የደንበኛውን ስም ሲናገር ‹‹እሱን ለማግኘት አልተፈቀደም›› የሚል ምላሽ በመስጠት ጠበቃው ከደንበኛው ጋር ሳይገናኝ እንዲመለስ መደረጉን ተቃውመዋል፡፡

‹‹በሌላ በኩል ሌሎች ተጠርጣሪዎች ከጠበቆቻቸው ጋር ሲነጋገሩ በተመሳሳይ ቦታ ላይ ይታያሉ፡፡ ጠበቃን ማነጋገር መብት ከመሆኑ አንፃር እየለዩ አልተፈቀደምና ተፈቅዷል›› ማለቱ በሰዎች መካከል ልዩነትን ስለሚፈጥር ጥሩ አይደለም፤›› በማለትም አቶ ተማም አክለዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉ ተጠርጣሪዎቹ ፍርድ ቤት ስለመቅረባቸው ማስረጃ እንዲያቀርብ በመንገር፣ ውሳኔ ለመስጠት ለሐምሌ 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉ ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት ማቅረቡን የገለጸ ቢሆንም፣ ከአረና (ትግራይ) አመራር አብርሃ ደስታ በስተቀር የቀረበ ስለመኖሩ እንዳልሰሙና ማስረጃም አለመቅረቡን አቶ ተማም አስረድተዋል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

በደቡብ ክልል በሸካና ሸኮ ጎሳዎች ግጭት ከ130 በላይ ቤቶች መቃጠላቸው ተሰማ

$
0
0

-ቁጥራቸው ያልተገለጸ ሰዎችም መሞታቸው ተጠቁሟል

-ለግጭቱ ምክንያት ናቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎች መታሰራቸው ተሰምቷል

newsበደቡብ ክልል በሸካ ዞን ውስጥ በሚገኙት ሸካና ሸኮ ጎሳዎች መካከል በተነሳ ግጭት ከ130 በላይ ቤቶች መቃጠላቸውንና ከሁለቱም ወገኖች ነዋሪዎች ወደ ቴፒ ከተማ በመሸሽ ላይ መሆናቸው ተሰማ፡፡

በሁለቱ ጎሳዎች መካከል ግጭቱ ሊፈጠር የቻለው በጋምቤላ አዋሳኝ ድንበር አካባቢ፣ ጉስታ ቀበሌ ውስጥ በሚገኝ የማዕድን ሥፍራ ምክንያት መሆኑን የሪፖርተር ምንጮች ተናግረዋል፡፡

የሁለቱ ጎሳዎች ግጭት በ1985 ዓ.ም. የተጀመረ ሆኖ በ1994 ዓ.ም. ከረር ያለ ግጭት ውስጥ ገብተው እንደነበር ያስታወሱት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ልዩ የፖሊስ አባላትና የፌዴራል ፖሊሶች መሀል ገብተው ግጭቱን ያስቆሙት ቢሆንም፣ ውስጥ ለውስጥ መተነኳኮሱ ቀጥሎ፣ በተለይ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ የከረረ ግጭት በመጀመራቸው በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውንና የሰዎች ሕይወትም እንዳለፈ ይናገራሉ፡፡

የማዕድን ቦታውን ለማልማት ከሸካ ዞን ፈቃድ የጠየቁት ሸኮዎች ፈቃድ በመከልከላቸው፣ መዠንገር ዞን ሄደው ፈቃድ ማግኘታቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡

የሸካ ዞን የማዕድን ቦታውን ለሌላ አልሚ ሰጥቶ ስለነበር፣ ሸኮዎቹን ሲከለክሏቸው በተፈጠረ ግጭት ለኢንቨስተር የተፈቀደውን ቦታ ይጠብቅ የነበረ የጥበቃ ሠራተኛ በመገደሉ፣ ግጭቱ ተባብሶ መቀጠሉንና የሸኮ ጎሳዎች ሸካዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ እያደረጉ በመሆናቸው ንብረት እየወደመና ሕይወት እያለፈ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በጎሳዎቹ መካከል የተፈጠረውን ግጭት ለማስቆም ከተሰማሩት ልዩ ኃይሎች ውስጥ አንድ የፖሊስ ባልደረባ መገደላቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ፣ የችግሩ አሳሳቢነት የተመለከተው የክልሉ መንግሥት የፌዴራል ፖሊስ እንዲገባ በማድረጉ ግጭቱ መብረዱን አስረድተዋል፡፡ የተወሰኑ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በሥፍራው እንዲቆዩ ተደርጎ ፌዴራል ፖሊስ መመለሱንም አክለዋል፡፡ የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥትም ግጭቱን ለማብረድ መተባበሩን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡

በሁለቱ ጎሳዎች ግጭት እጃቸው አለበት የተባሉ ነጋዴዎችና ግለሰቦች ታስረው ጊዜ ቀጠሮ እየተጠየቀባቸው ፍርድ ቤት እየተመላለሱ መሆኑንም ነዋሪዎች ጠቁመዋል፡፡ በሁለቱ ጎሳዎች ግጭት ምክንያት ቤታቸው የተቃጠለባቸው በርካታ ነዋሪዎች ቀዬቸውን ለቀው ቴፒ ከተማ ተጠልለው እንደሚገኙም ነዋሪዎቹ አክለዋል፡፡ የፌዴራል መንግሥና የክልሉ መንግሥት በጋራ ጉዳዩን እልባት ካልሰጡት ወደማያባራ ግጭት ሊያመራ ስለሚችል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በሁለቱ ጎሳዎች መካከል ስለተፈጠረው ግጭት ማብራሪያ ለማግኘት ለሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በተደጋጋሚ የተደረገው ሙከራ ባይሳካም፣ የቴፒ ከተማ አስተዳደር ዓቃቤ ሕግ አቶ አሰፋ ደምሴ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ አቶ አሰፋ እንደገለጹት፣ ግጭቱ ያለው ከቴፒ ከተማ በ60 እና 70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ያኮ ቀበሌ ውስጥ ነው፡፡ ወደ ቴፒ ከተማ ሸሽተው የመጡ ነዋሪዎች መኖራቸውንና እስካሁን ድረስ በተሰባሰበው መረጃ 129 ቤቶች መቃጠላቸውን አስረድተዋል፡፡ ቦታው ሩቅና ገጠር በመሆኑ መረጃ ለማግኘት እንደማይቻል የገለጹት አቶ አሰፋ፣ ቤት የተቃጠለባቸው ነዋሪዎች በቴፒ ከተማ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በአካባቢው አንፃራዊ ሰላም መስፈኑን ጠቁመው፣ ግጭቱ አሁን ስላለበት ሁኔታ ዝርዝር መረጃ እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

ሰማያዊ ፓርቲ ‹የዜጎች ቃል ኪዳን ሰነድ›ን ለውይይት ሊያቀርብ ነው

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) አዲስ አበባ፡- ሰማያዊ ፓርቲ (ሰማያዊ) እሁድ ሰኔ 29/2006 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ የብሔራዊ ምክር ቤት ስብሰባ በኮሚቴ ውይይት ሲደረግበት የነበረውን የዜጎች የቃል ኪዳን ሰነድ ለምክር ቤቱ በማቅረብ በሰነዱ ይዘትና አፈጻጸም ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ በሚቀጥሉት ሳምንታት ውስጥ ለህዝብ ይፋ እንዲሆን ስምምነት ላይ መድረሱን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ethiopia-blue-party-300x164
ሰነዱ ለውይይት በሚበቃ መልኩና ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በሚያስማማ መልኩ በኮሚቴ ታይቶ ስምምነት የተደረሰበት መሆኑን የገለጹት የህዝብ ግንኙነቱ በቅርብ ቀን ህዝብ፣ ምሁራን፣ የህግ ባለሙያዎች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉ ተወያይተው በህገ-መሰረት እንዲጠቀሙበት እንዲያስችል እቅድ መያዙን ገልጸዋል፡፡ አቶ ዮናታን ‹‹የቃል ኪዳን መሰረቱ የተዘጋጀበት ዋናው ምክንያት ባለፉት 50ና 60 አመታት ህገ-መንግስት ተረቀቀ ቢባልም የህዝብ ሀሳብ ያልተካተተበትና የህዝብን ጥቅም መሰረት አድርገው ያልወጡ መሆናቸውን ተከትሎ ይህን ክፍተት ለመሙላት ነው፡፡›› ሲሉ የሰነዱን አላማ ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም የቃል ኪዳን ሰነዱ በርካታ አካላት የሚወያዩበት በመሆኑ የሰማያዊ ፓርቲ ብቻ እንደማይሆን የገለጹት የህዝብ ግንኙነቱ ‹‹ማንኛውም አካል ህግ ለማውጣት መሰረት እንዲያደርገው ለውይይት የምናቀርበው ሰነድ ነው ብለዋል፡፡›› ሰማያዊ ፓርቲ ስልጣን ቢይዝ ህገ-መንግስትነት ይጠቀመዋል ወይ ብለን የጠየቅናቸው ኃላፊው ‹‹የቃል ኪዳን ሰነዱን ህገ-መንግስት አናደርገውም፡፡ ነገር ግን ህገ-መንግስቱን ጨምሮ ሁሉም ህጎች ሲሻሻሉም ሆነ ሲቀየሩ የቃል ኪዳን ሰነዱ መነሻ ይሆናል›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ

”’የሽንፈት ሰላም ግን ከሽብር ይከፋል።” ማሪቱ ለገሰ ”እንድያው ዘራፈዋ!” (ያድምጧት)

Viewing all 2784 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>