(ዘሐበሻ) ጋዜጠኛ ተመስገን ያቀረበው ይግባኝ ውድቅ ተደርጎ የ3 ዓመት እስሩ እንዲፀናበት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወሰነ ። ከዚህ ፍርድ ቀደም ብሎ ወንድሞ ታሪኩ ደሳለኝ በ8 ፖሊሶች ክፉኛ ተደበደበ።
ታሪኩ ደሳለኝ በፌስቡክ ገጹ ጉዳዩን እንዲህ ገልጾታል:-
ለስምንት አንድን ሰው በደም እስኪታጠብ ድረስ በርግጫ፣ በጥፊና በሰደፍ መደብደብ፣ በእጁ ላይ የሚገኝውን ብርና መፃሀፍ መንጠቅ፣ ስልኩን መስበር…. ይህ ድርጊት በሌሊት አንድ ሰው ላይ በሌቦች የተፈፀመ ሳይሆን ትላንት ከረፋዱ በ 5 ሰዓት ላይ በዝዋይ እስር ቤት ግቢ ውስጥ በኔ ላይ የተፈፀመ ነው፤
ነገሩ እነዲህ ነው የሆነው፣ እንደልማዴ ዝዋይ የደረስኩት በማለዳ ነው፡፡ የያዝኩትን ስንቅ አስፈትሼ እንደጨረስኩ የሬዲዬ መገናኛ የያዘ መቶ አለቃ እንደሆነ የሚገልፅ ማዕረግ ያለው ወታደር እየገላመጠኝ “ለምን መጣህ?” አለኝ፤ “እዚህ የታሰረ ወንድም አለኝ እሱን ለመጠየቅ ነው” ስል መለስኩ፡፡ ቀጥ ብለህ ወጣ ተከተለ “አንተ ወንድምህን መጠየቅ አትችለም” ሲለኝ “ምክኒያቱ ይነገረኝ” ብዬ ብናገር ከጉዳይም አልቆጠረኝም “እሺ እ…ኔ ባልገባ እንኳን ያመጣሁት ምግብን አድርሱልኝ” ብል ስሚ አጣሁ፡፡ አንገቴን ደፍቼ ልወጣ ስል መቶ አለቃው በሬዲዬ እያወራ አንድቆም በእጁ ምልክት ሲሰጠኝ ልገባ ነው ብዬ ደሰ አለኝ፡፡ መቶ አለቃው በፍጥነት ወደኔ በመምጣት ያዙት አለ፡፡ በዙሬያዬ ወደ ስምንት የሚጠጉ ወታደሮች ከበቡኝ፡፡ የመቶ አለቃው “የተመስገን ታናሽ ወንድም ታሪኩ ነህ?” አለኝ፡፡ የተመስገን ወንድም መሆኔን በአንገቴም በአፌም “አዎ ነኝ” ከማለቴ ጥፊ ጆሮዬ ላይ ጮኽ፡፡ ከዛም አንደኛው በከስክስ ጫማ ሌላኛው በሰደፍ ተቀባበሉኝ፡፡ ደምቼ መሬት እስክወድቅ ድረስ ደበደቡኝ….ደበደቡኝ፤ ወደኩኝ፡፡ ከነደሜ አነሱኝ የያዝኩትን ብርና መጽሐፍ ነጠቁኝ ያመጣሁትን ምግብ መሬት ላይ ደፉተው እየገፈታተሩ ከግቢው አስወጡኝ፡፡ እስር ቤቱ ፊት ለፊት አቧራው ላይ ተቀመጥኩኝ፡፡ ተሜን በዓይን ርቀት ያህል ብቀርበውም መጠየቅ ባለመቻሌ አለቀስኩኝ፤ ደሜን አፍስሼ ወንድሜን ሳላይ ተመልሻለሁ … ተሜ ለኔ አንተን አለማየት የማይቻል ሽክም ነው፡፡ ይሄንንስ እነዴት ልንገርህ?!
የታሪኩን ድብደባ ናፍቆት እንደሚከተለው ተርካዋለች:-
በሰላም እንዳሳደርከኝ በሰላም አውለኝ” ማለት ትልቅ ነገር ነው!
ታሪኩ ደስአለኝ የጋዜጠኛ ተመስገን ታናሽ ወንድም ነው። ተመስገን ከታሰረ በኅላ ታሪኩ ሥራ በዝቶበታል። ከዲስ አበባ ዝዋይ በሳምንት 4 ግዜ እየተመላለሰ ለወንድሙ ሥንቅ ማቀበል።
ሮብ ዕለት ለወንድሙ ሥንቅ ይዞ በጠዋት ዝዋይ የደረሰው ታሪኩ፣ የወንድሙን ደህነት አይቶ ለደካማ (በዕድሜ)እናቱ ለመግለፅ እንጂ፣ ሌላ ችግር ይፈጠራል ብሎ አላሰበም።
ነገሩ እንዲህ ነው፦ ታሪኩ ዝዋይ እሥር ቤት ወንድሙን ለማየት ይገባል። እዚያም፣ “ተመስገንን ጥሩልኝ ” ሲል ፖሊሶችን ይጠይቃል። በዚህ ግዜ የመቶ ዓለቃ ማዕረግ ያለው ወታደር (ፖሊስ) ተመስገንን መጠየቅ እንደማይችል ይነግረዋል።
ታሪኩም “ምን ተፈጠረ ወንድሜን እንዳልጠይቀው የተከለከልኩት ?” በማለት ለፖሊሱ ጥያቄ ያቀር…ባል።
ፖሊሱም በማመናጨቅ “ውጣ” ይለዋል። ነገሩ ያላማረው ታሪኩ ለወንድሙ ያመጣውን ስንቅ እንደያዘ ወደ በሩ ያመራል። ነገር ግን” ውጣ” ያለው ፖሊስ በድጋሚ ታሪኩን እንዲቆም ያዘዋል።
ታሪኩም ወንድሜን ሊያገናኘኝ ነው ብሎ በደስታ ይቆማል። ፖሊሱ በመገናኛ እያወራ ” የተመስገን ወንድም ነህ አይደል?.”ይለዋል።” አዎ’ ብሎ ሳይጨርስ 8ፖሊሶች ታሪኩን ይከቡታል። ለወንድሙ ያመጣውን ምግብ ከደፉ በኅላ የዱላ ውርጅብኝ ያዘንቡበታል። ለ8። ደም በደም እስኪሆን። በድብደባ ከጎዱት በኅላ ወደ አዲስ አበባ መመለሻ የያዘውን ገንዘብ ከኪሱ (700 ብር) ይቀሙትና የእጅ ሥልኩን በመስበር ከግቢ ያስወጡታል።
ታሪኩም በዱላ የተጎዳውን ሰውነቱንና የሚፈሰውን ደም እየጠራረገ መታወቂያውን እስይዞ ገንዘብ ለትራንፖርት ተበድሮ ወደ አዲሥ አበባ ይመለሳል።…ታሪኩ ደስአለኝ በትላንትናው ዕለት በተክለኅይማኖት ሆስፒታል ህክምና ያደረገ ሲሆን፣ ጀርባው ላይ በጠመንጃ ሰደፍ በመመታቱ የአጥንት ስፔሻሊስት እንዲያየው እንደታዘዘለት ለማወቅ ችያለሁ።
ታዲያ የአባት ዕዳ ለልጅ ይተርፋል ይህ አይደል?…
ፍትህ! ፍትህ !