~በበርካታ ፊልሞች እና ድራማዎች ላይ ተውናለች በተለይም በኤፍቢሲ ሲተላለፍ በነበረው <<ትናናሽ ፀሀዬች>> በተሰኘው የሬድዮ ድራማ የእማማ ጨቤ የተሰኙ ገፅ ባህሪ በመወከል ተጫውታለች።
ቅዳሜ ምሽት በኢቢሲ እየተላለፈ በሚገኘው ቤቶች ድራማ ላይም ትርፌ በሚለውን ገፀባህሪዋ በርካታ ተከታታዮችን አፍርታለች አርቲስት ሰብለ ተፈራ።
መስከረም 1/2008 እንደደረሰን መረጃ ከሆነ ሳሪስ አካባቢ በደረሰ የመኪና አደጋ የአርቲስቷ ሂወት አልፏል። ለወዳጅ ዘመዶቿ እንዲሁም ለአድናቂዎቿ መፅናናትን እንመኛለን።