Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2784

አሜሪካ ሙስሊም መሪ “አያስፈልጋትም “ ያሉ እጩ ፕ/ታዊ ተወዳዳሪ ተቃውሞ ገጠማቸው (ከታምሩ ገዳ)

$
0
0

12036537_10154338576224298_4988585076349569315_n
ጥያቄው በዚህ ብቻ አልተቋጨም ወረድ ሲልም “ታዲያ የእስልምና ሐይማኖት ከአሜሪካ ሕገ መንግሰት ጋር ይጣጣማል ብለው ያምናሉ?” የሚል ጥያቄ ቀረበላቸው። የቤን ካርሰን ምላሽ”ነው ብዩ በፍጹም ነው ብዩአላስብም ። አገሪቱን ሙስሊም ፕ/ት ይምራ ብዮ አልቀሰቅስም፣ በዚህ ሃሳብ በጭራሽም አልስማማም” የሚል ነበር ። የ64 አመቱ ጸሃፊው፣ፖለቲከኛው ፣ ጡረተኛው የእንጎል ቀዶ ጥገና ስፐሻሊስቱ(እዚህ ላይ የእርሳቸውም የእንጎል ሰራስር ትንሽ ላላ ያለ ይመሰላል) እና ወግ አጥባቂ ክርስቲያን የሆኑት ቤን ካርሰን ወዲያውኑ ከተለያዩ ወገኖች ተቃውሞዎች የገጠማቸው ሲሆን በተለይ የአሜሪካ የሙስሊም ካውንስልዳይሬክተር የሆኑት ኒሃድ አዋድ “ካርሰን በዚህ አንጋገራቸው ብቻ ብቁ ፕ/ት መሆን አይችሉም፣ከውድድር በቅድሚያ ሊባረሩ ይገባል፣ለእጩ ፕ/ታዊ ተወዳዳሪዎች የምመክራቸው ነገር ቢኖር የአሜሪካ ህገ መንግስት ምን እንደሚል በቅድሚያ አንዲያነቡት ነው ።”በማለት ተችተዋል፣መክረዋል።

የካርሰን የምረጡኝ ቅስቀሳ ቡደን በበኩሉ” የ እጩ ፕ/ታዊው የ ካርሰን አስተያየት ተጣሟል /ተጋንኖ ነው የቀረበው” ሲል መላሽ በመሰጠት የካርሰን አስተያየት የነበረው”አሜሪካ በአሁኑ ወቅት ሙስሊም ፕ/ት ለመቀበል ዝግጁ አይደለችም የሚል ነበር ፣ካርሰን በቅርቡ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ለማነጋገር ዝግጁ ናቸው።” በማለት አልሸሹም ዞር አሉ አይነት ምልሹን ሰጥቷል። ዛሬ ማክሰኞ የምረጡኝ ዘመቻውን ኦሃዮ ውስጥ ያካሄዱት ካርሰን ከቀደመው አቋማቸው ፈቀቅ እንዳላሉ “ይልቁንም ሃይማኖታዊ ተጽእኖ ለማሳደር የሚሻ ክርሰቲያናዊ መሪም ቢሆን ቦታ የለውም።”ሲሉ ተደምጠዋል።ካርሰን በአሁኑ ወቅት 20% ቅደመ ምርጫ ደጋፍ በማግኝት በረፖብሊካኑ ጎራ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

ከዚህ ቀደም “ ፕ/ት ኦባማ ትውልዳቸው አሜሪካ አይደለም ፣የልደት ካርዳቸውም ቢሆን አሜሪካዊነታቸውን ሰለ መጠቆሙ እጠራጠራለሁ ።”ያሉት (የሪፐብሊካኖችን እጩዎች እየመሩ ያሉት) ቱጃሩ ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሰሞን ደግሞ “ከተመረጥኩ የሜክሲኮ ሰደተኞች ወደ ግዛታችን (አሜሪካ ) ዝር እንዳይሉ በአለም ትልቁ የሆነ አጥር በድንበራችን ላይ እገነባለሁ፣ፕ/ት ኦባማ የክርስትና እምነትን እያጠፉ ነው። “ በማለታችው ከዲሞክራቶች ታላቅ ተቃውሞ ገጥሟቸው ሰንብተዋል ።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2784

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>