Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all 2784 articles
Browse latest View live

ሶፊያን አህመድ በዋሽንግተን ዲሲ ተዋረደ * የወያኔ ተላላኪዎች በዲያስፖራው ውሻ መሆናቸውን ቀጥለዋል (Video)

$
0
0

ሶፊያን አህመድ በዋሽንግተን ዲሲ ተዋረደ * የወያኔ ተላላኪዎች በዲያስፖራው ውሻ መሆናቸውን ቀጥለዋል
በውጭ ያለው ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የወያኔ ተላላኪ ባለስልጣናትን እና የወያኔ ባለስልጣናትን እንደውሻ አሳፍሮ ወደ መጡበት መመለሱን ቀጥሎበታል:: መለስ ዜናዊ.. አቦይ ስብሃት.. ሬድዋን ሁሴን… ህላዊ ዮሴፍ.. ቴዎድሮስ አድሃኖም… አባዱላ ገመዳ… እስካሁን ከተዋረዱት መካከል ሲጠቀሱ አሁን ደግሞ የገንዘብ ሚኒስትሩ የሕወሓት ተላላኪ ሶፊያን አህመድ ቀልቡን በዋሽንግተን ዲሲ ተገፎ ወደ መጣበት ተመልሷል:: ቭዲዮ::

sofian_ahmed

The post ሶፊያን አህመድ በዋሽንግተን ዲሲ ተዋረደ * የወያኔ ተላላኪዎች በዲያስፖራው ውሻ መሆናቸውን ቀጥለዋል (Video) appeared first on Zehabesha Amharic.


በአይሲስ ላይ ኢትዮጵያ የሃይል እርምጃ መውሰድ አለባት ያሉ የሠራዊቱ አዛዦች ታሰሩ

$
0
0

ethiopians isis
ሊቢያ ውስጥ አይ ኤስ በተባለው አሸባሪ ቡድን በዜጎች ላይ የተፈፀመውን ግፍ የተሞላበት ግድያ መንግስት ፈጣን ግብረ መልስ መስጠት አለበት በማለት የጠየቁ የሰራዊት አዛዦች እየታሰሩ መሆናቸውን ምንጮች ሲል የደህሚት ድምጽ ዘገበ::

ለደህሚት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው የምዕራብ እዝ 7ኛ ሜካናይዝድ የሬጅመንት ምክትል አዛዥ ሻለቃ ሙሉአለም የተባለ መኮነን የኢህአዴግ ገዥው መንግስት በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም በየመን በኢትዮጵያውያን ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ላለው አስቃቂ ግፍ መንግስት ፈጣን ግብረ መልስ መስጠት አለበት ብሎ ስለጠየቀ ብቻ ፀረ ሰላም ነህ ተብሎ ባህር ዳር መኮድ በተባለ ቦታ እንደታሰረ ምንጮቻችን አስታወቁ።

ስርዓቱ በአይ ኤስ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ፍላጎት ስለሌለው የዜጎቻችንን ደም መመለስ አለብን የሚል ጥያቄ ለሚያነሱ ሰዎች እንደ ጠላት እያዬ ወደ እስር ቤት እያስገባቸው እንደሚገኝ የገለፀው ይህ መረጃ የመከላከያ ሰራዊትም በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ላለው የሚያሳዝን ተግባር ዋነኛ ተጠያቂው በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ ስርዓት መሆኑን በተደጋጋሚ እየገለፁ እንደሚገኙ ምንጮቻችን ያደረሱን መረጃ ገልጿል።

The post በአይሲስ ላይ ኢትዮጵያ የሃይል እርምጃ መውሰድ አለባት ያሉ የሠራዊቱ አዛዦች ታሰሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሶማሊያ የባህር ዘራፊዎች ታፍኜ ነበር –“ሁላችንም በፍርሐት ውስጥ እንድንገባ አደረጉን; ግርፋቱንና ስቃዩን በአይኔ ባላየውም ጩኸቱን ግን እሰማው ነበር”

$
0
0

ባለፈው አመት ሚያዝያ ላይ ነበር ሙምባይ ውስጥ በሚገኝ የኬሚካል ኩባንያ አማካኝነት የባህር ሐይል ኦፊሰር ለመሆን ስልጠና የወሰድኩት። ስራችንን ለመጀመር ወደ መርከቧ የተሳፈርነው ሰዎች እኔን ጨምሮ 22 ነበርን፡፡ ከህንድ የተውጣጡ ፕሮፌሽናል መርከበኞች እና ኢንጂነሮች ይገኙበታል። መርከቧ ላይ ከተሳፈርነው ሰዎች መካከል በእድሜ ትንሹ እኔ ነበርኩ፡፡ 21 ዓመቴ ነው፡፡
alshebab
መርከባችን የተነሳችው ከህንድ ሲሆን አቅጣጫዋ ደግሞ ወደ ኖርዌይ ነበር፡፡ ጉዞው 25 ቀናቶችን ይወስዳል፡፡ ጉዞ በጀመርን በአራተኛው ቀን ላይ አንድ ባልደረባችን ከፊት ለፊታችን የምትመጣውን ጀልባ ተመልክቶ ጩኸቱን አቀለጠው፡፡ ከኦማን 120 ማይል በሚርቅ ባህር ላይ ነበርን፡፡ ይህ ክልል ደግሞ አደገኛና አስፈሪ ነው፡፡ የጀልባዋን አመጣጥና መጠን ተመልክተን ዘራፊዎች መሆናቸውን አወቅን፡፡

ወዲያውኑ ህንድ ውስጥ ላለው የባህር ሐይል ጣቢያ የሬዲዮ ግንኙነት አደረግሁኝ፡፡ ነገር ግን ዘግይቼ ነበር፡፡ በደቂቃዎች ውስጥ ስድስት የባህር ዘራፊዎች መርከባችን ላይ በመንጠላጠል የጥይት እሩምታ ከፈቱብን፡፡ በጣም አስፈሪና አስደንጋጭ ነበር፡፡ እጅ ከመስጠት ውጭ አማራጭ አልነበረንም።
ወዲያውኑ በቀማኞቹ እየተገፈተርን ወደ ሞተር መቆጣጠሪያው ክፍል ውስጥ ገባን፡፡ ወለሉ ላይ በደረታችን እንድንተኛ ታዘዝን፡፡ ዘራፊዎቹ ለምንሰራለት ኩባንያ የ15 ሚሊዮን ዶላር ጥያቄ እንደሚያቀርቡና ገንዘቡን ካላገኙ እንደሚገድሉን በተሰባበረ እንግሊዝኛ ደነፉብን፡፡ ከፍተኛ ፍርሐት ዋጠን፡፡ እስከ ቀጣዩ ጧት ድረስ ሁላችንም ከተኛንበት ወለል ላይ ሳንንቀሳቀስ በዝምታ አሳለፍን፡፡ ሌሎች 6 ዘራፊዎች መርከባችንን ከተቀላቀሉ በኋላ ወደ ሶማሊያ ሊወስዱን እንደሆነ ነገሩን፡፡

በመርከብ ላይ ታፍነን ያሳለፍነው አስቸጋሪ ህይወት እንዲህ በቀላሉ የሚነገር አልነበረም፡፡ በመቆጣጠሪያው ክፍል ውስጥ በየጥጉ ኩርምት ብለን ተቀምጠናል፡፡ መስኮት የሌለው ክፍል በመሆኑ የታፈነ አየር ለመሳብ ተገደናል፡፡ መፀዳጃ ቤት እንድንጠቀም ቢፈቀድልንም ተበላሽቶ በመጥፎ ጠረን ታውዷል፡፡ በዚህ ምክንያት ሁላችንም ታመምን፡፡ ምግብ የሚሰጠን በሳምንት ሁለት ጊዜ ብቻ ነው፡፡ እሱም ህይወታችንን ለማቆየት እንዲረዳን ያህል ከድንች እና ሽንኩርት የተሰራ ነበር። በኋላ ላይ እግራችንን እንድንዘረጋ ስለፈቀዱልን ትንሽ ተንፈስ አልን፡፡

ዘራፊዎቹ የደቀኑብን ጠብመንጃ የማምለጥ ተስፋችንን ገድሎታል፡፡ ከነሱ ጋር ወዳጅነት እንዳንፈጥር ደግሞ ዘወትር ያስፈራሩናል፣ ይደበድቡናል፡፡ በኔ ላይ መጥፎ ድብደባ እንዳይደርስብኝ የተቻለኝን ባደርግም ባልደረቦቼ ግን ክፉኛ ሲቀጠቀጡና ሲሰቃዩ ተመልክቼያለሁ። አንደኛውን ባልደረባዬን በኤሌክትሪክ አሰቃይተውታል፤ ሌላኛውን ደግሞ ከብረት ጋር ጠፍረው በማሰር ለረዥም ሰዓት ደብድበውታል። በሌላኛው ክፍል ውስጥ የነበሩ ወዳጆቼ እንደሚሰቃዩ በድምፃቸው አረጋግጫለሁ፡፡ አሁን ድረስ የስቃይ ድምፃቸው ያቃጭልብኛል፡፡ እኔን ልክ እንደ ሌሎቹ ባልደረቦቼ ለምን ብዙ እንዳላሰቃዩኝ አላውቅም፡፡ ምን አልባት ገና ለጋ አልያም የማልጠቅም መሆኔን ተረድተው ይሆናል።

አንዳንድ ባልደረቦቼ ከዘራፊዎቹ ጋር ይፋጠጡ የነበረ ቢሆንም እኔ ግን ከእንዲህ መሰሉ ነገር እጠነቀቅ ነበር፡፡ በእያንዳንዱ ቀን ጧት፤ ከተኛሁበት የብረት ወለል ላይ ስነቃ በዚያው ቀን እንድሞት እመኝ ነበር። ወዲያው ደግሞ ራሴን በማረጋጋት የወደፊቱን ለማየት እቅበጠበጣለሁ፡፡ ማድረግ የቻልኩት ግን ዝም ብዬ መጠበቅ ነበር፡፡ አልፎ አልፎ ከመካከላችን ውስጥ አንደኛችንን መርጠው ህንድ ለሚገኘው ኩባንያችን እንድንደውል ያደርጉ ነበር፡፡ እኛም በተሰጠን የስልክ እድል ተጠቅመን ህይወታችንን እንዲታደጉልን የኩባንያ ሰዎቻችንን እንማፀናለን፡፡ እነሱ ግን የገንዘቡ መጠን እስካልተቀነሰላቸው ድረስ ምንም ማድረግ እንደማይችሉ ይነግሩናል፡፡

በመጀመሪያዎቹ አራት ወራቶች ውስጥ፤ በወር አንድ ጊዜ ከቤተሰቦቻችን ጋር በስልክ እንድንገናኝ ተፈቀደልን፡፡ ዘራፊዎቹ ይህን ያደረጉት ቤተሰቦቻችን ኩባንያ ላይ ግፊት እንዲያደርጉ ነበር። ነገር ግን ከቤተሰቦቻችን ጋር ገና ጥቂት ቃላቶችን ብቻ እንደተለዋወጥን ስልኩን ይነጥቁናል፡፡ ከስልኩ መቋረጥ ጋር የኛም አንጀት አብሮ ይቆረጣል፡፡

ገንዘቡ ሳይከፈል ብዙ ወራቶች ካለፉ በኋላ ዘራፊዎቹ ካፒቴናችንን ወስደው በሌላ ጀልባ ለብቻው አስቀመጡት፡፡ ይገድሉታል በሚል ሁላችንም ጭንቀት ውስጥ ገባን፡፡ እነሱ ግን ኩባንያው የተጠየቀውን ገንዘብ እንዲከፍል አሁንም የበለጠ እንድንለምን ነገሩን፡፡ ከ238 ቀናቶች በኋላ፣ እንድናለን ብለን ባልገመትንበት ሰዓት ኩባንያችን አምስት ሚሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ፡፡ የጀርመን መርከብ ሊወስደን እንደሚመጣም ተነገረን፡፡ ዘራፊዎቹ ገንዘባቸውን ካገኙ በኋላ ሌላ ጀልባ ላይ ተሳፍረው ከአካባቢው ጠፉ፡፡ የተባለችው የጀርመን መርከብ መጥታ ስትወስደን ደስታዬ ወደር አልነበረውም፡፡ ከ238 ቀናት በኋላ አይኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ብርሐን አየ፡፡ ደንዝዤ ስለነበረ አላለቀስኩም፡፡ ሌሎቹ ግን እየነፈረቁ ነበር፡፡ ለቅሷቸውን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡ እኔ እንደገና የተወለድኩ ያህል ነበር የተሰማኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ የበላሁት ምግብ፣ የወሰድኩት ሻወር፣ የቀየርኩት ልብስ ሁሉ ለኔ የማይታመን እንግዳ ነገር ነበር፡፡ ከስድስት ቀናት በኋላ ቤተሰቦቼ ጋር ተቀላቀልኩ። ሰውነቴ ከመክሳቱ በተጨማሪ ሁለመናዬ አስቀያሚ ሆኗል፡፡ ይህን ጉስቁልናዬን የተመለከቱት ቤተሰቦቼ በጣም አለቀሱ፡፡ ወደተከራየሁት መኖሪያ እንደተመለስኩ መርከብ ላይ በተፈጠረብኝ አጠቃላይ ሁኔታ ንዴቴን መቆጣጠር አቅቶኝ ነበር፡፡ ነገር ግን ምንም አይነት ህክምና ለመውሰድ አልፈለግሁም፡፡ በህይወቴ ውስጥ የተፈጠረው ይህ አስቀያሚ አጋጣሚ ስራዬን እንድተው አላደረገኝም፡፡ እንዲያውም ተጨማሪ የመርከበኝነት ስልጠና ከወሰድኩ በኋላ እንደገና ወደ ባህር ስራዬ ተመለስኩ፡፡ ዘራፊዎቹ የህይወቴን አቅጣጫ እንዲቀይሩት አላደረግሁም፡፡ ጉዳቱን እንደሆነ አንዴ ቀምሼዋለሁ፤ ከዚህ በላይ ምኔን ይጉዱት?
(ዲፔንድራ ይሀንን ታሪኩን በራሱ ድምፅ ቀርፆ በኢንተርኔት ለቆታል፡፡)

Source: Addis Admass Newspaper

The post በሶማሊያ የባህር ዘራፊዎች ታፍኜ ነበር – “ሁላችንም በፍርሐት ውስጥ እንድንገባ አደረጉን; ግርፋቱንና ስቃዩን በአይኔ ባላየውም ጩኸቱን ግን እሰማው ነበር” appeared first on Zehabesha Amharic.

ሐዲስ ሐዋርያ አባ ወልደ ትንሳኤ “ከኤማሁስ መንደር ሊብያ ትበደር”በደብረ ፅዮን ድንግል ማርያም ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ካቴድራል

Next: Hiber Radio: በእስራኤል የዘረኝነት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ኢትዮጵያውያን የጠነከረ ተቃውሞ ተከትሎ ባለስልጣናት ዘረኛ እርምጃ የወሰደውን ፖሊስ እናባርራለን ማለታቸው፣ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ያላትን አቋም እንድትመረምር መጠየቁ፣በየመን ያሉ ኢትዮጵያውያን ሞተን ሻማ ከማብራታችሁ በፊት በሕይወት ታደጉን ሲሉ ጥሪ አስተላለፉ፣ዶ/ር መረራ በአገር ቤት ያለው የወጣቱ ሁኔታ ምርጫ 97ን ያስታውሳል ማለታቸው፣ የመኢአድ አባላት እየታፈኑ መወሰድ መቀጠሉ፣ የጦማሪ ሶሊያና ሺመልስ ቃለ መጠይቅ እና ሌሎችም
$
0
0

ሐዲስ ሐዋርያ አባ ወልደ ትንሳኤ “ከኤማሁስ መንደር ሊብያ ትበደር” በደብረ ፅዮን ድንግል ማርያም ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ካቴድራል

 

debre

The post ሐዲስ ሐዋርያ አባ ወልደ ትንሳኤ “ከኤማሁስ መንደር ሊብያ ትበደር” በደብረ ፅዮን ድንግል ማርያም ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ካቴድራል appeared first on Zehabesha Amharic.

Hiber Radio: በእስራኤል የዘረኝነት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ኢትዮጵያውያን የጠነከረ ተቃውሞ ተከትሎ ባለስልጣናት ዘረኛ እርምጃ የወሰደውን ፖሊስ እናባርራለን ማለታቸው፣ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ያላትን አቋም እንድትመረምር መጠየቁ፣በየመን ያሉ ኢትዮጵያውያን ሞተን ሻማ ከማብራታችሁ በፊት በሕይወት ታደጉን ሲሉ ጥሪ አስተላለፉ፣ዶ/ር መረራ በአገር ቤት ያለው የወጣቱ ሁኔታ ምርጫ 97ን ያስታውሳል ማለታቸው፣ የመኢአድ አባላት እየታፈኑ መወሰድ መቀጠሉ፣ የጦማሪ ሶሊያና ሺመልስ ቃለ መጠይቅ እና ሌሎችም

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ሚያዚያ 25 ቀን 2007 ፕሮግራም

< ...በእስር ቤት በሴቶችም በወንዶችም ላይ የሚፈጸመው የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የጭካኔ ቅጣት በእነ ኤዶም ላይ የተጀመረ አይደለም እነሱ ደፍረው በማዕካላዊ የተፈጸመባቸውን ማጋለጣቸው ነው። ይሄ ወንጀል በሰብዓዊነት ላይ የተሰራ በመሆኑ በይርጋ የሚቀር አይደለም ወንጀለኞች መቼም ቢሆን ለፍርድ የሚቀርቡበት ነው…እኛ ለራሳችን ነጻነት መቆም ያለብን እኛው የአሜሪካዋ ባለስልጣን ግን… >

ጦማሪ ሶሊያና ሽመልስ በማዕከላዊ ምርመራ ሳሉ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬና ጦማሪ ማህሌት ፋንታሁን በመርማሪዎች የተፈጸመባቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በተመለከተ ያቀረቡትን አቤቱታ መሰረት በማድረግ ለጠየቅናት ከሰጠችን ማብራሪያ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<… በየመን ያለን ኢትዮጵያውያን እሳት ውስጥ ነው ያለነው አሸባሪዎቹ የሱኒ አማጽያንን ካረዱበት ቦታ እኔ ካለሁበት የየመን ዋና ከተማዋ ሰንዓ አርባ ኪሎ እርቀት ነው ያለው…ስንሞት ሻማ ቢበራልንና ሰልፍ ቢወጣልን ምን ይጠቅማል አስቀድሞ ወገን ለዓለማቀፉ ማህበረሰብ ለዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር እና አይ.ኦ.ኤም ይጩህልን። በተለይ በኤደን ያሉት ወገኖቻችን ከፍተኛ ችግር ላይ ናቸው…>

ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ሀይማኖት ከየመን ሰንዓ ለህብር ከሰጠው ወቅታዊ ማብራሪያና የድረሱልን ጥሪ መልዕክቱ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

በእስራኤል የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በወገናቸው ላይ ለተወሰደው ዘረኛ እርምጃ ያሳዩት ቁጣ የተቀላቀለበት ተቃውሞና የባለስልጣናቱ ምላሽ (ልዩ ጥንቅር)

ውይይት በኦቲዝም ላይ

ኦቲዝም ምንድነው? የኦቲዝም ያለባቸውን ልጆች እንዴት ለይተን በጊዜ ተገቢውን የህክምና እርዳታ ማግኘት ይችላሉ? ኦቲዝም ያለባቸው ልጆችና ወላጆቻቸው በማህበረሰባችን የሚገጥማቸው ፈተና እና መፍትሄው

ከዶ/ር ኤፍሬም መኮንን ከአትላንታ፣ ሰናይት አድማሱ የስነ ልቦና ባለሙያ ከሎስ አንጀለስ እና ከዚያው ከተማ የሁለት ልጆች ወላጅ የሆነችው ወ/ሮ ፌቨን ፋንቱ ጋር ተወያይተናል(ሙሉውን ያዳምጡት)

<…መንግስት ለስልጣኑ ካድሬው ለሆዱ አስቸግሮናል ።ሕዝቡን ስብሰባ እንዳይወጣ ሞክረው አልተሳካላቸውም አርባና ሃምሳ ሺህ ሰው በተለይ ወጣቱ ግልብጥ ብሎ ወጥቷል። ሁኔታው ምርጫ 97ን ያስታውሳል…እኛን ደገፉ ባሏቸው ላይ የሚደረገው ጥቃት ቀጥሏል…>

ዶ/ር መረራ ጉዲና ስለ ወቅታዊው የፓርቲያቸው የምርጫ ቅስቀሳ እና በስርዓቱ ስለሚደረግባቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰት በተመለከተ ከሰጡን ማብራሪያ(ሙሉውን ያዳምጡ)

የክፍለ ዘመኑ የቡጢ ውድድር በቬጋስ እና የአሸናፊው ቡጢኛ ማይዌይዘርና የፓኩዋያ የቅዳሜ ምሽት ግብ ግብ(ውይይት)

አቶ ጸጋዬ አላምረው በስርዓቱ የፈረሰው የእውነተኛው አንድነት የም/ቤቱ ም/አፈ ጉባዔና የፓርቲው የፋይናንስ ሀላፊ ከሰጡን ቃለ መጠይቅ

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስደተኛው ሲኖዶስ የሊቢያ ሰማዕታትን በየዓመቱ ለመዘከር ወሰነ

ሕዝቡ አሸባሪዎቹን በወገኖቹ ላይ የወሰደውን የግፍ ግድያ ኢንዳያይና እንዳያሰራጭ ተጠይቋል

በየመን የሚገኘው አይሲስ የሱኒ አማጽያንን በጭካኔ ገደለ

የኢትዮጵያኑ እጣ ፋንታ አልታወቀም

የአሜሪካ መንግስት የአገር ቤቱን አገዛዝ ከማሞካሸት እንዲቆጠብና ስለ ኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ ትክክለኛ ምልከታ እንዲኖረው ተጠየቀ

ኤርትራ የኬኒያ ፕሬዝዳንት ሁሩ ኬኒያታ በአየር ክልሌ እንዳያመሩና ወደ አሜሪካ የሚያደርጉትን ጉዞ አላስተጓጎልኩም ስትል አስተባበለች

በየመን ያሉ ኢትዮጵያውያን የአሸባሪዎች ጥቃት ሰለባ ከመሆናችን በፊት በቁማችን ድረሱልን አሉ

ዶ/ር መራራ ጉዲና በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የወጣቱ ስሜት ምርጫ 97 የሚያስታውስ መሆኑን ገለፁ

የመኢአድ አባላት ታድነው እየታሰሩ ነው

የእስራኤል ባለስልጣናት በኢትዮጵያ ቤተ እስራኤላዊ ላይ የዘረኝነት ጥቃት የፈፀመው ፓሊስ ከስራ እንደሚባረር አስታወቁ

ጠ/ሚ/ር ኔታኒያሁ የኢትዮጵያውያኑን ተወካይ ሊያነጋግሩ ነው

የሚሉና ሌሎችም ዜናዎች አሉን

The post Hiber Radio: በእስራኤል የዘረኝነት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ኢትዮጵያውያን የጠነከረ ተቃውሞ ተከትሎ ባለስልጣናት ዘረኛ እርምጃ የወሰደውን ፖሊስ እናባርራለን ማለታቸው፣ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ያላትን አቋም እንድትመረምር መጠየቁ፣በየመን ያሉ ኢትዮጵያውያን ሞተን ሻማ ከማብራታችሁ በፊት በሕይወት ታደጉን ሲሉ ጥሪ አስተላለፉ፣ዶ/ር መረራ በአገር ቤት ያለው የወጣቱ ሁኔታ ምርጫ 97ን ያስታውሳል ማለታቸው፣ የመኢአድ አባላት እየታፈኑ መወሰድ መቀጠሉ፣ የጦማሪ ሶሊያና ሺመልስ ቃለ መጠይቅ እና ሌሎችም appeared first on Zehabesha Amharic.

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ ነው

Previous: Hiber Radio: በእስራኤል የዘረኝነት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ኢትዮጵያውያን የጠነከረ ተቃውሞ ተከትሎ ባለስልጣናት ዘረኛ እርምጃ የወሰደውን ፖሊስ እናባርራለን ማለታቸው፣ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ያላትን አቋም እንድትመረምር መጠየቁ፣በየመን ያሉ ኢትዮጵያውያን ሞተን ሻማ ከማብራታችሁ በፊት በሕይወት ታደጉን ሲሉ ጥሪ አስተላለፉ፣ዶ/ር መረራ በአገር ቤት ያለው የወጣቱ ሁኔታ ምርጫ 97ን ያስታውሳል ማለታቸው፣ የመኢአድ አባላት እየታፈኑ መወሰድ መቀጠሉ፣ የጦማሪ ሶሊያና ሺመልስ ቃለ መጠይቅ እና ሌሎችም
$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ
• በየ ክፍለ ሀገሩ የሚገኙ አባላት ላይ የሚፈፀመው ድብደባ ቀጥሏል
• ‹‹የተጀመረውን የሀሰት ክስ እውነት ለማስመሰል የታቀደ ነው››
ethiopia-blue-party-300x164የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መንግስት ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አይ ኤስ አይ ኤስን ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ሰበብ እየታደኑ እየታሰሩ መሆኑን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ሀሙስ ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም ብሌን መስፍንና ተዋቸው ዳምጤ ከመስሪያ ቤት ተይዘው የታሰሩ ሲሆን ሚያዝያ 24/2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተደረገውን አመጽ መርታችኋል፡፡›› በሚል ፖሊስ ክስ እንዳቀረበባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ ዛሬ ሚያዝያ 26/2007 ዓ.ም ማቲያስ መኩሪያ ቤቱ ውስጥ እያለ በፖሊስ ተይዞ ታስሯል፡፡ ማቲያስ፣ ብሌንና ተዋቸው ወረዳ 10 (ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ) ታስረው ይገኛሉ፡፡ ይህንን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የሚደረገው እስርም ‹‹መንግስት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ የጀመረውን የሀሰት ክስ እውነት ለማስመሰል የታቀደ ነው፡፡ ፖሊስ ምርመራ ሳይጨርስ በሀሰት 20 አባላትንና 6 አመራሮችን አስረናል ብለው ነበር፡፡ እነሱ የፈለጉት ይህን ሚዲያ ላይ ወጥተው በሀሰት የፈፀሙትን ውንጀላ ማሰመሰል ነው፡፡›› ሲል አቶ ዮናታን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
በሌላ ዜና በየ ክፍለ ሀገሩ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ደህንነትና ፖሊስ የሚፈፅመው ድብደባ አሁንም መቀጠሉ ተገልጾአል፡፡ በዛሬው ቀን የደብረማርቆስ ከተማ ነዋሪና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነችው የሀሳብ ጌታቸው ‹‹ለሰማያዊ ፓርቲ ወረቀት በትነሻል›› በሚል ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀሙባት ተገልጾአል፡፡

The post የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

ወላይታ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ቅስቀሳ እንዳያደርግ ተከለከለ

$
0
0

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

• ‹‹ወላይታ ውስጥ መንግስት የለም›› አቶ ስለሽ ፈይሳ

blue partyበወላይታ ዞን ሰማያዊ ፓርቲ ቅስቀሳ እንዳያደርግ እንደተከለከለ የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊው አቶ ስለሽ ፈይሳ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ በመኪና ላይ ቅስቀሳ እያደረጉ እንደነበር የገለጹት አቶ ስለሽ ሆኖም የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች በሞተር ብስክሌት በመከታተል የመኪናውን ጎማ በሚስማር በማስተንፈስ እንዲሁም የምርጫ ዘመቻ አባላቱን በመደብደብ ቅስቀሳውን ማስተጓጎላቸውን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ ወረቀት የሚቀበለውን ህዝብ እየተከታተሉ እንደሚያስፈራሩና እንደሚደባደቡ አቶ ስለሽ ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ ጌትነት በሱፍቃድ የተባሉ ዕጩና ሌላ የሰማያዊ ፓርቲ አባልን ሞባይሎች በመቀማት ከፍተኛ ድብደባ እንደፈፀሙባቸው ተገልጾአል፡፡

የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ስም፣ የሚጠቀሙበትን መኪና ታርጋና ሌሎችም የፈፀሙትን ድርጊት በዝርዝር በማቅረብ ለፖሊስ ቢያቀርቡም ፖሊስ ‹‹ይህ ማስረጃ ሊሆን አይችልም›› በሚል ለተፈፀመባቸው በደል ምንም አይነት ትኩረት እንዳልሰጠው አቶ ስለሽ ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠቱ ለዞኑ የምርጫ ኃላፊ ቢያመለክቱም፣ የምርጫ ኃላፊው ‹‹ይህንማ ሊያደርጉ አይችሉም፡፡ ከዞኑ የኢህአዴግ የድርጅት ጉዳይ ጋር እንነጋገርበታለን›› እንዳሉ ገልጸው ምርጫ ቦርድም ከኢህአዴግ የድርጅት ጉዳይ ጋር ተነጋግሮ ነው ውሳኔ የሚሰጠው ብለዋል፡፡ ለሚፈፀምባቸው በደል መፍትሄ የሚሰጥ አካል እንደሌለ የገለጹት አቶ ስለሽ ‹‹ወላይታ ውስጥ መንግስት የለም›› ሲሉም በፓርቲው ላይ ስለሚደርሰው በደል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

The post ወላይታ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ቅስቀሳ እንዳያደርግ ተከለከለ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢትዮጵያ ብትመች – (ፍቅሬ ቶሎሳ፥ ፒ ኤች ዲ –የሁማኒቲስ ፕሮፌሰር)

$
0
0
ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ

ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ

አንተ የደላህ ሰው ሁሉን ለራስ ይዘህ፥ ተው ግፍ

አትናገር፥ “ወጣቱን ከሃገር ማን ውጣ አለው?” ብለህ፥

ሕሊናህ ደንዞ በምቾትህ ብዛት፥ የወጣቱን ስቃይ

ተስኖህ መረዳት፤ኧረ ተው አትቅጠፍ አውነቱን አብለህ!!!

ጊዜ ያነሳውን እሽቅብ ተኩሶ፥

ግፍ አዳላጭ ሆኖ ቁልቁል ሲከሰክስ፥

ፍርድ ይስተካከላል፤ ፍትህ ይበቀላል፥

የድሃ እምባን ሊያብስ፥ ተበዳይን ሊክስ ።

—ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ —-

 

 

 

 

The post ኢትዮጵያ ብትመች – (ፍቅሬ ቶሎሳ፥ ፒ ኤች ዲ – የሁማኒቲስ ፕሮፌሰር) appeared first on Zehabesha Amharic.


ትንሽ ሰለ ጀማል ወይም በትክክለኛው ስለ ኤፍሬም የማነ

$
0
0

Muslim Wedaje

11188495_847159402031809_4959704176181540321_nበሊቢያ ከተገደሉት ንፁሃን ዜጎች መካከል በሚዲያ በተለቀቀው መሰረት 28 ኢትዬጲያውያን እንደተገደሉ ተገልፆ ነበር፡፡ ሆኖም ከቀናት ቡሃላ ኢትዬጲያውያን ብቻ ሳይሆኑ ኤርትራውያንም አብረው እንዳሉ ተገልፆል፡፡

የሟቿቹ ማንነት እየተለየ በመጣ ወቅት አንዳንዱ ወድያው ማንነታቸው ታውቆ ቤተሰቦቻቸው ሃዘን ሲቀመጡ ሌሎች ደግሞ ፎቶዋቸው የተመሳሰለባቸውን እከሌም ሞተ በማለት በፌስቡክ ሲሰራጭ ቆይቷል፡፡ ሆኖም ያልሞቱት ሰዎች እረ እኔ በሂወት አለው በማለት ስህተቱን እያረምን በጋራ ስንጓዝ ነበር፡፡

በተመሳሳይም ከተገደሉት መካከል ጀማል ራህማ የተባለ ሙስሊም ኢትዬጲያዊ አብሮ መገደሉን ሶማሌላንድ ፕሬስ የተሰኘ ድህረ ገፅ መረጃውን ለቆ ነበር፡፡ ይህም መረጃ በተለያዩ ቦታዎች ተሰራጭተው ነበር፡፡ ይህንንም መረጃ በሚያጠናክር ሁኔታ የቪኦኤ የኦሮምኛው ክፍል በሊቢያ ካሉ ኢትዬጲያውያን ጋር ባደረገው ቃለመጠይቅ አንድ በሊቢያ የሚገኝ ኢትዬጲያዊ የተገደሉትን በሙሉ እንሚያውቃቸውን ቃሉን በመስጠት ከሞቱት ውስጥ አንድ ሙስሊም መኖሩን ለቪኦኤ ተናግሮ ነበር፡፡ በወቅቱ ስሙን ግን አልጠቀሰም ነበር፡፡ በዚህ መረጃ የተነሳ ጀማል ራህማ ከወገኖቹ ጋር መሰዋቱ በሰፊው ሲነገር ቆይቷል፡፡ ይህ መረጃ ሁሉም ሲቀባበለው ግን አንዳንድ እሳት ለመጫር ሌት ቀን የሚለፊት የክብሪት ልጆች እንደሚያናፍሱት ታሪክ ለመጋራት አልያ ደግሞ በውሸት ሰዎችን ለመሸንገል በሚል አልነበረም፡፡

ለመጀመርያ ጊዜ ጀማል የተባለ ሰው መሰዋቱን የዘገበው ይህ ድህረገፅ ይህ ነበር፡፡

http://www.somalilandpress.com/ethiopia-muslim-martyr-amon…/

በመቀጠልም የቪኦኤ የኦሮምኛው ክፍል በሊቢያ በስደት የሚገኝ የኦሮምኛ ተናጋሪው የሆነ ኢትዬጲያዊን ያነጋገረበትን እና ከተገደሉት ውስጥ 1 ሙስሊም መኖሩን የተናገረበትን ከቪኦኤ የኦሮሚኛ ድህረገፅ ውስጥ ገብታቹ አልያ የሚከተለውን ሊንክ በመክፈት ማድመጥ ትችላላችሁ፡፡

http://www.voaafaanoromoo.com/audio/2714864.html

ሁለቱም መረጃዎች ከላይ የተቀመጡ በመሆናቸው የመረጃ ምንጮቹን መጠየቅ እና ማረጋገጥ ይቻላል፡፡

እንደ ዳንኤል ክብሪትአይነቱ ጭራሽም ሙስሊም እና ክርቲያኑን ለማዋደድ የተፈጠረ ድራማ እንደሆነ አስመስለው ሲያቀርቡ ነበር፡፡ የሙስሊም እና የክርስቲያን ተከባብሮ በሰላም የመኖር ታሪክ አሁን የተጀመረ እስኪመስል ድረስ ሙስሊሞች ድራማ እንደሰሩ አስመስሎ ማቅረብ ለምን አስፈለገው ??ስለመስዋትነትስ በኢትዬጲያ ሙስሊሞች ላይ ለመንጠባረር ስለምን አስፈለገው??? መስዋትነትን፣ መታረድን ለኢትዬጲያ ሙሰሊምስ ይነገረዋል እንዴ???. እስቲ ቦሩ ሜዳ ትመስክር!!

የኢትዬጲያ ሙስሊም ከጥንት ታሪኩ ጀምሮ በኢትዬጲያ ውስጥ ባሉ መሪዎች አንገቱ ሲቀላ፣ሲታረድ እና ሲጨፈጭ እመቢኝ ብሎ ለእምነቱ ሲሰዋ እና ሲንገላታ መቆየቱን ሊዘነጋ አይገባውም፡፡ ሙስሊሙ የተጨፈጨፈው በውጪ ጠላት ሳይሆን በሃገሬው መሪ መሆኑም ይሰመርበት፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ሙስሊሙ በክርስቲያን ወገኖቹ ላይ አልተዘባበትም፣በፍቅር እና በሰላም ተዋዶ ተከባብሮ እየኖረ ይገኛል፡፡

የኢትዬጲያ ሙስሊም ድርጊቱን ያወገዘውስ ሃይማኖቱ ስለሚያዘው፣ሰብአዊነት ስለሚሰማው እና የሞቱት ወገኖቹ በመሆኑ እንጂ የክብሪት ልጆች እንዳይከፋቸው በሚል አልነበረም፡፡

ግድያን እና ግፍን የምናወግዘው እምነት እየለየን ቢሆን ኖሮ የሊቢያ የተገደሉት ክርስቲያኖች ስለሆኑ ምን አገባን ባልን ነበር፡፡ እስካሁን አይኤስ ከገደላቸው ሙስሊሞች ቁጥር አንፃር ሲታይ እምነታቸው ክርስቲያን በመሆናቸው የተገደሉት ሰዎች ቁጥራቸው ለንፅፅር እንኳን የማይቀርብ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ምክንያቱም ISIS በአስርሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞችን በኢራቅ እና በሶሪያ አርዷል ጨፍጭፏል፡፡ ሌላው ቢቀር ሰሞኑን ብቻ የመን ገብቶ የገደላቸውን ሰዎችን ስናይ ክርስቲያኖች አልነበሩም፡፡ ይህ ስል ግን ግድያን ከቁጥር ጋር እያወዳደርኩኝ እያቃለልኩኝ አይደለም፡፡ የአንዲት ነፍስ ዋጋ በኢስላም ከሰው ልጆች ነፍስ እኩል ዋጋ እንዳላት ስላስተማረን ማንም በግፍ ቢገደል እናዝናለን እንጂ እምነቱ ሌላ ስለሆነ አንደሰትም፡፡ ሙስሊሞች እየተጨፈጨፉ በመሆኑ የሌላ እምነት ተከታዬችም ይገደሉ አንልም፡፡

በወገኖቻችን ላይ በሊቢያ የደረሰው ግድያ የሽብር ቡድኑ ISIS በለቀቀው የ 28 ደቂቃ ቪዲዬ ላይ እምነታቸውን እንዲቀይሩ ብቻ ተጠይቀው መገደላቸውን ሳይሆን የተገለጸው እምነታቸውን የማይቀይሩ ከሆነ መክፈል ያለባቸውን ግብር እንዲከፍሉ እና እንዲለቀቁ ተጠይቀው እንደነበር ነው፡፡ ሽብር ቡድኑ ሁለቱንም የማታደርጉ ከሆነ በሚል እንደገደላቸው በቪዲዬ ላይ ተገልፆል፡፡ አንድ መዘንጋት የሌለበት ጉዳይ ግን ሶርያ እና ኢራቅ ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች እምነታቸውን ሳይቀይሩ ግዴታ የሚደረግባቸውን አመታዊ ግብር እየከፈሉ በሰላም እምነታቸውን እያራመዱ እየኖሩ መሆኑን ማስታወስ እወዳለው፡፡ ይህን ለማንሳት የፈለኩት ዳንኤል ክብሪት የኢትዬጲያ ሙስሊሞች ወንጀሉን የፈፀሙት ያህል ሙስሊሙን በመጠየፍ በተደጋጋሚ በጀማል ሽፋን ሙስሊሞች የክስርስቲያኖችን ክብር ለማጉድፍ እንደተንቀሳቀሱ አስመስሎ ሲያቀርብ ስለነበር ነው፡፡ –

መታወቅ ያለበት ሌላው ነጥብ የኢትዬጲያ ሙስሊም ማንንም ፈርቶ ለማጭበርበር የሚሞክበት ነገር የለም፡፡ ጀማል ሙስሊም ሆነ ክርስቲያን አልያ ድንጋይ አምላኪ ለኛ ለሙስሊሞች ሰው በመሆኑ ብቻ የተፈጸመበትን ድርገት እናወግዛለን፡፡ ጀማል ሙስሊም በመሆኑም አንዳችም ለኢትዬጲያ ሙስሊም የሚጨምርለትም ሆነ የሚቀንስበት ነገር የለም፡፡ ከተገደሉት መካከልም ሙስሊም አለ ብሎ መናገሩ ሆን ተብሎ ሰዎችን ለማጭበርበር ሳይሆን የአይን እማኞች አይተናል ብለው የተናገሩትን መረጃ በመመርኮዝ ነው፡፡

ጀማል የተባለው ሰው ትክክለኛ ማንነቱ ኤፍሬም የማነ መሆኑ ቢታወቅ ቀድሞ የተለቀቀው መረጃ ስህተት ነበር ብሎ እንደሌሎቹ ከማለፍ ይልቅ ሙስሊሙ ሆን ብሎ ክርስቲያኑን ለመሸንገል የፈጠረው አድርጎ ለማቅረብ መሞከሩ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ያለውን ንቀት እና በሙስሊም እና በክርስቲያኑ ወገኖች መካከል እሳት ለማቀጣጠል ያለውን ትጉህ ፍላጎት ያሳየ ነው::

ጀማል የተባለው ሰው ኤፍሬም ሆኖ በመገኘቱ ኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች የሚያጡት አንዳችም ነበር የለም፡፡ ድርጊቱን ያወገዙት ጀማል ስለሆነ አልያ ገብረማርያም ስለሆኑ ሳይሆን ሰው በመሆናቸው ብቻ ነው፡፡ በእምነታቸው መገደላቸው የእምነቱ ተከታዬች የበለጠ ቢያስቆጫቸውም በአለም አቀፍ ደረጃ የሽብር ቡድኑ እየጨፈጨፈ የሚገኘውን ሙስሊም ብዛት አይናቸው ተከፍቶ ቢያዩ ግን ተመስገን ብዙም እኛን አልነኩንም ብለው ያመሰግኑ ነበር፡፡

በተረፈ የሙስሊሞችን ስብእና ለማጉላት ጀማል የተባለ ገጸ ባህሪ ፈጥሮ የምናወራበት ምክንያት አለመኖሩ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ለ 1400 አመታት ሙስሊሙ ከክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖቹ ጋር ችሎ በመኖር አስመስክሯል፡፡ አሁንም በሊቢያ ባሉ ስቃይ እየደረሰባቸው በሚገኙ ክርስቲያን ወገኖች ላይ ሂወታቸውን በከፍተኛ አደጋ ውስጥ በመክተት ድጋፍ እና ትብብር እያደረጉላቸው የሚገኙት የዳንኤል ክብሪት ቲፎዞዎች ሳይሆኑ ኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች መሆናቸው ሊዘነጋ አይገባም፡፡ ይህን ደሞ በድህረገጽ መረጃ የተገኘ ሳይሆነ በሊቢያ የሚገኙት ክርስቲያን ወገኖቻችን በአንደበታቸው የመሰከሩት ነው፡፡ ሙስሊሙ ግን ይህን መልካም ነገር በመደረጉ በክርስቲያን ወገኖቹ ላይ እንደዳንኤል ክብሪት አልተመፃደቀም፡፡ ሙስሊሞቹ ሃይማኖታዊም ሆነ ሰብአዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው እናመሰግናቸዋለን እንጂ ሙስሊሞቹ በሰሩት ስራ እዚህ ያለነው ሙስሊሞች አንመፃደቅም፡፡

በመጨረሻም፡,- ጀማል በሚል ተሰራጭቶ የነበረው መረጃ ትክክለኛ መረጃው ሲጣራ እነክብሪት ሲፎክሩ እንደነበረውኢትዬጲያዊ ሳይሆን ኤርትራዊ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ትክክለኛ ስሙም ኤፍሬም የማነ የሚል ነው፡፡ የራሱ የፌስቡክ ገፅ ላይ እንደተመለከትኩት የሙስሊሞችን ነጭ ጀለብያ ለብሶ የተነሳውንም ፎቶ ተመልክቻለው፡፡ እንደዛም ሁሉ ክር አንገቱ ላይ የሚያሳይ ፎቶም አድርጎ ተመልክቻለው፡፡ በመሆኑም ጀማል ተብሎ የነበረው ኤፍሬም የማነ በሚል መረጃውን እናስተካክላለን ማለት ነው፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን ከራሱ የፌስቡክ ገፅ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

https://www.facebook.com/efremg.yemane/

ኤፍሬም ሙስሊም ነው ክርስቲያን ነው ብለን ሂሳብ አናወራርድም፡፡ ሙስሊም መሆኑን የሚገልፅ የፅሁፍ እና አይን እማኞች መረጃ ሰማን፡፡ እሱን ተቀበልን፡፡ መረጃው ሲጣራ ጀማል ሳይሆን ኤፍሬም መሆኑ ታወቀ፡፡ ስለዚህ ኤፍሬም የሚለውን ተቀብለን አንሄዳለን፡፡ በድህረገፅ የተለቀቀው መረጃ ስህተት መሆኑን ስንቀበል በቪኦኤ በኦሮምኛው ክፍል የቀረበውን መረጃ ደግሞ ልክ እንደዚሁ ሁሉ እስኪረጋገጥ እንጠብቃለን ማለት ነው፡፡ ለኛ ለሙስሊሞች ግን ኤፍሬም መሆኑ ወይም ጀማል መሆኑ ወይም ኢትዬጲያዊ ወይም ኤርትራዊ መሆኑ ሳይሆን ሰው በመሆኑ ብቻ የደረሰበትን ግድያ አውግዘናል፡፡ወደፊትም እናወግዛለን ኢንሻአላህ

ከዚህ በዘለለ ጉዳዩ ሆን ተብሎ የተደረገ በማስመሰል የፖለቲካ ቁማር ለማድረግ ለሚኳትኑ ክብሪቶች ልክ እንደስሟ ክብሪት ከራሷጋር ተጋጭታ እሳት ፈጥራ እንደምትቃጠለው ሁሉ የሰው ክብሪቶችም ከራሳቸው ጋር ተጋጭተው ሲነዱ ይከርማሉ እንጁ ሙስሊሙ እና ክርስቲያኑ ወደ እርስ በእርስ እልቂት አይጋበዝም፡፡

ለሙስሊም ወንድም እና እህቴቼ ደግሞ ሚያዚያ 30 መላው ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ የፍርድ ውሳኔ የሚተላለፍበት ቀን በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ቢዚ በመሆን እንዳንዘናጋ አደራ እላለው፡፡

ለሃገራች አላህ ሰላምን ያስፍንልን

ለኤፍሬም ቤተሰቡ መፅናናትን አላህ ይስጣቸው

The post ትንሽ ሰለ ጀማል ወይም በትክክለኛው ስለ ኤፍሬም የማነ appeared first on Zehabesha Amharic.

ጠ/ሚኒስትር ናታኒያሁ የተቃውሞው መነሻ የሆነውን ወታደር ደማስ ፈቃደማስ ፈቃደን አነጋገሩ

$
0
0

natanyahu 2

netanyahu
ኢሳት ዜና :-በሺዎች የሚቆጠሩ ቤተእስራኤላውያን ዘረኝነትን በመቃወም ካለፈው ሃሙስ ጀምሮ የጀመሩት የተቃውሞ ሰልፍ እሁድ ተጠናክሮ ከቀጠለ በሁዋላ፣ የአገሪቱ ጠ/ሚኒስትር ቤንጃሚን ናታኒያሁ ፣ የተቃውሞው መነሻ የሆነውን ወታደር ደማስ ፈቃደን አነጋግረውታል።

ወታደር ደማስ በእስራኤል ፖሊሶች መደብደቡ በአገሪቱ የሚኖሩትን በተእስረኤላውያንን በእጅጉ አበሳጭቶ ለተቃውሞ አደባባይ አስወጥቶአቸዋል። ቤተእስረኤላውያኑ በአገሪቱ ውስጥ ያለውን ዘረኝነት እጥብቀው የተቃወሙ ሲሆን፣ ቁጣቸውንም የተለያዩ ጠርሙሶችና ፕላስቲኮችን በፖሊሶች ላይ በመወርወር ገልጸዋል። በፖሊሶችም በቤተእስረኤላውያን ላይ ጉዳት መደርሱን መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል።

እሁድ የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በቅርብ የእስራኤል ታሪክ ያልታየ ነው ተብሎአል። ተቃውሞውን ተከትሎ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያውያኑ በአግባቡ አለመያዛቸውን፣ ቁጣውም ለአመታት የተጠራቀመ መሆኑን በመግልጽ ይቀርታ ጠይቀዋል።

ጠ/ሚኒስትሩም ችግሩን እንደሚፈቱ ቃል በመግባት ሁኔታውን ለማረጋጋት እየሞከሩ ነው።
ኢሳት ያነጋገራቸው ቤተእስራኤላውያን እንደሚሉት የአሁኑ ተቃውሞ የ30 አመታት የዘር መድሎ የወለደው ነው። ቤተእስረኤላውያኑ ተቃውሟቸውን የሚቀጥሉ ከሆነ፣ ሁኔታው ሊቀየር እንደሚችል ተስፋቸውን እየገለጹ ነው።
የአለም የመገናኛ ብዙሃን ቤተእስረኤላውያኑ ያደረጉትን ተቃውሞ ሰፊ የዜና ሽፋን ሰጥተውታል።

The post ጠ/ሚኒስትር ናታኒያሁ የተቃውሞው መነሻ የሆነውን ወታደር ደማስ ፈቃደማስ ፈቃደን አነጋገሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

የትውልደ-ኢትዮጵያ ቤተ-እሥራኤል ቁጣ – VOA

$
0
0

60167F0B-2C9A-46FD-A63D-B03C1534AF37_w640_r1_sትውልደ-ኢትዮጵያ ቤተ-እሥራኤል ይደርስብናል የሚሉትን የዘረኝነት መድልዎህ የፖሊስ ጭካኔ የሚያጣራ የመንግሥት ኮሚቴ በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ተቋቁሟል፡፡

ትውልደ-ኢትዮጵያ ቤተ-እሥራኤል ይደርስብናል የሚሉትን የዘረኝነት መድልዎህ የፖሊስ ጭካኔ የሚያጣራ የመንግሥት ኮሚቴ በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ተቋቁሟል፡፡

የቤተ-እሥራኤላዊያኑ ችግር መድኃኒት ሊፈለግለት የሚገባ “ክፍት ቁስል” ነው ሲሉ የእሥራኤል ፕሬዚዳንት ሩቨን ሪቭሊን ዛሬ አስታውቀዋል፡፡

ትናንት በሺሆች የሚቆጠሩ እሥራኤላዊያኑ የኢትዮጵያ አይሁድ በማዕከላዊ ቴል አቪብ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥተው ዋናውን አውራ ጎዳና ለረዥም ሰዓት ዘግተዋል፡፡

የእሥራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ከትውልደ-ኢትዮጵያ ቤተ-እሥራኤል ማኅበረሰብ አባላት ጋር ዛሬ ተገናኝተው ተወያይተዋል፡፡

እሥራኤላዊያኑ የኢትዮጵያ አይሁድ በማዕከላዊ ቴል አቪብ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥተው ዋናውን አውራ ጎዳና ለረዥም ሰዓት ዘግተዋልእሥራኤላዊያኑ የኢትዮጵያ አይሁድ በማዕከላዊ ቴል አቪብ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥተው ዋናውን አውራ ጎዳና ለረዥም ሰዓት ዘግተዋል

ፕሬዚዳንት ሪቭሊን በዛሬው መግለጫቸው “አላስተዋልንም፤ በቅጡ አላዳመጥንም፡፡ እኛ’ኮ እርስ በራሣችን ባይተዋር አይደለንም፤ ወንድማማች ነን፡፡ በኋላ ሁላችንም ወደሚያሳዝነን ወይም ሊቆጨን ወደሚችል ደረጃ ልንዘቅጥ አይገባንም” ብለዋል፡፡

ችግሮቹና በደሎቹ እንዳይደገሙ ሊወሰዱ የሚገባቸውን እርምጃዎችም ዛሬ የተቋቋመው ኮሚቴ ይተልማል ተብሏል፡፡

የተቃውሞ ሰልፎቹ የተጀመሩት ባለፈው ሣምንት የእሥራኤል ፖሊሶች አንድ የደንብ ልብስ የለበሰ የኢትዮጵያ ዝርያ ያለውን የራሣቸውን ወታደር ክፉኛ ሲደበድቡ የሚያሣይ ቪዲዮ ከወጣና ከተሠራጨ በኋላ ነው፡፡

እሥራኤል ውስጥ ከ135 ሺህ በላይ ትውልደ-ኢትዮጵያ ቤተ-እሥራኤል ይኖራሉ፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

[jwplayer mediaid=”41118″]

The post የትውልደ-ኢትዮጵያ ቤተ-እሥራኤል ቁጣ – VOA appeared first on Zehabesha Amharic.

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ ነው:: ‪

$
0
0

ሰማያዊ ፓርቲ የአፍሪካ ህብረት ምርጫውን እንዳይታዘብ እንደሚፈልግ ገለጸ

•የህብረቱ ታዛቢ ቡድን ፓርቲዎችን አነጋግሯል
• በየ ክፍለ ሀገሩ የሚገኙ አባላት ላይ የሚፈፀመው ድብደባ ቀጥሏል
• ‹‹የተጀመረውን የሀሰት ክስ እውነት ለማስመሰል የታቀደ ነው››

ethiopia-blue-party-300x164የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መንግስት ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አይ ኤስ አይ ኤስን ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ሰበብ እየታደኑ እየታሰሩ መሆኑን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ሀሙስ ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም ብሌን መስፍንና ተዋቸው ዳምጤ ከመስሪያ ቤት ተይዘው የታሰሩ ሲሆን ሚያዝያ 24/2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተደረገውን አመጽ መርታችኋል፡፡›› በሚል ፖሊስ ክስ እንዳቀረበባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ ዛሬ ሚያዝያ 26/2007 ዓ.ም ማቲያስ መኩሪያ ቤቱ ውስጥ እያለ በፖሊስ ተይዞ ታስሯል፡፡ ማቲያስ፣ ብሌንና ተዋቸው ወረዳ 10 (ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ) ታስረው ይገኛሉ፡፡ ይህንን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የሚደረገው እስርም ‹‹መንግስት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ የጀመረውን የሀሰት ክስ እውነት ለማስመሰል የታቀደ ነው፡፡ ፖሊስ ምርመራ ሳይጨርስ በሀሰት 20 አባላትንና 6 አመራሮችን አስረናል ብለው ነበር፡፡ እነሱ የፈለጉት ይህን ሚዲያ ላይ ወጥተው በሀሰት የፈፀሙትን ውንጀላ ማሰመሰል ነው፡፡›› ሲል አቶ ዮናታን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

በሌላ ዜና በየ ክፍለ ሀገሩ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ደህንነትና ፖሊስ የሚፈፅመው ድብደባ አሁንም መቀጠሉ ተገልጾአል፡፡ በዛሬው ቀን የደብረማርቆስ ከተማ ነዋሪና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነችው የሀሳብ ጌታቸው ‹‹ለሰማያዊ ፓርቲ ወረቀት በትነሻል›› በሚል ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀሙባት ተገልጾአል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ የአፍሪካ ህብረት 5ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንዳይታዘብ እንደሚፈልግ ለህብረቱ ታዛቢ ቡድን ገለጸ፡፡ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ዛሬ ሚያዝያ 26/2007 ዓ.ም በምርጫ የሚወዳደሩ ፓርቲዎችን በተናጠል በምርጫው ዙሪያ ያነጋገረ ሲሆን፣ ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው ቡድኑን ያነጋገሩት አቶ ወረታው ዋሴ እና አቶ እምዕላሉ ፍስሃ ህብረቱ ምርጫውን እንዳይታዘብ እንደሚፈልጉ አስረድተዋል፡፡

የህብረቱ ታዛቢ ቡድን ከአሁን ቀደም በተካሄዱት ሀገራዊ ምርጫዎች መታዘቡን ያወሱት የሰማያዊ ተወካዮች፣ ህብረቱ በሪፖርቱ ለአምባገነኖች እውቅና ከመስጠት ያለፈ አንዳች እውነታውን የሚያሳይ ትዝብቱን አላስቀመጠም ሲሉ ለታዛቢ ቡድኑ መግለጻቸውን ተናግረዋል፡፡

‹‹ህብረቱ የአምባገነኖች ስብስብ ነው›› ያሉት የፓርቲው ተወካዮች፣ የአውሮፓ ህብረትና አሜሪካ በኢትዮጵያ ምርጫ ላይ ተስፋ በማጣት በታዛቢነት እንደማይሳተፉ ማሳወቃቸውን በመግለጽ፣ የአፍሪካ ህብረት ግን ለአምባገነኖች እውቅና ለመስጠት መምጣቱ በሰማያዊ ፓርቲ ተቀባይነት የሌለው ነው ብለዋል፡፡

‹‹ቀደምት ፓን አፍሪካኒስቶች አፍሪካን ከቅኝ ግዛት ነጻ ለማውጣት ታግለዋል፤ የአሁኖቹ እውነተኛ ፓን አፍሪካኒስቶች ደግሞ አፍሪካን ከአምባገነኖች ነጻ በማውጣት ወደ ዴሞክራሲ ማሸጋገር ይጠበቅባቸዋል›› በማለት ለህብረቱ ታዛቢዎች የገለጹት የፓርቲው ተወካዮች፣ በዚህ ረገድ ህብረቱ ተገቢውን ስራ እያከናወነ ነው ለማለት እንደማይቻል አስረድተዋል፡፡

የአፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ መንግስት ጋባዥነት 5ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለመታዘብ በቅርቡ አዲስ አበባ መግባቱ ይታወቃል፡፡ ህብረቱ በዛሬው ዕለት ያነጋገራቸው ፓርቲዎች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ በውል አልታወቀም፡፡

The post የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ ነው:: ‪ appeared first on Zehabesha Amharic.

የዜጎች ከፍተኛ ጭፍጨፋ በመተማ

$
0
0

– የሚሊዮኖች ድምጽ
በሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ከተማ፣ በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች ናቸው ያሏቸውን ቤቶች ለማፍረስ በሚሞክሩበት ጊዜ፣ ከነዋሪው በተነሳዉ ተቃዉሞ ምክንያት በተፈጠረው ግጭት፣ የሕወሃት ታጣቂዎች ሁለት ነዋሪዎችን ሲገድሉ፣ ሶስት ለሞት የሚያደርስ ከፈተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከአምሳ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል።
metema 3

metema 2

metema
በአምቦ፣ በባህር ዳር በመሳሰሉት ቦታዎች እንደታየው ዜጎች በሕወሃት ታጣቂዎች ጥይት እንደ ቅጠል እየረገፉ ነው። ህወሃት ከሕዝብ የሚነሱትን መሰረታዊ የፍትህ፣ የዴሞክራሲና የለዉጥ ጥያቄዎች፣ በሃያ አንደኛ ክፍል ዘመን እንዳሉ ድርጅቶ ዘመናዊና ስልጣኔ በተሞላበት መልኩ ማስተናገድ ሲገባው፣ በስድሳዎች ጊዜ እንደነበረው መግደል፣ ማረድና ፣ ዜጎችን እንደ እንስሳ መደብደቡን በመምረጥ የጫካን ኋላ ቀር ፖለቲካ እያራመደ መሆኑ በድጋሚ ዛሬ ደግሞ በመተማ ተመስክሯል።

ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ከደርቡሽ ጋር በተደረገ ትንቅንቅ አጼ ዮሐንስን ጨመሮ በርካቶች ደማቸውን ያፈሰሱባት መተማ፣ ዛሬ ከዉጭ ወራሪዎች ሳይሆን፣ ከሕወሃቶች በተተኮሰ ጥይት የልጆቿ ደም እየተረጨባት ይገኛል።
መተማ ዛሬ ይሄንን ትመስል ነበር።

The post የዜጎች ከፍተኛ ጭፍጨፋ በመተማ appeared first on Zehabesha Amharic.

የሽራሮ ከተማ አስተዳዳሪዎች የስር ተላላኪዎቻቸውን ሕዝቡ ኢሕአዴግን እንዲመርጥ አልቀሰቀሳችሁም በሚል ከሃላፊነታቸው ማውረዳቸው ተዘገበ

$
0
0

የሽራሮ ከተማ አስተዳዳሪዎች በነሱ ስር ሆነው ሲያገለገሏቸው የቆዩትን ሰዎች; ህዝቡን ኢህአዴግን እንዲመርጥ በሚያስችል መንገድ አልቀሰቀሳችሁትም በማለት ከሃላፊነታቸው እያወረዷቸው እንደሆኑ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ገለፀ ሲል የደህሚት ድምጽ ዘገበ::
election
በሸራሮ ከተማ የሚገኙት አስተዳዳሪዎች በነሱ ስር የሚገኙትን በሃላፊነት የተቀመጡ አባላት ላይ እምነት ስላጡባቸው ነዋሪው ህዝብ ህ.ወ.ሃ.ት ኢ.ህ.አ.ዴ.ግን እንዲመርጥ የሚያስችል አስፈላጊውን ቅስቀሳ አላደረጋችሁለትም በሚል ምክንያት ከሃላፊነታቸው እያወረዷቸው መሆኑን የገለጸው መረጃው ከስልጣናቸው ከተወገዱት መካከልም የወረዳው ፕሮፖጋንዳ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ሃፍቲና የወረዳው የሴቶች ሃላፊ ወ/ሮ ደስታ ማሙ እንደሚገኙባቸው ለማወቅ ተችሏል።

እነዚህ በሃላፊነት ደረጃ ሲሰሩ ቆይተው ባሁኑ ሰአት ከስልጣናቸው የታገዱት የህወሃት ኢህአዴግ አመራሮች ስርአቱ በህዝቡ ላይ ያለው ተቀባይነት ስላጣ የስርዓቱ ሃላፊዎች በነሱ ስር ለሚገኙ አመራሮች ከሃላፊነታቸው እያወረዷቸውና እየሾሟቸው አንደሆኑና; ይህ ድርጊትም በሸራሮ ከተማ ብቻ ሳይሆን; በመላው ያገራችን አካባቢዎች እየተሰራበት እንደሆነ መረጃው አክሎ አስረድቷል።

The post የሽራሮ ከተማ አስተዳዳሪዎች የስር ተላላኪዎቻቸውን ሕዝቡ ኢሕአዴግን እንዲመርጥ አልቀሰቀሳችሁም በሚል ከሃላፊነታቸው ማውረዳቸው ተዘገበ appeared first on Zehabesha Amharic.

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ

$
0
0

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ትናንት ሚያዝያ 27/2007 ዓ.ም ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
Yilikal
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የዴሞክራሲ፣ ሰብአዊ መብትና ሰራተኞች ምክትል ዋና ፀኃፊ የሆኑት ሚስተር ስቲቭ ፌልድስቴይን ጨምሮ ሌሎችንም ኃላፊዎች አግኝተው ስለ ኢትዮጵያና ስለ ቀጠናው ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል፡፡

ኢ/ር ይልቃል ከስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎቹ ጋር በነበራቸው ቆይታ ስለ መጭው ምርጫ፣ ሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የእምነት እና ሀሳብን በነፃነት መግለጽ መብት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በፀረ ሽብር ህጉና በደህንነት ስም እየተፈፀሙ ያሉ ችግሮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡

ሚስተር ፌልድስቴይን ስለ ሰማያዊ ፓርቲ እንቅስቃሴዎች ዝርዝር ጥያቄዎችን ያነሱ ሲሆን ኢ/ር ይልቃልም በዝርዝር ማስረዳታቸው ታውቋል፡፡ በቅርቡ ምክትል የውጭ ጉዳይ ኃላፊዋ ውይንዲ ሸርማን ንግግር ላይም መወያየታቸው ታውቋል፡፡

The post የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ appeared first on Zehabesha Amharic.


የሰሜን ጎንደር ሕዝብ አመጽ በርትቷል * በድንበር ከተሞች አሁንም ችግሩ እየሰፋ ነው

$
0
0

metema 2
ምንሊክ ሳልሳዊ

የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች እና ካድሬዎቻቸው በሕወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ተወካዮች መሪነት በባህር ዳር ስብሰባ መቀመጣቸው በታወቀበት በዚህ ሳምንት በአማራ ክልል ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ሕዝባዊ እምቢተኝነት መከሰቱን እና የፌዴራል ፖሊሶች ከሕዝቡ ጋር እየተጋጩ መሆኑ ሲጠቆም በጎጃም ገበሬው በብጡ ደጃፍ እና በቤቱ ውስጥ የእያኔን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት እንዲለጥፍ እየትገደደ እና እምቢ ያለ በመታሰር ላይ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል::

ሕወሓቶች በሚመሩት እና በባህር ዳር እየተካሄደ ያለው የብአዴን ስብሰባ ላይ ከምርጫው ጋር ተያይዞ የሚመጥውን ችግር እና ሕዝቡ ሊመርጠን ስለማይችል በድምጽ መስጫ ካርዶች ዙሪያ መወሰድ ስላለባቸው እርምጃዎች እንዲሁም ትጥቅ ያልፈቱ መሳሪያ የቀበሩ ሰዎች ካሉ አስቸኳይ ክትትል ተደርጎ እርምጃ እንዲወሰድ የሚሸፍቱ ሰዎች የሚተረጠሩ ካሉ እንዲታሰሩ የሚሉ ተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከትግራይ ክልል አማራ አዋሳኝ በሆኑ ቦታዎች ያሉ የሕወሓት ሚሊሻዎች እና ካድሬዎች ወደ አማራ ክልል በማምጣት ድምጽ ሰጥተው እደ አከባቢያቸው እንዲመለሱ እንዲሁም በተለያየ ወረዳ የተለያያ የመራጭ ካርድ ዬሰዱ ሰዎች አስቸኳይ የትራንስፖርት አቅርቦት እየተደረገላቸው በየወረዳው እየሄዱ እንዲመርጡ ሲባል ከምርጫው በኋላ ሊነሱ የሚችሉ የአመጽ ስጋቶችን ለመቆጣጠር የመከላከያ ሰራዊት አባላይ የፌዴራል ፖሊስ ልብሶችን በመልበስ ተክተው እንደሚሰሩ እና ካድሬዎች እና የጸጥታ ሰራተኞች አስፈላጊዉን ትብብር በማድረግ የሚፈጠረው ችግር በቁጥጥር ስር እንዲውል እንዲያደርጉ ከሕወሓት ሹሞች መመሪያ ተሰቷቸዋል::

በሰሜን ጎንደር የላይ እና የታች አርማጮ ጨምሮ በአብድራፊ በሁመራ በመተማ በሸዲ በጭልጋ አክባቢዎች በከፍተኛ ደረጃ ሕዝቡ እና የወያኔ ፖሊሶች ውጊያ የገጠሙ ሲሆን በርካቶች ሲቆስሉ በአከባቢው የተነሳው የህዝብ እምቢተኝነት እየሰፋ መምጣቱን እና ጥያቄዎች ምላሽ አለማግኘታቸው ሲከፋ የመኖሪያ ቤታችውን በማፍረስ ሕዝቡን ለጎዳና ተዳዳሪነት መዳረጉ በመተማ እና አከባቢው የሚኖሩ ሕዝቦችን ቁጣ ቀስቅሶ እስከ ዛሬ ድረስ ሊበርድ ያልቻለ ከፍተኛ ግጭት በአከባቢው እየተደረገ እንደሆነ የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::በአጠገባችን መጥቶ የሚያግዘን ማጣታችን ነው እንጂ ወያኔን ከጎንደር ክፍለሃገር ጠራርገን እናወጣው ነበር ያሉ ወጣቶች ባለው ስርአት መማረራቸውን በቁጣ ይናገራሉ::ይህ በእንዲህ እንዳለ በጎጃም ክፍለሃገር የሚኖሩ ገበሬዎች የወያኔን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት በቤታቸው እስጥ እና በቤታቸው ደጃፍ ላይ በግዳጅ እንዲለጥፉ የተደረገ ሲሆን ለመለጠፍ ፍቃደኛ ያልሆኑ ገበሬዎች በመታሰር ላይ እንደሚገኙ አንድ የደብረማርቆስ ወጣት በላከው መረጃ ገልጿል:: ሕዝቡ አስተባባሪ እና አደራጅ ነው ያጣው ቢባልም በራሱ መሪነት ብሶቱን እየገነፈለ እየወታ የሚገኘው ሕዝብ ለነጻነቱ በጋራ ሆኖ መታገሉን እንደቀጠለ ነው::

The post የሰሜን ጎንደር ሕዝብ አመጽ በርትቷል * በድንበር ከተሞች አሁንም ችግሩ እየሰፋ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

“የጀግኖች እናቶቻችንን እና አባቶቻችንን ፈለግ እንከተል!”–ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

$
0
0

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ማክሰኞ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. ቅፅ ፫ ፣ ቁጥር ፲፭

ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ አድርገዋት የኖሩት ደረታቸውን ለጦር፣ እግራቸውን ለጠጠር፣ ሕይዎታቸውን ለሀገር ሉዓላዊነት እና ክብር እንዲሁም ለወገኖቻቸው ነፃነት ሲሉ ሲገብሩ የኖሩ ጀግኖች እናቶች እና አባቶች ስለነበሩን ነው። ከ፸፬(ሰባ አራት) ዓመታት በፊት ፋሽስት ጣሊያንን ያንበረከኩት የዛሬው ትውልድ ወላጆች እና አያቶች፣ ከሁሉም የሚበልጠው የጽናታቸው ምንጭ፣ ለአገራቸው ነፃነት የነበራቸው ቀናዒነት ነበር። ነገር ግን «የእሣት ልጅ ዐመድ» ሆኖ፣ በእኛ ትውልድ ዘመን እነርሱ በብዙ ልፋት እና ትግል የገነቧት ኢትዮጵያ በመፈራረስ ሂደት ላይ ናት።
moresh
በአምሥቱ ዓመት የአርበኝነት ዘመን፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን «ዱሩ ቤቴ» ብለው የፋሽስት ጣሊያኖችን እና የእነርሱ ባንዳዎች የነበሩትን ከሃዲዎች ጥምር ጦር ተፋልመዋል። በኅዳር ወር ፲፱፻፳፯ ዓ.ም. ኦጋዴን ውስጥ ወልወል ወደተባለው የኢትዮጵያ ግዛት የፋሽስት ጣሊያን ወታደሮች ዘልቀው በፈጠሩት ትንኮሣ የተጀመረው ጦርነት፣ ከአምሥት ዓመታት በላይ ወስዶ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ቀዳማዊ ኃይለሥላሤ በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ወረራው ተቀልብሷል። በእኒያ አምሥት የአርበኝነት ዓመታት፣ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን፣ በተለይ ዐማሮች፣ በግፍ ተጨፍጭፈዋል። በአሁኑ የገንዘብ ስሌት ሲተመን በቢሊዮን ብሮች የሚገመት ንብረት ወድሟል። ውድ እና መተኪያ የሌላቸው ቅርሶች ተዘርፈዋል፣ ወይም እንዲወድሙ ተደርጓል። ይህ ሁሉ መስዋዕትነት የተከፈለው ክቡር የሆነውን የአገርን ነፃነት ለማስመለስ ነበር፣ ጀግኖቹ የዚያን ዘመን ኢትዮጵያውያን መስዋዕትነቱን ከፍለው አድርገውታል!

ከተለያዩ የታሪክ ድርሣናት እና መጻሕፍት ለማመሣከር እንደሚቻለው (ደጃዝማች ከበደ ተሰማ በ፲፱፻፷፪ ዓ.ም. «የታሪክ ማስታወሻ»፣ ዶ/ር ተወልደ ትኩዕ በ፲፱፻፺ ዓ.ም. «የኢትዮጵያ አንድነት እና ኢጣሊያ»፣ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ በ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. «የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983»፣ ገብረወልድ እንግዳወርቅ በ፪ሺህ ዓ.ም. «ማይጨው፣ የማይጨው ዘመቻና የጉዞ ታሪክ»፣ አምባሳደር ዘውዴ ረታ በ፪ሺህ፬ ዓ.ም. «የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት»፣ ፕሮፌሰር መሥፍን ወልደማርያም በ፪ሺህ፭ ዓ.ም. «መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ») ለማመሣከር እንደሚቻለው፣ በአምሥቱ ዓመት የፋሽስት ጣሊያን የወረራ ዘመን ከፍተኛውን መስዋዕትነት የከፈሉት አርበኞች በስፋት ይንቀሳቀሱ የነበሩት በተለይ፦ በሸዋ፣ በጎጃም፣ በጎንደር እና በወሎ ክፍለሀገሮች ነበር። ከእነዚያ ስመጥር የአርበኞች መሪዎች መካከል ለአብነት ያህል የሚከተሉት ይገኙበታል።

· በሸዋ፦ አቡነ ጴጥሮስ፣ መላከፀሐይ ኢያሱ (የልጅ ኢያሱ ልጅ እና የሸዋ አርበኞች መሪ፣ አበበ አረጋይን ራስ ብለው የሾሙ)፣ ራስ ደስታ ዳምጠው (በሲዳሞ ግንባር ያዋጉ እና በጉራጌ አውራጃ በፋሽስቶች ተማርከው የተገደሉ)፣ ራስ አበበ አረጋይ (መንዝ፣ ተጉለትና ቡልጋ፣ ምንጃር)፣ ራስ መስፍን ስለሺ፣ ደጃዝማች አበራ ካሣ (ሰላሌ)፣ ደጃዝማች አስፋው ወሰን ካሣ (ሰላሌ)፣ ደጃዝማች ወንደወሰን ካሣ (ሰላሌ)፣ ደጃዝማች ባልቻ ሣፎ (በጉራጌ)፤ ደጃዝማች ፍቅረማርያም አባተጫን፣ ደጃዝማች አውራሪስ (መሐል ሸዋ)፣ ደጃዝማች መንገሻ ወሰኔ (መሐል ሸዋ)፣ ደጃዝማች ፀሐዩ እንቆሥላሤ (መርሃቤቴ እና ሰላሌ)፣ ደጃዝማች ገረሱ ዱኪ (ጅባትና ሜጫ)፣ ደጃዝማች ከበደ ብዙነሽ (ጅባትና ሜጫ)፤ ደጃዝማች በቀለ ወያ (በጉራጌ)፤ ጄኔራል ጃጋማ ኬሎ፣ ልጅ ኃይለማርያም ማሞ፣ ወይዘሮ ሸዋረገድ ገድሌ፣

· በጎጃም፦ ራስ እምሩ ኃይለሥላሴ (የጎጃምን እና የጎንደርን ጦር መርተው በሽሬ ግንባር ያዋጉ)፣ ራስ ኃይሉ በለው (ሞጣ)፣ ቢትወደድ አያሌው መኮንን (ባህርዳር-አቸፈር)፣ ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ (አቸፈር እና አገው ምድር)፣ ደጃዝማች አበረ ይማም (ባህርዳር፣ አቸፈር እና ሜጫ)፣ ደጃዝማች ነጋሽ በዛብህ (ቡሬ ዳሞት)፣ ደጃዝማች ደስታ እሸቴ (ደጋ ዳሞት)፣ ደጃዝማች ኃይለኢየሱስ ፍላቴ (ደጋ ዳሞት)፣ ደጃዝማች በላይ ዘለቀ (ብቸና)፣ ደጃዝማች መንገሻ አቦዬ (ሞጣ፣ ትውልዳቸው አልቡኮ (ወሎ))፣ ቀኝጌታ ዮፍታሄ ንጉሤ፣ አአቶ ጌታሁን ተሰማ (በኋላ ሚኒስትር እና አምባሣደር)፤

· በጎንደር፦ ደጃዝማች ዮሐንስ እያሱ (የልጅ እያሱ ልጅ፣ እና የቤገምድር አርበኞች አስተባባሪ)፣ ቢትወደድ አዳነ መኮንን፣ ቢትወደድ ገሠሠ ረታ፣ ራስ ውብነህ (አሞራው) ተሰማ፣ ደጃዝማች ዳኘው ተሰማ (ጎንደር፣ ቤገምድር)፣ ደጃዝማች ብሬ ዘገዬ፣ ደጃዝማች ታደሰ ይማም፣ ደጃዝማች ጀምበሩ፣ ደጃዝማች ገብሬ ካሣ፣ ፊታውራሪ ሥዩም ነጋሽ፣ ፊታውራሪ ሽፈራው ጌታሁን(አባ ከንትር)፣ ፊታውራሪ አለማየሁ ቢተዋ (ጭልጋ)፤

· በወሎ፦ ደጃዝማች ኃይሉ ከበደ (በላስታ)፣

· በባሌ፦ ደጃዝማች በየነ መርዕድ፤

· በሐረርጌ (ኦጋዴን)፦ ግራዝማች (በኋላ ደጃዝማች) አፈወርቅ ወልደሰማዕት፤

· በኢሉባቦር፦ አቡነ ሚካኤል፤

በዚህ ዝርዝር ውስጥ ስማቸው ያልተካተቱ አያሌ አርበኞች አሉ። ለወደፊት እያጣራን በስፋት እንዘግብበታለን።

ከፋሽስት ጣሊያን ጦር ጋር ሲፋለሙ የነበሩት አብዛኞቹ ጀግኖች እናቶች እና አባቶች ዛሬ በሕይዎት የሉም። ከመቃብር በላይ የሚውል ሥራቸው ግን ለዘለዓለም በትውልድ ሲዘከር የሚኖር ነው። ለመሆኑ እኒያ ጀግኖች ዛሬ ከመቃብር ተነስተው የትግሬ-ወያኔ የሚያመሰቃቅላት አገራቸው ኢትዮጵያ ያለችበትን እጅግ አሣፋሪ የታሪክ ምዕራፍ ቢመለከቱ ምን ይሰማቸው ይሆን? መቼም በምንም ተዓምር የባንዶች ልጆች እና የልጅ-ልጆች የሆኑት እነ መለስ ዜናዊ፣ ስብሐት ነጋ፣ ወዘተርፈ የሚያፈራርሷት የኢትዮጵያ ሁኔታ ሐሴትን ሊያቀዳጃቸው በፍጹም እንደማትችል ማንም ጤነኛ አዕምሮ ያለው ሰው የሚገነዘበው ነው። ስለዚህ በእኛ ስንፍና እና ቸልተኝነት አገራችንን ለዚህ የታሪክ ውርደት ያበቃነው የአሁኑ ትውልድ፣ ለተተኪው ትውልድ የባሰ ችግር ከምናወርሰው፣ ቆም ብለን ያለፍንበትን የስህተት ጎዳና እንመርምር፣ ጊዜው ሣይጨልምብንም እናርመው!

ኢትዮጵያ በታማኝ እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ፀንታ ትኖራለች!

The post “የጀግኖች እናቶቻችንን እና አባቶቻችንን ፈለግ እንከተል!” – ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት appeared first on Zehabesha Amharic.

የአዲስ አበባ አስተዳደር ሰማያዊ ፓርቲ በመስቀል አደባባይ ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳያደርግ ከለከለ (ደብዳቤውን ይዘናል)

$
0
0

semayawi
• ‹‹ተቀባይነት የሌለው ተልካሻ ምክንያት ነው›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 9/2007 ዓ.ም መስቀል አደባባይ ላይ ለማድረግ ያቀደውን ህዝባዊ ስብሰባ እውቅና እንደማይሰጠው ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ ገልጾአል፡፡ አስተዳደሩ በላከው ደብዳቤ ‹‹መስቀል አደባባይ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት ከመሆኑም በላይ በርካታ የተከማዋ ነዋሪ የሚተላለፍበት እና የከተማው ነዋሪ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ተፅዕኖ የሚፈጥር›› ነው ሲል ለህዝባዊ ስብሰባው እውቅና እንደማይሰጥና ሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባውን መስቀል አደባባይ ማድረግ እንደማይችል ገልጾአል፡፡

በሌላ በኩል የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ አስተዳደሩ የሰጠው መልስ ‹‹ተቀባይነት የሌለው ተልካሻ ምክንያት ነው›› ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ኃላፊው አክሎም ‹‹አደባባዩ የተሰራው እንደዚህ አይነት ተግባራት ሊከናወኑበት ነው፡፡ ኢህአዴግ ሲጠራ ትራፊክ ተጨናነቀ ተብሎ አያውቅም፡፡ ሰማያዊ ሰልፍና ስብሰባ ሲጠራ ግን እንዲህ አይነት ተልካሻ ምክንያት ያቀርባሉ፡፡ በመሆኑም ይህን ተልካሻ ምክንያት ሰማያዊ ፓርቲ አይቀበለውም›› ብሏል፡፡

ከትራፊክ መጨናነቅ ባሻገር አስተዳደሩ ሰማያዊ ለሚያደርገው ህዝባዊ ስብሰባ የፀጥታ ኃይል ለመመደብ እንደሚቸገርም የገለጸ ሲሆን አቶ ዮናታን ተስፋዬ በበኩሉ ‹‹ለጥበቃ የለንም ያሉትን የፀጥታ ኃይል ንፁሃንን ለመደብደብ ሲያሰማሩ በተደጋጋሚ አይተናል፡፡ አሁንም የጥበቃ ኃይል የለንም የሚሉት ስብሰባውን ለማስተጓጎል ነው፡፡ ያኔ ግን ሰላማዊ ዜጎችን ለመደብደብ ይልኩታል፡፡ በመሆኑም የአስተዳደሩ ውሳኔ በምክንያት ያልተደገፈና ተቀባይነት የሌለው ነው›› ብሏል፡፡

ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ

The post የአዲስ አበባ አስተዳደር ሰማያዊ ፓርቲ በመስቀል አደባባይ ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳያደርግ ከለከለ (ደብዳቤውን ይዘናል) appeared first on Zehabesha Amharic.

ሰመጉ ጥቃት እየደረሰበት መሆኑን አስታወቀ

$
0
0

Semguኢሳት ዜና :-የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ( ኢሰመጉ) የአሁኑ ሰመጉ ሚያዚያ 26 ቀን 2007 ዓም ባወጣው መግለጫ በአዋሳና አዲስ አበባ በሚገኙ የድርጅቱ ፅህፈት ቤቶች ላይ ጉዳት እንደደረሰበት

አስታውቋል።

መንግስት በተለያዩ ወቅቶች ላይ በድርጅቱ ላይ አፍራሽ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን የጠቀሰው ሰመጉ፣ ሚያዚያ 24 ቀን 2004ዓም የሰመጉ የሃዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ በስራ ቀን ከጠዋቱ 4 ሰአት ላይ ተደፍሯል። ሰመጉ የጽ/ቤቱን የጠረጴዛ መሳቢያዎች ገንጥሎ

ሰነዶችን ሲበረብር እጅ ከፍንጅ የተያዘ ግለሰብ ለፖሊስ ተላልፎ ቢሰጥም፣ የክስ ሂደቱ በመታየት ላይ እያለ ግለሰቡ በዋስ ተለቋል በሚል ከአካባቢው እንዲሰወር ተደርጓል ብሎአል።

መጋቢት 21 ቀን 2007 ዓም የሃዋሳ ሰመጉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ግልጽ ባልሆነ መንገድ በሩ ተከፍቶ ተገኝቷል የሚለው መግለጫው፣ በውስጡ የሚገኙት የመዛግብትና የልዩ ልዩ እቃዎች መስቀመጫ ቁምሳጥኖችና የቢሮው ጠረጴዛ መሳቢያዎች ተሰብረዋል።

ብዛት ያላቸው የድርጅቱ መዝገቦችና የሂሳብ ሰነዶችም በስርአት ተቀምጠው ከነበሩበት ስፍራ ተነስተው በጠረጴዛውና በወለሉ ላይ ተበታትነው ተገኝተዋል። የድርጅቱ ማህተም ከተቀመጠበት ቦታ ተንስቶ ሌላ ስፍራ በመገኘቱ፣ ማህተሙ ለህገወጥ ተግባር ውሎ ይሆናል

የሚል ከፍተኛ ጥርጣሬና ስጋት ማሳደሩን የሰብአዊ መብት ተማጓቹ ድርጅት ጠቅሷል። ጉዳዩን የያዘው ፖሊስ ውጤቱን እስካሁን ለሰመጉ አላመለከተም።

መጋቢት 24 ደግሞ ከቀኑ 11 ሰአት አካባቢ አዲስ አበባ በሚገኘው የሰመጉ ዋና ጽ/ቤት የመኪና ማቆሚያ ስፍራ ላይ በነበረ የሰመጉ መኪና ላይ ከፎቅ ላይ ወደቀ የተባለ እቃ ጉዳት እንዳደረሰበት ገልጿል። ጉዳዩን ለፖሊስ ቢያመለክትም ምንም መልስ ሊያገኝ

አለመቻሉንም ገልጿል።

መንግስት በሃገሪቱ ውስጥ የሚካሄዱ ሰብአዊ መብቶችን የማስከበር እንቅስቃሴዎችን በአሉታዊ መንገድ መመልከቱ፣ እንቅስቃሴዎችንም በተለያዩ መንገድ ማዳከሙ እና ጭራሹ አፋኝ ህጎችን በማውታት የማጥፋት ሙከራ ማድረጉ ህጋዊና ጠቃሚ አሰራር አለመሆኑን

በተለያዬ ጊዜያት መግለጹን ድርጅቱ ጠቅሷል።

መንግስት የሰብአዊ መብት ተሟጋች አባሎቻቸውንና ሰራተኞቻቸውን ደህንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ግዴታውን እንዲወጣ ሰመጉ ጠይቋል።

ብቸኛው የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅት፣ በመላው አገሪቱ የነበረውን ጥንካሬ በገዥው ፓርቲ ተጽእኖዎች እንዲያጣ ተደርጓል። ድርጅቱ ላለፉት 24 አመታት የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ሲያጋለጥ መቆየቱ ከገዢው ፓርቲ ጋር እንዲላተም አድርጎታል። በአሁኑ ጊዜ

አብዛኞቹን የክልል ጽ/ቤቶች በገንዘብ እጥረት ምክንያት እንዲዘጋ በመደረጉ ፣ በፊት እንደሚያከናውነው ተከታታይ መግለጫውን ሲያወጣ አይታይም። ይሁን እንጅ በተወሰኑ ወራት የሚያወጣቸው መግለጫዎች አሁንም ገዢውን ፓርቲ እያስቆጡት መሆኑን ዘጋቢያችን

ገልጿል።

Source:: Ethsat

The post ሰመጉ ጥቃት እየደረሰበት መሆኑን አስታወቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የተያዙበት ሁኔታ ለህይወታቸው አስጊ ነው ተባለ

$
0
0

የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በከፍተኛ ህመም በመሰቃየት ላይ ሲሆኑ እስካሁን በዶክተሮች ለመጎብኘት አልቻሉም።
andargachew new picture
አያያያዛቸው የከፋ መሆኑን በማስመልከት የእንግሊዝ መንግስት አስቸኳይ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መጻፉንም ምንጮቻችን ገልጸዋል።

አቶ አንዳርጋቸው ያለፉትን ተከታታይ ወራት ጸሃይ የሚባል ነገር ሳያዩ ጨለማ ቤት ተዘግቶባቸው አሳልፈዋል; ከህመማቸው ጋር በተያያዘም ምግብ መመገብ በእጅጉ ቀንሰዋል።

በከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና ውስጥ የሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው፣ አያያዛቸው አስከፊ እንደሆነ በቅርቡ ለጎበኙዋቸው የእንግሊዝ አምባሳደር መናገራቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ይህንን ተከትሎም የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ጠንከር ያለ ደብዳቤ መጻፉን የአዲስ አበባ ምንጮች ገልጸዋል። የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ በአፋጣኝ የማይለወጥ ከሆነ፣ በህይወታቸው ላይ ያልተጠበቀ አደጋ ሊፈጠር እንደሚችል ያስጠነቀቁት የእንግሊዝ ባለስልጣናት፣ አቶ አንዳርጋቸው የኮንሱላር ድጋፍ እንዲያገኙ፣
በመደበኛ እስር ቤት ውስጥ እንዲታሰሩና በጠያቂዎች እንዲጎበኙ ፣ ሃኪሞች እንዲያዩዋቸውና ሰብአዊ መብታቸው እንዲከበር ደብዳቤ መጻፋቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

ገዢው ፓርቲ ከአቶ አንዳርጋቸው የረባ መረጃ ለማግኘት ባለመቻሉ_የስነ ልቦና ጫና በማሳረፍና ህክምና በመከልከል ለመጉዳት ማሳቡን ምንጮች ገልጸዋል።

የእንግሊዝ ባለስልጣናት በሂደት ስለሚወስዱት እርምጃ ግልጽ ባያደርጉም፣ ጉዳዩን በቀላሉ እንደማያዩት ለኢህአዴግ ሹሞች እንደገለጹላቸው ታውቋል።

አቶ አንዳርጋቸው በየመን የጸጥታ ሃይሎች ተይዘው ለኢህአዴግ የጸጥታ ሃይሎች ተላልፈው ከተሰጡ በሁዋላ፣ ገዢው ፓርቲ ሁለት ጊዜ በቴሌቪዥን አቅርቧቸዋል። ተቆራርጦ የተላለፈውን ቪዲዮ ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ትችት ሲቀርብብት ቆይቷል።

ኢህአዴግ አቶ አንዳርጋቸውን ህዝብ ሊጎበኛቸው በሚችል እስር ቤት አለማሰሩና ሰብአዊ መብታቸውን ሁሉ መግፈፉ የገዢውን ፓርቲ የፍርሃትና የበቀል ደረጃ፣ እንዲሁም ራሱ ላወጣው ህግ እንኳን የማይገዛ መሆኑን የሚያሳይ ነው ተብሏል።

The post አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የተያዙበት ሁኔታ ለህይወታቸው አስጊ ነው ተባለ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 2784 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>