Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all 2784 articles
Browse latest View live

ገዥው ፓርቲ ኦሮሚያ ውስጥ ምርጫውን ጀምሮታል ተባለ

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ገዥው ፓርቲ ምርጫውን ከአሁኑ እንደጀመረው ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተለያዩ የኦሮሚያ ክፍሎች ካድሬዎች መራጮችን በጋንታ፣ በሴልና በኔትወርክ እያደራጁ ‹‹ኦህዴድ/ኢህአዴግን መርጫለሁ›› በሚል እያስፈረሙና ፎርም እያስሞሉ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በጋንታ፣ በሴልና በኔትወርክ ተደራጅተው ‹‹ኦህዴድን መርጠናል›› ብለው እንዲፈርሙ የተደረጉ ዜጎች ፎርሙን ከሞሉበት ቀን ጀምሮ የምርጫ ካርዳቸውን ለጋንታ፣ ሴልና ኔትወርክ መሪዎቻቸው እንደሚሰጡ ታውቋል፡፡ የጋንታ፣ የሴልና የኔትወርክ መሪዎችም ኢህአዴግን ከአሁኑ መርጠዋል ተብለው የተደራጁ ዜጎችን ስምና የምርጫ ካርድም ለኦህዴድ/ኢህአዴግ ከፍተኛ ካድሬዎች እንደሚሰጡ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡
Oromia
ካድሬዎች ግንቦት 16 ቀን በፊት የምርጫ ካርዳቸውን ለጋንታ፣ ለሴልና ለኔትወርክ መሪዎች የሚሰጡትን ዜጎች ቤት ለቤት እየዞሩ እያስፈረሙ እንደሚገኙ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ በጋንታ፣ ሴልና ኔትወርክ ተደራጅተው ኦህዴድ/ኢህአዴግን ከአሁኑ እንደመረጡ በፊርማቸው አረጋግጠዋል የተባሉት ዜጎች ግንቦት 16/2007 ዓ.ም በሚደረገው ምርጫ እንደማይሳተፉ የታወቀ ሲሆን አብዛኛዎቹ በግዳጅና በማስፈራሪያ እየሞሉ እንደሚገኙ ተገልጾአል፡፡

የጋንታ፣ የሴልና የኔትወርክ እንዲሁም የመራጮች ስምና ፊርማቸው እየሰፈረበት ከግንቦት 16 በፊት እንደመረጡ ተደርጎ ዜጎች እንዲሞሉት የሚደረገውና ከስር የሚታየው ቅጽ ካድሬዎች በአርሲ ዞን በቆጅ ወረዳ ቤት ለቤት ሲያስሞሉ የተገኘ ነው፡፡

The post ገዥው ፓርቲ ኦሮሚያ ውስጥ ምርጫውን ጀምሮታል ተባለ appeared first on Zehabesha Amharic.


እኔ እንዲህ አስባለሁ – [ለወንድሜ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት] –ዶክተር በድሉ ዋቅጂራ

$
0
0

እኔ እንዲህ አስባለሁ፡፡

ለወንድሜ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

የአንተን ጽሁፍ ሀሳብ መነሻ አድርጌ፣ ‹‹ጀማል ማንስ ቢሆን?›› በሚል ርእስ ስር ያነሳሁትን ሀሳብ ተመርኩዘህ፣ የጻፍክልኝን ሶስት አብይ ጥያቄዎች የያዘ አጭር ጽሁፍ አነበብከት፡፡ የዚህ ጽሁፌም አነሳስ እነዚያን ጥያቄዎች ለመመለስ መሞከር ነው፡፡
bedilu wakjira
የአንድን ሰው ማንነት ከባለቤቱ ውጭ ያለ ሰው ለእርሱ በሚመስለውና በሚፈልገው መንገድ ለመቀየር መብት አለውን?
በአጭሩ መብት የለውም፡፡ እኔም በቀደመው ጽሁፌ ያልኩት፣ ‹‹ዳንኤል ልብ እንድትልልኝ የምፈልገው፣ አንተ የጻፍከው እውነት አይደለም ማለቴ እንዳልሆነ ነው፤ እኔ የምለው፣ ‹እኔ እውነት ብዬ የተቀበልኩት (አንተ ሀሰት ነው ያልከው) ሀሰት ቢሆን እንኳን፣ አሁን ባለንበት ሁኔታ ከእውነቱ የበለጠ ዋጋ አለው›› ነው፡፡ ስለዚህ የእኔ ሀሳብ የተሰነዘረው ጉዳይ (ታሪኩ) ማህበረሰቡ ውስጥ ከሚያሳድረው ስለምንና ባለንበት ስሱ ሁኔታ ከሚያሳርፈው ተጽእኖ አንጻር እንጂ፣ የሰማእቱን ማንነት (ዜግነቱን፣ ጎሳውን፣ አስተዳደጉን፣ ሀይማኖቱን) በማስረጃ አስደግፌ፣ እውነት ውሸት ብዬ ለመከራከር አይደለም፤ በዚህ ጉዳይ ላይ እንኳን ለአደባባይ ሙግት፣ ለማኪያቶ ወግ የሚበቃ እውቀትም ሆነ መረጃ የለኝም፡፡

በዚህ ረገድ የእኔ ነጥብ፣ በዚህ ሀይማኖትን ተመርኩዞ በደረሰብን ጉዳት፣ ምንም እንኳን አይ.ኤስ ሙስሊሞችን ባይወክልም፣ የገዳዮቹ ሙስሊምነትና እራሳቸውን ትክክለኛ የእስልምና ተከታይ አድርጎ ማየት፣ ሙስሊም ገዳይ ክርስቲያን ተገዳይ የሚል ስሜት መፍጠሩ አይቀርም፡፡ አብዛኛው ህዝብ ደግሞ (የከተማውም ቢሆን) እንደእኔና እንዳንተ ባለቻናል ቲቪ የለውም፤ የኢንተርኔቱንም ተደራሽነት የምናየው ነው፡፡ እና የመጀመሪያው የጀማል ታሪክ ይህንን ሀሳብ የሚያፈርስ በመሆኑ ብዙዎችን አጽናንቷል፤ ቢያንስ በእኔና በዙሪያዬ ስላሉት ሰዎች ስሜት እማኝ ነኝ፡፡ ታሪኩ ፈጣራም ቢሆን እንኳ የፈጠረው በጎ መንፈስ ነው፡፡ እስቲ የጀማልን ኤፍሬምነት ከገለጥክበት ጽሁፍ ስር ያለውን አስተያየት አስተውል፤ በአብዛኛው ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች ወገን ለይተው የሚነታረኩበት ነው፡፡ እኔንም ጣልቃ ገብቼ ሀሳቤን እንድገልጥ ያደረገኝ የኸው ነው፡፡ የአንተም ሆነ የብዙዎች የሀሳብህ ተጋሪዎች ነጥብ፣ ‹‹እውነትና ታሪክ ለምን ይደበቅ?›› የሚል አስተያየት ነው፡፡ እኔ ይህ ድርጊት ከመቸው ታሪክ እንደሆነ፣ ከመቼው ተደብቆ የመቅረቱ አደጋ ሰዎችን እንዳሳሰበ ይገርመኛል፤ ጎበዝ ገና እኮ የሀዘን ድንኳን አልፈረሰም፡፡ ታሪክን የመዘገብ፣ ትላንታችንን ቆፍሮ እውነትን መግለጥ ለሚሻ፣ የሰው ዘር መገኛ፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት የሆነች ሀገራችን ያሏት የታሪክ መዛግብት ቢቆጠሩ፣ በክፍለ ዘመን አንድ ወይም ሁለት ቢደርሱ ነው፡፡ ወንድሜ ዳንኤል በዚህ የተነሳ ነው ህሊናዬ፤ ‹‹ታሪክ እንዳይቀበር . . .›› የሚለውን ምክንያት አልቀበል ያለኝ፡፡

ደግሞ እንዲህ በሀዘን ስሜት ውስጥ ተሁኖ የተጻፈ ታሪክ በስሜት የመበረዝ እድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ ይቅርታ አድርግልኝና ወንድሜ ዳንኤል፣ ከዚህኛው ጽሁፍህ ቀደም ብሎ፣ ‹‹ጎበዝ እየተስተዋለ እንጂ. . ›› በሚል፣ የጻፍከውን ጽሁፍ ከዚህኛው ሳስተያየው፣ ህሊናዬ ስሜታዊነትህን አግዝፎ፣ መረጃህን እንድጠራጠር ነግሮኛል፡፡ እስቲ ከቀደመው ጽሁፍህ ልጥቀስ፣

‹‹ . . . ከኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ጋር ጀማል የተባለ ሶማልያዊ ሙስሊም ክርሲቲያኖችን እረዳለሁ ብሎ፣ አብሮ ተሰውቷል የሚለውን መረጃ ለመቀበል ያስቸግራል፡፡ በመጀመሪያ ሶማልያውያንን ለጥያቄ አይቀርቧቸውም፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ጓደኞቼን ትቼ አልሄድም ስላለ፣ ና አብረሀቸው ሂድ ብሎ አስተያየት የሚያደርግ ቡድን አይደለም፡፡ በሊላ በኩል ተጓዦቹ ሲያዙ የሊቢያ ወታደሮች እንደያዝዋቸው እንጂ፣ አይኤስኤስ መሆናቸውን የሚያውቁበት እድል የለም፡፡ የለበሱትም የወታደር ልብስ ነው፡፡ . . . .በዚህ ሁሉ ነገር ጀማል ኢትዮጵያዊ ክርስትያኖችን ለመርዳት እድል የሚያገኝበት መንገድ የለም፡፡ ቢፈልግ እንኳን፡፡ . . . . እንኳን ለመታረድ አብሮ ለመቆየት እድል የለውም፡፡…››

እንግዲህ ወንድሜ ዳንኤል አንተ፣ ስለአሸባሪው ቡድን ባህሪ፣ ስለአካባቢው ሁኔታ አገናዝበህ፣ ንባብና እውቀትክ ተጠቅመህ፣ የጀማልን እውነትነት መቀበል ያስቸግራል ያልከው አስቀድመህ፣ የኤፍሬምን መረጃ ከማምጣትህ በፊት ነው፡፡ በሁለቱ ፅሁፎች መካከል ያለው ልዩነት፣ የመጀመሪያውን ጥርጣሬህና ግምትህን ሁለተኛው ላይ ኤፍሬምን መረጃ አድርገህ ለማስረገጥ መሞከርህ ነው፡፡ በነገራችን ላይ አንድ ኤፍሬም የሚባል ሰማእት መኖሩ ከጀማል ጋር እንዴት እንደሚገናኝ አልገባኝም (ዝርዝሩን የሚቀጥለውን ጥያቅ ስመልስ እመለስበታለሁ)፡፡ እና ወንድሜ ዳንኤል እውነትን ለመግለጥ የሚለውን ሀሳብህን ያልተቀበልኩት በቀደመው የግል ትንታኔህና፣ እውነት ባልከው መካከል ምንም ልዩነት ባለመኖሩም ጭምር ነው፡፡

ያልነጠረና ውሸት የሆነ ታሪክን ለምን እናቆየዋለን? በዘመናችን ለምን አናጠራውም?
እውነት ነው ውሸትን ታሪክ ብሎ ማቆየት ይቅርና እውነት ብሎ መቀበል በጎ አይደለም፡፡ ግን በዚህ ጉዳይ ላይ እውነቱ ምንድነው? የቱ ነው?እሲቲ ጉዳዩን በተጠየቅ እንፈትሸው፡፡

መነሻው፣ ‹‹ጀማል የሚባል ሙስሊም የክርሲቲያኖችን መገደል ተቃውሞ አብሮ ሞተ›› የሚለው ነው፡፡ ማፍረሻ ተደርጎ የቀረበው ሀሳብ ጀማል የሚባል ሰው የለም፤ ጀማል የተባለው ኤፍሬም ነው የሚል ነው፡፡

ተጠየቅ 1፡ ኤፍሬም የሚባለው ኤርትራዊ ሰማእት እንደምን ከጀማል ጋር ሊያያዝ ቻለ? ይህ ሊሆን የሚችልበት መንገድ ሁለት ነው፡፡ አንድ፣ የኤፍሬም ፎቶ ጀማል ነው ተብሎ ተቀምጦ ከሆነ፡፡ ሁለት፡ ለጀማል የተሰጠው ታሪክ የኤፍሬም መሆኑ ከተረጋገጠ፡፡ ኤፍሬም ክርስቲያን ነው፤ ሰማእት የሆነው እንደሁሉም ሰዎች ክርስቲያን ስለሆነ እንጂ የሌሎቹን መገደል ተቃውሞ አይደለም፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ ታሪካቸው ስለማይመሳሰል ሁለተኛው ምክንያት ውድቅ ነው፡፡ ችግሩ የመጀመሪያው (የፎቶ መሳከር) ከሆነ ደግሞ፣ ይህ የሚያረጋግጠው ጀማል የተባለው ኤፍሬም መሆኑን፣ የሰማእታቱን ማንነት መለየት ላይ ችግር መፈጠሩን እንጂ፣ ጀማል የሚባል ሰው አለመኖሩን አያረጋግጥም፡፡ ስለዚህ በምንም መንገድ የኤፍሬም ማንነት መረጋገጥ የጀማልን አለመኖር አያረጋግጥም፡፡ በጀማል አለመኖር እርግጠኛ መሆን የሚቻለው የሰላሳውም ሰማእታት ማንነት ተለይቶ፣ ከመካከላቸው ጀማል የሚባል ሰው ከሌለ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ ዲያቆን ዳንኤል ከጻፍከው ውስጥ እውነቱ የኤፋሬም መኖር ብቻ ነው፡፡ ገና ማንነታቸው ያልተረጋገጠ በርካታ ሰማእታት እያሉ ‹‹ጀማል የሚባል ሰው መኖሩ ውሸት ነው ብሎ መደምደም አይቻልም፡፡ ካልንም ከግምት ውጭ እውነት ሊሆን አይችልም፡፡ ስለዚህ ወንድሜ ዳንኤል፣‹‹ ያልነጠረ ውሸት የሆነ ታሪክ ለምን እናቆያለን?›› ብለህ ለጠየቅከኝ መልሴ፣ የጀማል ታሪክ መቶ በመቶ ውሸት መሆኑ የሚረጋገጠው ሁሉም ሰማእታት ተለይተው ሲታወቁ ብቻ ሆኖ ሳለ ለምን አሁን እርግጠኛ ሆነህ ትናገራለህ? ችኮላው ምንድነው? የኤፍሬም ማንነት ጊዜውን ጠብቆ እንደተገለጠው፣ ሁሉም እስኪረጋገጥ መጠበቅ አይሻልም? ይህ ግን የኤፍሬምን ማንነት ስለአበሰርከን ያለኝን አድናቆት አይቀንሰውም፡፡

3 .የኢትዮጵያውያን የሙስሊሞችና ክርሲቲያኖች የፍቅርና የመግባባት ታሪክ በውሸት ላይ ለምን ይመሰረታል? ሰብአዊነትን በእውነት ላይ እንጂ በውሸት ላይ ለምን እንመሰርተዋለን?

ለዚህ የምሰጠው መልስ አጭር ነው፤ ወንድሜ ዳንኤል የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችና ክርሲቲያኖች የፍቅርና የመግባባት ታሪክ ለምን በውሸት ላይ ይመሰረታል ያልከው፣ የሁለቱን ህዝቦች የአብሮነት ታሪክ ዛሬ ‹‹ሀ›› ብለም መሰረት ልንጥልለት የተዘጋጀን ያስመስለዋል፡፡ የሁለቱ ህዝቦች ታሪክ መሰረቱን ከጣለ አይደለም፣ ጣራውን አልብሶ ካጠናቀቀ ክፍለ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡ አሁን የእኛ ትውልድ በዚያ የፍቅርና መተሳሰብ ቤት ውስጥ እየኖረ ነው፡፡ እና የጀማልን ትርክት ለኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችና ክርሲቲያኖች የፍቅርና የመግባባት ታሪክ መሰረት አድርጎ ማሰብ፣ ከልቤ ነው የምልህ፣ እንዳንተ ከፍተኛ የሀይማኖትና ታሪክ እውቀት ካለው ሰው የመጣ መሆኑ አስገርሞኛል፡፡

ሰብአዊነትን በእውነት ላይ እንጂ በውሸት ላይ ለምን እንመሰርተዋለን? ላልከው፣ የሰብአዊነት መሰረቱ እውነት ወይም ውሸት አይደለም፡፡ የሰብአዊነት መሰረቱ ሰው ሆኖ መፈጠር ብቻ ነው፡፡

እንደ ማስገንዘቢያ፤

የሰው ልጅ ነጻነት የመጨረሻው መገለጫ ኅሊና ነው፡፡

ወንድሜ ዳንኤል፣ እንዳነበብከው በአንባቢዎቻችን ከተሰጡት አስተያየቶች እጅግ የሚበዙት ወገናዊነትን መሰረት ያደረጉ፣ ስሜታዊነት የተንጸባረቀባቸው ናቸው፡፡ ይህንን አንተም ልብ ያልከው ይመስኛል፡፡ ለካ በጎሳ፣ በፓርቲ፣ በወንዝ ብቻ ሳይሆን፣ በሀሳብም እየተቧደንን ነው፡፡ ይህንን ዝም ብዬ ማለፍ አቃተኝና ነው እዚህ ላነሳው የወደድኩት፡፡

የሰው ልጅ ነጻነት የመጨረሻው መገለጫ ኅሊና ነው፡፡ የአንድ ሀገር ዜጎች፣ የአንድ ዘር ውላጆች፣ የአንድ እናትና አባት ልጆች ልንሆን እንችላለን፡፡ በመሆኑም የሀገሩ ህግ፣ የጎሳው ልማድና ደንብ፣ የምንከተለው ሀይማኖትና የቤተሰባችን የአስተዳደግ ሁኔታ በየደረጃው ሊጫነን ይችላል፤ በዚህ ሁሉ ተጽእኖ መሀል የተለየን ነጻ ሰብአዊ ፍጡር መሆናችንን የሚያረጋግጥልን ህሊናችን ነው፡፡ ህሊናችን ነገሮችን በራሳችን መንገድ እንድንመረምር ሙሉ ነጻነት ይሰጠናል፡፡ የአንድ ሰው ሀሳብ ከሀሳባችን ጋር ሲሰምር እንደግፈዋለን፤ ሲቃረን ደግሞ ሀሳቡን በሀሳብ እንሞግታለን፡፡ አለመታደል ሆኖ እኛ በዚህ በኩል ብዙ ይቀረናል፡፡ ብዙዎቻችን የጎሳችንንና የሀይማኖታችንን ተጽእኖ አልፈን ከህሊናችን የማሰብ ነጻነት ጋር አልተገናኘንም፡፡ አሁን እኔና አንተ ውይይት ላይ እንኳን ብትመለከት፣ እኔ ያንተን ሀሳብ ስላልተቀበልኩ፣ ሙስሊምና ፕሮቴስታንት መሆኔን እርግጠኛ ሆነው ሀሳባቸውን ሳይሆን ስድባቸውን የገለጹ አሉ፡፡ የአንተንም ሃሳብ ከእስልምና ጥላቻ ጋር አያይዘው ዘለፋ የጻፉ ብዙዎች ናቸው፡፡ ለምን እንዲህ አደረጉ ማለት አይቻልም፤ ይህ በሁለት ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ አንደኛው፣ ሀሳቡ ካንተ ወይም ከእኔ ሀሳብ የሰመረለት ሰው፣ ለሚቃረኑት ሀሳቦች የሚያቀርበው ስድብና ማንቋሸሽ ነው፡፡ ይህ ሰው የማያውቀው የሌላን ሰው ሀሳብን ማክበርንና ሀሳብ ላይ መሟገትን ነው፡፡ ገዢዎቹ በአንባገነንነት፣ ማህበረሰቡና ቤተሰቡ በ‹‹ተው! ይህን አታድርግ›› ሲሰድቡትና ሲያበሻቅጡት አሳድገውታልና እሱም ከሀሳብህ ተሻግሮ አንተን ይሰድብና ያበሻቅጥሀል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ አይነቱ ሰው የራሱ ሀሳብ አለው፤ የቸገረው ተግባቦቱ ነው፡፡ ሁለተኛው አይነት ሰው የራሱ ሀሳብ የለውም፤ የሚያስበው እንደአንድ ነጻ ሰብአዊ ፍጡር ሳይሆን፣ በቡድን ነው፡፡ እንደ እንድ ሀገር ዜጋ፣ እንደእንድ ጎሳ አባል፣ እንደአንድ ፓርቲ አባል፣ እንደአንድ ሀይማኖት ተከታይ . . ወዘተ. ያስባል፡፡ እና በምንም መንገድ ከነዚህ ቡድኖች ፍላጎት ጋር የተቃረኑ ሀሳበችን አይቀበልም፤ እንዲያውም መደፍጠጥና ማጥፋትን ያስቀድማል፡፡ በዚህ የተነሳ ይህ ቀድሜ ከጠቀስኩት የበለጠ ለለውጥና መሻሻል እንቅፋት ይሆናል፡፡

የአንድ ማህበረሰብ ጥንካሬና እድገት ከግለሰባዊ ሰብአዊ ነጻነቱ ጋር እጅጉን የተቆራኘ ነው፡፡ የማሰብ ነጻነት ሁለንተናችንን የመመርመር ነጻነት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ብዙ የሚበጁና የማይበጁ ሀሳቦች ወደ አደባባይ ወጥተው ውይይት እንዲደረግባቸው እድል ይሰጣል፡፡ ያን ጊዜ በሰለጠነ መንገድ በሀሳብ ላይ የመወያየት ባህል ያዳበረ ማህበረሰብ፣ የሚበጀውን ሀሳብ እያዳበረ ያድጋል፤ በበጎ ይለወጣል፡፡ እንደእኛ ያለው የማሰብ ነጻነቱን ያላስከበረ፣ የመወያየት ባህሉን ያላዳበረው ደግሞ፣ አዲስ ሀሳብ ብቅ ባለ ቁጥር አሳቢውን ጭምር እየኮረኮመ ባለበት ይረግጣል፤ አንዳንዴም ይዘቅጣል፡፡ እኔ እዚህ ላይ የምለው ነገር ‹‹ሰው የለስላሳ ጠርሙስ ወይም፣ በአንድ ፋብሪካ የተመረተ የሸራ ጫማ አይደለም!›› ነው፡፡ ሰው ተመሳሳይ ሊሆን አይችልም፡፡ 80 (?) ሚሊየን ህዝብ በአንድ ወይም በሁለት ሀሳብ ላይ ይስማማ ማለት እንዴት ይቻላል? ማንም ማንንም ‹‹እንዲህ አስብ›› ሊለው አይችልም፡፡ ፈጣሪም እኮ አላደረገውም! አዳምና ሄዋንን ሲፈጥርና ‹‹አትብሉ›› ሲላቸው እንኳ ትእዛዙን እስከመጣስ የሚያደርስ ህሊናዊ ነጻነት ነበራቸው፡፡ አይገርምም! እና እባካችን ሀሳብ ላይ የመወያየት ባህላችንን እናዳብር፡፡

ቸር እንሰንብት!

The post እኔ እንዲህ አስባለሁ – [ለወንድሜ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት] – ዶክተር በድሉ ዋቅጂራ appeared first on Zehabesha Amharic.

ቅዱስ ሲኖዶስ: በሊቢያ ክርስቲያን በመኾናቸው የተገደሉ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች እና የግብጽ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ‹‹የዘመኑ ሰማዕት›› እንዲባሉ ወሰነ፤ ‹‹የ፳፩ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሰማዕታት›› በመባል በአንድነት ይታሰባሉ!!!

$
0
0
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከሚያዝያ ፳፯ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. የመክፈቻ ጸሎት ሥነ ሥርዐት ጀምሮ ለአራት ቀናት ያካሔደውን የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ኹለተኛ ዓመታዊ ቀኖናዊ ጉባኤ ሲያጠናቀቅ ባወጣው ባለዐሥራ አንድ ነጥቦች መግለጫው÷ በሊቢያ ራሱን እስላማዊ መንግሥት(ዳኢሽ) እያለ የሚጠራው ዓለም አቀፍ አሸባሪ ቡድን ስለ ክርስቲያንነታቸው በግፍ እና በአሠቃቂ አኳኋን የገደላቸውን ኢትዮጵያውያን እና ግብጻውያን ኦርቶዶክሳውያን የሰማዕትነት ሥያሜ በመስጠት በሰማዕትነት ክብር ማክበሩን አስመልክቶ፣ ተከታዮቹን ኹለት ዐበይት ውሳኔዎች ማሳለፉን ዛሬ፣ ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. አስታውቋል፡-
  1. ምንም ጥፋት እና በደል ሳይኖርባቸው ክርስቲያኖች በመኾናቸው ብቻ በሊቢያ ሀገር አይ ኤስ በተባለ የአሸባሪ ቡድን በግፍ እና በሚዘገንን ኹኔታ የተገደሉ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች እና የግብጽ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን በተመለከተ ቋሚ ሲኖዶስ ቀደም ሲል በሟቾቹ መንፈሳዊ ሕይወት ላይ ተወያይቶ ባቀረበው ሐሳብ መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ያለውን ኹኔታ በጥልቀት ከተረዳ በኋላ ሟቾቹ የዘመኑ ሰማዕት እንዲባሉተስማምቶ ወስኗል፡፡

the synod canonize ethiopian and coptic martyrs

 

ethiopian-and-coptic-christians

የኢትዮጵያ እና የግብጽ አኃት አብያተ ክርስቲያን ቅዱሳን ሲኖዶሶች በሰማዕትነት ክብር ያከበሯቸው 30 ኢትዮጵያውያን እና 21 ግብጻውያን ኦርቶዶክሳውያን የ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታ

 

2. እንዲኹም እንደ ኢትዮጵያውያን አቆጣጠር ሚያዝያ ፲፩ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. በሊቢያ የተሠዉት 30 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች ልጆቻችን እና እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር የካቲት 15 ቀን 2015 በሊቢያ የተሠዉት 21 የኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባላት ክርስቲያኖችበኹለቱም አብያተ ክርስቲያናት ሲኖዶስ የሰማዕትነት ክብር የተሰጣቸው ስለኾነ፣ የኹለቱ አኃት አብያተ ክርስቲያናት የ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታት ተብለው በአንድነት እንዲታሰቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ተስማምቷል፡፡
3. በልዩ ልዩ ምክንያት ከኢትዮጵያ ሀገራቸው ወጥተው በባዕድ ሀገር የሚገኙትንና ወደ ሀገራቸው በመመለስ ላይ ያሉትን ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን ከማንኛውም ጥቃት ለመከላከል እና ለማቋቋም ቤተ ክርስቲያናችን መንግሥት ከሚያደርገው ጥረት ጋራ በመቀናጀት አስፈላጊውን ኹሉ እንድታደርግ፣ ይህን በተመለከተ ጉዳዩን የሚከታተል ኮሚቴ፣ የቤተ ክርስቲያናችን የልማት እና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽንም ርዳታ ሰጪዎችንም በማስተባበር ሓላፊነቱን ወስዶ በንቃት እና በትጋት እንዲሠራ ጉባኤው ወስኗል፡፡

The post ቅዱስ ሲኖዶስ: በሊቢያ ክርስቲያን በመኾናቸው የተገደሉ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች እና የግብጽ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ‹‹የዘመኑ ሰማዕት›› እንዲባሉ ወሰነ፤ ‹‹የ፳፩ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሰማዕታት›› በመባል በአንድነት ይታሰባሉ!!! appeared first on Zehabesha Amharic.

አሁንም የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በደህንነቶች እየታደኑ እየታሰሩ እየተደበደቡ ነው

$
0
0

 

መንግስት ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አይ ኤስ አይ ኤስን ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ላይ የተነሳበትን ተቃውሞ ሰበብ በማድረግ ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን እያደነ መያዙን ቀጥሏል፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን በየመስሪያ ቤትና መኖሪያ ቤታቸው እያደነ ሲይዝ የቆየ ሲሆን ዛሬ ሚያዝያ 30/2007 ዓ.ም የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ቢሴ ብርሃኑ መኖሪያ ቤቱ አካባቢ ተይዞ ታስሯል፡፡ በአሁኑ ወቅት አዲስ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ ይገኛል፡፡
67በምስራቅ ጎጃም አስተባባሪና የደብረማርቆስ ዕጩ የሆነው ሳሙኤል አወቀ፣ በደቡብ ጎንደር ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ አለማየሁ አደመና ደብረማርቆስ የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነችው የሀሰብ ጌታቸው ላይ የተፈፀመባቸው ድብደባ ይህን ይመስላል፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

The post አሁንም የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በደህንነቶች እየታደኑ እየታሰሩ እየተደበደቡ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

የለውጥ ሃይሎችን አፍሶ በማሰር እና በማሳደድ ስር ነቀሉን የለውጥ አብዮት ማስቆም አይቻልም

$
0
0

metemaበሃገራችን ውስጥ ለይስሙላ በወያኔ የተጠራውን ምርጫ በመንተራስ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያጣው የወያኔ ስርአት የለውጥ ሃይሎችን እያፈሰ በማሰር እና በማሳደድ ላይ መሆኑ ባለፉት ሳምንታት እየተመለከትን ነው::የወያኔ አምባገነን ጁንታ በጠራው የጸረ አይሲስ ሰልፍ አሳቦ የተቃዋሚ ሃይሎች አባላትን በተለይ የሰማያዊ ፓርቲ የለውጥ ሃይሎችን እንዲሁም የተለያዩ የለውጥ ፈላጊ ሃይሎችን ከየመንገዱ እየለቀመ እያፈሰ በማሰር ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ የማጎሪያ ካምፖች እያከማቸ ይገኛል:እንዲሁም መንግስታዊ ሽብርተኝነትን በመሸሽ የሚሰደዱ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ በገሃድ እየታየ ነው::

በአዲስ አበባ እና በክፍለ ሃገር ከተሞች ምርጫውን ተከትሎ ግርግር ያነሳሉ ሕዝባዊ አመጽ ይመራሉ ያስተባብራሉ የተባሉ ወጣቶች ታፍሰው የታሰሩ በአውቶብስ እና በጭነት መኪና ተጭነው ከየእስር ቤቱ ከከተሞች ክልል ውጪ ባሉ የማጎሪያ ካምፖች በመውስድ ላይ መሆኑን ሲታወቅ ገና ያልተጫኑ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች በየእስር ቤቱ እንደሚገኙ ጉዳዩን እየተከታተሉ የሚገኙ የገለጹ ሲሆን የለውጥ ሃይል የሆኑ ወጣቶችን አፍሶ አስሮ እና አሳዶ ስር ነቀል የሆነውን የለውጥ አብዮት ማስቆም እንደማይቻል ወያኔዎች በፍጹም አልተረዱትም::እንዲሁም ከምርጫው ጋር በተያያዘ አፈሳውን እና መታሰሩን በመፍራት የተለያዩ ክፍለሃገር ነዋሪዎች ወደ ጎረቤት ሃገሮች እየተሰደዱ መሆኑ ከየአከባቢው የሚወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ::

ምርጫውን ተከትሎ የስል ነቀል አብዮት አመጽ ያሰጋው ወያነ ህዝቡ አንድነቱን በማሳየት በአደባባይ ተቃውሞውን መግለጹ ከፍተኛ ስጋት ላይ እንደጣለው ራሱ እየመሰከረ ባለበት ባሁኑ ወቅት የምርጫ ካርዶችን አምጡ በማለት በማስገደድ ላይ ይገኛል::ወያኔ ማንም እንደማይመርጠው በማወቁ ያለው እድል የመሳሪያ ሃይል ተጠቅሞ በአንድነት የተነሳበትን ሕዝብ ማዳከም ሌላው አላማ ቢሆንም አንድ ለአምስት ብሎ ከዚህ ቀደም ያደራጀው እንዳልሰራለት እና አሁንም በሌላ መንገድ ያንኑ አንድ ለአምስት የሚለውን አደረጃጀቱን ለምርጫው ለመጠቀም እየሰራ መገኘቱ የለውጥ ሃይሎች የትግል ውጤት ምን ያህል እንዳፍረከረከው በተግባይ እየታየ ነው::ይህንንም የለውጥ ሃይሎች እንቅስቃሴ በመስጋት በከፍተኛ ደረጃ ወጣቶችን በማፈስ በማሰር እና በማሳደድ ለማሸማቀቅ ቢሞክርም ቀሪው የህብረተሰብ ክፍል ከንፈሩን በመንከስ ወያኔን ሊበቀለው በዝግጅት ላይ መሆኑን በተግባር አንድነቱን አጠናክሮ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል::ወጣቱን ሃይል በማሰር እና በማሳደድ ስር ነቀሉን የለውጥ አብዮት ማስቆም አይቻልም::

‪#‎Miniliksalsawi‬

The post የለውጥ ሃይሎችን አፍሶ በማሰር እና በማሳደድ ስር ነቀሉን የለውጥ አብዮት ማስቆም አይቻልም appeared first on Zehabesha Amharic.

የግብጹን መሪ ሰብአዊነት ያዩ ባለ ሥልጣኖቻችን ለሕዝባቸው ምን ምላሽ አላቸው?!

$
0
0

በፍቅር


ethiopia2ብጥብጥና ኹከት በነገሠባት፣ እንደ አይ ኤስ ላሉ ጽንፈኞች፣ አክራሪ፣ ጨካኝና ነፍሰ ገዳይ ቡድን መናኻሪያ ከኾነችው ከአገረ ሊቢያ ባለፈው ሰሞን ኹላችንንም እጅጉን ያሳቀቀን፣ እንባን ያራጨን፣ እማማ ኢትዮጵያን የኀዘን ከል ያለበሰ ከፉ መርዶን፣ የሚሰቀጥጥ ዜናን ሰምተናል፡፡ እንባችን ገና ከዓይናችን ሳይደርቅና ሳይታበስም ደግሞ ከዛች የሞት ምድር በምንሰማው ወገኖቻችን የእባካችሁ የድረሱልን ጥሪ ግራ ተጋብተን፣ በምናምጥበት፣ እግዚኦ አምላክ ሆይ ድረስልን! እያልን ባለንበት ከፈርዖኖቹ ምድር፣ ከዓባይ ስጦታ ምድር፣ ከወደ ግብጽ ደስ የሚያሰኝ የምሥራችን ሰማን፡፡

ከመሐመድ ጋዳፊ ሞት በኋላ ይኼ ነው የሚባል መሪ በሌላት በአገረ-ሊቢያ በስደት፣ በሞት ፍርሃትና በሥጋት ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን የግብጽ መንግሥት ነጻ አውጥቷቸው በዛች በፈርኦኖች ምድር ወገኖቻችን ደስታቸውን ሲገልጹ ዐየን፡፡ ለእነዚህ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የአገሪቱ ፕሬዝዳንት የኾኑት ጄ/ል አብዱልፈታህ አል ሲሲ በዓለም አቀፉ በካይሮ አየር ማረፊያ ከባለ ሥልጣኖቻቸው ጋር በአካል ተገኝተውም አቀባበል ሲያደርጉላቸው ጭምርም፡፡

ethiopiaኢትዮጵያውያኑም ስደተኞች ፊታቸው ላይ አንዳንች ልዩ ስሜትና ፈገግታ እየተነበባቸው የግብጽን ባንዲራ እያውለበለቡ ከሞት ሥጋትና ፍርሃት ላታደጓቸው የግብጽ መንግሥትና ለጄ/ል አብዱል ፈታህ አል ሲሲ አድናቆታቸውን፣ ምስጋናቸውን ሲገልጹ የሚያሣዩ ምስሎችንና ቪዲዮዎችንም በርካታ ኢትዮጵያውያን በአድናቆትና እጅግ በመገረም በማኅበራዊ ድረ ገጾች እየተቀባበሉት ይገኛሉ፡፡

በርካታዎችም፡- ‹‹ከናዝሬት መልካም ነገር ይወጣልን?! እንዲል ቅዱስ መጽሐፍ በታሪካዊ ጠላትነት ከፈረጅናት ከግብጽ ይሄ ዓይነቱ መልካምነት፣ ደግነት እንዴት ኾነ በሚል በመንታ ስሜት ውስጥ ኾነው የግብጽን መንግሥት በእጅጉ እያመሰገኑ ነው፡፡ ሌሎች ደግሞ ከምስጋናቸው ባሻገር ይህ የጄ/ል አል-ሲሲ ዕርምጃ አንዳች ፖለቲካዊ አጀንዳና ዲፕሎማሲያዊ መልእክት እንዳለው እየተናገሩ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ወደታች ጥቂት ነገሮች አነሣለሁ፡፡ ለነገሩ ይኼ ሁለተኛ ነገር ይመስለኛል፡፡ ትልቁና ዋናው ወገኖቻችን በሕይወት ለአገራቸው ምድር የሚበቁበት መንገድ መመቻቸት መቻሉ ነው፡፡

ዛሬ በሊቢያ በረኻ የወገን፣ የመንግሥት ያለኽ! በሚል ሲጮኹና ሲንከራተቱ የነበሩ እነዚህ ወገኖቻችን ከጭንቀትና ከሥጋት ተገላግለው የሰላም አየር ወደሚተነፍሱበት ወደ ግብጽ ምድር በሰላም መድረሳቸው ሰው የመኾን ክብርን፣ ፍቅርና ሰብአዊ ርኅራኄ ምን እንደኾነ በቅጡ ለምንረዳ ሰው ለኾንን ሰዎች ኹሉ ከፖለቲካውም፣ ከዲፕሎማሲያዊውም አጀንዳ በላይ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ፣ የሚገባኝም!!

በእርግጥም እነዚህ ወገኖቻችን ከዛ የሞት መናፍስት ካረበቡበት፣ ነፍሰ ገዳዮች፣ የሞት አበጋዞችና የክፋት ልጆች ያለ አንዳንች ከልካይ የጥፋት ሰይፋቸውን መዘው ከሚርመሰመሱበት፣ ሞትና ጭካኔ ከነገሠባት ከምድረ ሊቢያ ነጻ ወጥተው በሰላም ወደ ግብጽ ምድር መድረሳቸው እፎይ፣ ተመስገን ፈጣሪ ሆይ የሚያሰኝ ታላቅ ነገር፣ ድንቅ የኾነ የምስራችም ነው፡፡ ሌሎችም በጣርና በጭንቅ ያሉ ወገኖቻችንም የእነርሱ ዕድል እንዲገጥማቸው ነው የምንጸልየው፣ የምንመኝላቸው፡፡

እንደ እውነቱ ከኾነ ኢትዮጵያውያኑ በካይሮ አየር መንገድ የግብጽን ባንዲራ እያውለበለቡ ከመከራ፣ ከጭንቀት፣ ከሞት ለታደጋቸው የግብጽ መንግሥት ደስታቸውን ሲገልጹ ማየት በሥልጣን ላይ ላለው የኢሕአዴግ መንግሥት ትልቅ ኪሣራና ውርደት ነው፡፡ በነጋ ጠባ ልማት፣ ዕድገት እያለ የሚለፍፈው መንግሥት ሕዝቡን ከስደት ለመታደግ አቅቶትና ያለ ምንም እፍረት የወገኖቻችንን እልቂት ለራሱ ፖለቲካዊ አጀንዳ ሲጠቀምበት ታዝበነዋል፡፡ ይህን ውርደት ከማየት የበለጠ እንደ አገር፣ እንደ ሕዝብ ምን የሚያሳፍር፣ ምን የሚጠዘጥዝ ሕመምና ሥቃይ ይኖራል ወገን፡፡

እንደው የጄ/ል አል ሲሲ ምንም የተደበቀ ይባል የተሰወረ ፖለቲካዊ/ዲፖሎማሲያዊ አጀንዳ ይኑራቸው ግና ኢትዮጵያውያኑ ወገኖቻችንን በካይሮ አየር መንገድ ማረፊያ ገኝተው አቀባበል ሲያደርጉላቸው፣ የወገኖቻችንን በግፍ መታረድ ሰምተው ቢያንስ እንኳን ለሕዝቡ መጽናኛ የሚሆን መልእክት ለማስተላለፍ እንኳን ገና እያጣራን ነው በሚል በወገኖቻችን ሞት ላይ ሰብአዊ ርኅራኄ በጎደለው ሁኔታ ርካሽ ፖለቲካቸውን ሲሸቅጡብን፣ ሲነግዱብን አንዳንች እፍረት ብሎ ነገር ያልተሰማቸው ባለ ሥልጣኖቻችን እንደው ይሄን የጄ/ል አል ሲሲን ደግ ተግባር ሲያዩ ምን ተሰምቶአቸው ይኾን?!

ከትልቅ አክብሮትና ትሕትና ጋር፣ ለመሆኑ ክርስቲያን ነን በሚል በአደባባይ ያወጁልን የአገራችን ርዕሰ ብሔርና ጠቅላይ ሚ/ር እነዚህን ወገኖቻችንን የግብጹ ፕ/ት ዓላማቸው ምንም ይሁን ምንም ካይሮ አየር ማረፊያ ድረስ ተገኝተው አቀባባል ሲደርጉላቸው ሲያዩ ምን ተሰምቶአቸው ይሆን?! መቼም ለወገናቸው ልባቸው ውስጥ የቀረች ትንሽ እንጥፍጣፊ የኾነች ፍቅር፣ ክብርና ሰብአዊነት ካላቸው ይህን ውርደትና እፍረት የሚሸከሙበት ጫንቃ፣ ወኔ ይኖራቸውስ ይኾንን?!

ከሊቢያ በረኻ እስከ ደቡብ አፍሪካ፣ ከየመን እስከ ሳውዲና መካከለኛው ምሥራቅ የወገኖቻችን ደም የውሻ ደም ያኽል እንኳን ክብር ተንፍጎት፣ ሕዝባችን ላይ የሞት ሞትና ውርደት ሲታወጅባቸው ኀዘናችን፣ ቁጭታችንን ብሶታችንን ለመካፈል አንድ ቀን እንኳን በቅጡ ድምጻቸው ያልተሰማው ባለ ሥልጣኖቻችን፣ መሪዎቻችን ይህን የአል ሲሲን ሰብአዊነት ሲመለከቱ ምን ተሰምቶአቸው ይኾን?! እናስተዳድረዋለን ለሚሉት ሕዝባቸው ፍቅርና ሰብአዊነት ብሎ ነገር የተራቆቱ እነዚህ ባለ ሥልጣኖቻችን ከበቀልና ከክፋት ወጥተው ቆም ብለው ልባቸውን፣ ራሳቸውን በቅጡ ይፈትሹ፡፡

ጭካኔና በቀል በረበበትና በሚነበብበት ፊታቸው፣ ወዳጃችን ዲ/ን ዳንኤል ክብረት እንደጸፈው ማዘናቸውንም ኾነ መደሰታቸውን በማይገልጽ ድርቅ ያለ ስሜት፣ ከሥልጣን/ከወንበር ጋር ፍቅር በወደቀ ብኩን ልባቸው፣ በስንት ጉትጎታና እግዚኦታ በቴሌቪዥን ቀርበው የሚናገሩት ቃላቸው ሣይቀር እንደ በቆሎ ቂጣ አፋቸው ላይ እየተፈረፈረ ሲወድቅ እየታዘብን፣ ውስጣችን በኀዘን ነዶና ተኮራምቶ ከበገነ፣ ከተቃጠለ በኋላ የማታ ማታ የግዳቸውን የሚያስተላልፉልን እንጨት እንጨት የሚል ማጽናኛቸው እንኳን ከልባችን ከጆሮአችን ለመድረስ አቅም የሌለው መኾኑን ማን በነገራቸው፡፡

ለመሆኑ መንግሥታችን ፍቅርና ሰብአዊነት ምን እንደሆነ ይገባዋል፣ ያውቃልን?! እስቲ ከሰማችሁን ይህችን ዘመን አይሽሬ የኾነች ‹‹ታላቁ ነፍስ›› በሚል በሕዝባቸው የሚሞካሹት፣ የህንድ የነጻነት አባት የኾኑት ማሕተመ ጋንዲ በአንድ ወቅት ተናገሩትን አባባላቸውን ልጥቀስላችሁ፡- ‹‹Power based on Love is a thousand times more effective and permanent than power derived from fear.››

ፍርሃት አምጦ የወለደውን ጭካኔያችሁን እስቲ በፍቅር፣ በሰብአዊነትና በርኅራኄ ዘይት አለስልሱት፡፡ እንዲህ የምታስጨንቁትን ሕዝብ የሚያይ፣ የሚመለከት ፈጣሪ፣ ታዳጊ አምላክ እንዳለም አትዘንጉ፡፡ ያን አፍሪካን ሳይቀር የሚጠብቅ ግዙፍ የኾነ ሰራዊትና መሳሪያ ገንብቻለኹ፣ ማን ወንድ፣ የትኛውስ ጀግና ነው ከፊቴ የሚቆመው ብሎ የተገደረውን ደርግን/ጎልያድን በእናንተ በታናናሾቹ/በዳዊቶቹ ያዋረደው ሕያው አምላክ ዛሬም በዙፋኑ ላይ እንዳለ አትዘንጉት፡፡

እናም መሪዎቻችን ፍቅር ከምንም በላይ ኹሉን ለመግዛት፣ ኹሉን ለማሸነፍ የሚያስችል ታላቅ ኃይልና ብርቱ ጉልበት እንዳለው ቢረዱ እንዴት መልካም በኾነ ነበር፡፡ መሳሪያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ሠራዊታቸውን ተማምነው ሕዝቡን እያስጨነቀ፣ በምስኪን ሕዝቡ ላይ የብረቱን ቀንበር እያጠበቀ ላለው መንግሥታችን ይህ መልእክት ይድርሰው ዘንድ ምኞቴ ነው፡፡

እባካችሁ አምባ ገነኖች የሕዝብን ቁጣና ብሶት በኃይል፣ በመሳሪያ መግታት እንደማይቻልም ከታሪክ ተማሩ፡፡ እኛ ግን እንዲህ እንላለን፣ እንዲህም እንመኛለን፣ መቼም ምኞት አይከለከልምና፡-

ለሕዝብ የአደራ ቃል ታማኝ የኾኑ፣ በሕዝብ ፍቅር የነደዱ፣ በሕዝባቸው ጽኑ ቃል ኪዳን የታሰሩ፣ ራሳቸውን ለመሥዋዕትነት ያዘጋጁ እንደ አይሁዳዊው ሕዝብ ነጻ አውጪ እንደ ሙሴ፡-‹‹ይህን ሕዝብን በምድረ በዳ ከምታጠፋው እኔ ከሕይወት መዝገብ ደምስሰኝ፡፡›› የሚሉ፣ በሕዝባቸው ስለ ሕዝባቸው ፍቅር በነፍሳቸው የቆረጡ፣ ጽኑ፣ ባለ ራእይ የኾኑ፣ ከሥልጣን፣ ከወንበር በፊት ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ስፍራን፣ ክብርን ያገኙ፣ ጀግና መሪዎችን እንመኛለን፤ በእውነት ይህን ማግኘትም ትልቅ መታደል ነው፡፡

እንደ መውጫ ከፍጥረት ታሪክ ማግሥት ጀምሮ የግብጽ ምድር በረከት፣ ሲሳይና ሕይወት በኾነው በዓባይ ውኃ ሺ ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት ያላቸው ኢትዮጵያና ግብጽ፣ እስከ ዛሬ ዓይንና ናጫ ከኾኑበት የዓባይ ውኃ ፖለቲካ እስጥ አገባ ለጊዜውም ቢሆን ግብጾቹ አቋማቸውን አለሳልሰው እንዲያ እንዳላልናቁንና እንዳላዋረዱን፣ እንዲህ ወገኖቻችንን ከመታደግ ባለፈ በአደባባይ በርዕሰ ብሔራቸው አማካኝነት ወገኖቻችንን በክብር ለመቀበል የቻሉበት አካኼድ በኢትዮጵያና በግብጽ በኩል ለተጀመረው ዲፕሎማሲያዊ ድርድር አንድ እመርታ፣ አንድ ታላቅ ድል እንደኾነ ነው የሚሰማኝ፡፡

ትንግረተኛ በኾነው በዓባይ ወንዛችን ምክንያት ጠላትነትን ከተርፍንባቸው ከግብጾቹ እንዲህ ዓይነቱ ሰብአዊነትና ርኅራኄ ማየታችን የግብጹን ፕሬዝዳንት እናመስግናቸው ዘንድ ያስገድደናል፡፡ በመንግሥታችን፣ በባለ ስልጣነሞቻችን እያፈርንና እየተሳቀቅንም ቢሆን በሂደት ግብጾቹ አቋማቸውን በማለሳለስ እንዲህ ዓይነቱን ወገኖቻችንን ከሞት የታደጉበትን የወዳጅነት ውለታቸውን፣ ሰብአዊ ርኅራኄያቸውን መቼውንም ቢሆን አገራችንና ሕዝባችን የሚረሳው፣ የሚዘነጋው አይሆንም፡፡

ግብጻውያኑ ከበዛው ተንኮላቸውና መሰሪነታቸው ጋርም ቢሆን ፈረንጆቹ፡- ‹‹A friend in need is a friend in deed!›› እንዲሉ በዚህ የእማማ ኢትዮጵያ ዋይታና የሰቆቃ የቀውጢ ጊዜ ቢያነስ ከጎናችን ቆመው ታማኝነታቸውንና ወዳጅነታቸውን አሳይተውናልና ልናከብራቸቀው፣ ልናወድሳቸው ግድ ይለናል፡፡

በሌላ በኩል ግን ከላይ ለመግለጽ እንደ ሞከርኩት ይህ የግብጽ መንግሥት ዕርምጃ ሕዝቡን ከስደት፣ ከባዕድ ጋር ከሚደርስበት ግፍ፣ መከራ፣ ሥቃይና ሞት ለመታደግ ወኔውም ኾነ አቅሙ ላነሰው፣ ለሚያስተዳድረው ለሕዝቡ ፍቅርና ክብር ለመስጠት ላዳገተው መንግሥታችን ግን ቢያስተውለው ታላቅ ውርደት፣ ኪሳራም ነው!!

የቀሩትም በስደት ላይ ያሉ ወገኖቻችን ወደ አገራቸው በሰላም ይገቡ ዘንድ ጸሎታችን ነው!! ‹‹እግዚአብሔር ትዕግሥትን፣ በጎ ትምህርትንም ይሰጣቸው ዘንድ የድካማቸውንም ፍጹም ዋጋ ይሰጣቸው ዘንድ ስለ ተሰደዱ ሰዎች እንማልዳለን፡፡›› እንድትል የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ-ቅዳሴዋ!!

ሻሎም!!

 

The post የግብጹን መሪ ሰብአዊነት ያዩ ባለ ሥልጣኖቻችን ለሕዝባቸው ምን ምላሽ አላቸው?! appeared first on Zehabesha Amharic.

የብሄራዊ ደህንነት መረጃ ሃላፊዎች ጥብቅ ፍተሻ እንዲካሄድ አዘዙ

$
0
0

Policeሰሞኑን በአዲስ አበባ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አባላት ነን ያሉ ሲቪል የለበሱ ግለሰቦች፣ ከደህንነት መስሪያ ቤት ነው የመጣነው በማለት በየክፍለከተማዎችና ወረዳዎች እየዞሩ፣ ለመንግስት መስሪያ ቤቶችም ሆነ ለግል ተቋማት ሃላፊዎች፣ ” ማንም ሰው ፣ የመንግስት ባለስልጣናም ሆነ መለዮ ለባሽ ወታደር፣ ፖሊስ ወይም ተስተናጋጅ ባለጉዳይ” ሽጉጥን ጨምሮ የትኛውንም አይነት የጦር መሳሪያ ይዘው እንዳይገቡ፣ የመስሪያ ቤት ጠባቂዎች ጥብቅ ፍተሻና ቁጥጥር እንዲያደርጉ” ትእዛዝ አስተላልፈዋል።
እንዲህ አይነት ትእዛዝ ተላልፎ እንደማያውቅ የሚናገሩት ምንጮች፣ ትእዛዙ መጪውን ምርጫ ተከትሎ ረብሻ ሊፈጠር ይችላል ከሚል ስጋት ሳይሆን እንደማይቀር ምንጮች አስተያየታቸውን ቢሰጡም፣ ትእዛዙ በኢህአዴግ ባለስልጣኖች ላይ ሳይቀር መተላለፉ ውሳኔው ከመጪው ምርጫ ጋር ብቻ ያልተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ያመለክታል።
የደህንነት ሰራተኞች ለመስሪያ ቤት ሃላፊዎች ብቻ ሳይሆን ትእዛዙን ለጥበቃ ሃላፊዎችም እየሰበሰቡ በመናገር ላይ ናቸው።

Source:: Ethsat

The post የብሄራዊ ደህንነት መረጃ ሃላፊዎች ጥብቅ ፍተሻ እንዲካሄድ አዘዙ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 74 (በPDF ያንብቡ)


“ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም”–አርበኞች ግንቦት 7

$
0
0

የአርበኞች ግንቦት 7 በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ጽሁፍ

የህወሓት አገዛዝ ፋሽስታዊ ባህርያት እያደር መረን እያጣ፤ ነውረኛ እየሆነ መጥቷል። በአሳለፍነው ሣምንት ብቻ እንኳን አስነዋሪ ይዘት ያላቸው ሁለት ፋሽስታዊ ክስተቶችን አስተውለናል።
ginbot 7
አንዱ በምርመራ ስም በታሳሪዎች ላይ የሚደረገው አሳፋሪ ሰቆቃ ነው። በገላቸው በሚያፌዙና በሚሳለቁ ተቃራኒ ፆታ መርማሪዎች ፊት ለሰዓታት ተመርማሪዎች ራቁታቸውን እንዲሆኑ የሚደረግበት እና እየተፌዘባቸው የሚደበደቡበት ሥርዓት መኖሩ የጉዳቱ ሰለባዎች ይፋ ሲያወጡ እፍረቱ ለመርማሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉድ ተሸክመን ለኖርነው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ነው። በተለይም ደግሞ እንዲህ ዓይነት ክብረነክ ሰቆቃ በሴቶች ላይ እየተፈፀመ መሆኑን ስንሰማ አገራዊ ውርደቱ ያሸማቅቀናል። እንዲህ ዓይነቶችን በሰው ስቃይና እፍረት የሚዝናኑ ጉዶችን ተሸክመን የምኖር መሆናችን ሁላችንን ያዋርደናል። ይህንን አስነዋሪ “የምርመራ ዘዴ” ያጋለጡት የዞን 9 ብሎገሮች፣ ጋዜጠኞችና ፓለቲከኞች ክብርና ሞገስ የሚገባቸው ጀግኖች ሲሆኑ የተዋረዱት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን መሆናችን ሊሰማንና “ውርደት በቃ” ልንል ይገባናል።

ሁለተኛው አሳፋሪ ድርጊት ደግሞ ወገኖቻችንን በግፍ ባረደው አይሲስ በተሰኘው አሸባሪ ድርጅት ላይ የህወሓት አገዛዝ የተለሳለሰ አቋም ወስዷል ብለው ራሱ ህወሓት በጠራው ሰልፍ ላይ ተቃውሞዓቸውን ባሰሙ ወጣቶች ላይ አገዛዙ የወሰደው የኃይል እርምጃና ከዚያም ወዲህ እየተደረገ ያለው ነገር ነው። አገዛዙ ለፕሮፖጋንዳው ይጠቅመኛል ብሎ በጠራው ሰልፍ ወጥተው ተቃውሞዓቸውን የገለፁ ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድበዋል፤ በጅምላ ወደ እስር ቤቶች ተግዘዋል። የአገዛዙ ካድሬዎች ወገኖቻችንን የፈጀውን አይሲስን በመቃወም ፋንታ የራሱ የህወሓትን ውል አልባ ህግ አክብረው በመንቀሳቀስ ላይ ያሉትን ሰማያዊ ፓርቲ፣ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን እና አረና ፓርቲን እየወነጀሉ መሆኑ አጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። የአይሲስን አረመኔአዊ ድርጊት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር ለማገናኘት በህወሓት የደህንነት ቢሮ አማካይነት እንቅስቃሴ መጀመሩ እየተሰማ ነው። ለወጣቱ በብዛት መሰደድ በምክንያትነት የሚያቀርቡት ደላሎችን መሆኑ አላዋቂነት ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ቅራኔው በኢትዮጵያዊያን መካከል እርስ በርስ እንዲሆን ያለመ መሠሪነት ነው። ከዚህም አልፎ የትግራይ ወጣቶችን ነጥሎ በመሰብሰብ “ትምክህተኞች ሊበሉህ ነውና ታጥቀህ ሳይቀድሙህ ቅደም” እያሉ መቀስቀስ በመንግሥት ደረጃ የእርስ በርስ እልቂትን ከማደራጀት ተለይቶ አይታይም። የሥርዓቱ ይሉኝታ ቢስነት የደረሰበት ዝቅጠት ገላጭ ከሆኑ ነገሮች አንዱ “እስከምርጫ መጨረሻ ድረስ ልጆቻችሁን አስረን እናቆይላችሁ” እያሉ ወላጆችን እስከመጠየቅ መድፈራቸው ነው።
arbegnoch ginbot 7
ከላይ በአጭሩ የተዘረዘሩት ኩነቶች የሚያረጋግጡት ህወሓት የተማከለ አመራር አጥተው መንገድ የጠፋቸው፤ ሆኖም ግን እጃቸው ውስጥ የገባው ስልጣንና ሀብት ላለማጣት ምንም ነገር ከማድረግ የማይመለሱ አውሬዎች ስብስብ መሆኑ ነው። እንዲህ ዓይነቱን የአውሬዎች ስብስብ የሚገዛው የህግም ሆነ የሥነ-ምግባር ገደብ የለም። ህወሓት እስር በርሳችንን አባልቶ አገራችንንና ሕዝቧን ወደ ማንወጣው አዘቅት ከመክተቱ በፊት ራሱ ህወሓትን ማስወገድ እና በምትኩት ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን መገንባት የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው። ይህ ካላደረግን አሁን በወህኒ ቤቶች የሚደረገው ዜጎችን ልብስን አስወልቆ የማዋረድ አስነዋሪ ተግባር ነገ በአደባባዮች የማይደረግ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ የለንም። ይህ ትውልድ ኃላፊነቱ ካልተወጣ ህግን አክብረው ከአገዛዙ የተለየ ሀሳብ እናራምዳለን የሚሉ ወገኖቻችን በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው። በህወሓት መሠሪ ተግባራት ሳቢያ በክርስትናና እስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን መካከል ያለው መግባባት እንዲሻክር እየተደረገ ነው። ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም። ይህንን ማስቆም ያለብን እኛ ሁላንችንም ነን። በአደባባይ መደራጀት ሲከለከል በምስጢር መደራጀትን መልመድ የኛ ኃላፊነት ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓልን ስናከብር ከቀደምቶቻችን ልንወርስ ከሚገቡን እሴቶች አንዱ ለክብራችን ዋጋ መክፈል ያለብን መሆኑን ጭምር ነው። የኢትዮጵያዊያን ክብር በወያኔ ሲዋረድ እያየን ዝምታን ከመረጥን ከዚህም የባሰ እንዲመጣ መፍቀዳችንን እንወቀው።

አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የዜጎችና የአገር ውርደት ይብቃ! በተባበረ ክንድ ህወሓት ይወገድ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመመሥረት መሠረት እንጣል፤ ይህንን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣት በኅብረት እንነሳ ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!

The post “ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም” – አርበኞች ግንቦት 7 appeared first on Zehabesha Amharic.

አሰፋ ማሩ –ልክ የዛሬ 8 ዓመት ወደ ቤቱ ሊገባ ሲል በወያኔ ተረሽኖ ሕይወቱ አለፈ

$
0
0

ልክ የዛሬ 18 ዓመት ሚያዝያ 30 ቀን 1989 ዓ.ም አቶ አሰፋ ማሩ ወደ ቤቱ ሊገባ ሲል በወያኔ ተረሽኖ ሕይወቱ አለፈ
የኢመማ ጀግኖች ሰማእታትን እናስብ።
asefa maru
የዛሬ 18 ዓመት ሚያዚያ 30 ቀን 1989 ዓ.ም አቶ አስፋ ማሩ ከቤቱ በሰላም ወጥቶ ወደ ሥራ በመሔድ ላይ እያለ በአዲስ አበባ ሐምሌ19 የሕዝብ መነፈሸ አካባቢ በጠራራ ጸሐይ በወያኔ/ኢህአዴግ ነፍሰ ገዳይ ፖሊሶች የጥይት እሩምታ ሰለባ የሆነ ጀግና ኢትዮጵያዊ ነው።

አቶ አሰፋ ማሩ በጊዜው በወሎ ክፍለሀገር በላስታ አውራጃ መቄት ወረዳ በ1951ዓ.ም ተወለደ። በመምህርነት ሙያ ከማገልገሉም ባሻገር በሙያ ማህበሩ የአመራር አባል በመሆንም የመምህራንን መብትና ጥቅም ለማስከበር ፣ የትምህርቱን ጥራት ለማስጠበቅ በሚደረገው ትግል በግምባር ቀደምትነት ከሚታገሉት አንዱ ሆኖ ሕይወቱ በግፈኞች እስካለፈበት ዕለት በጽናት ቆሞ ቆይቷል። በወቅቱ በነበረው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤም በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት የላቀ ድርሻ አበርክቷል።

The post አሰፋ ማሩ – ልክ የዛሬ 8 ዓመት ወደ ቤቱ ሊገባ ሲል በወያኔ ተረሽኖ ሕይወቱ አለፈ appeared first on Zehabesha Amharic.

ፖሊስ የፍ/ቤት ትዕዛዝን በመሻር የሰማያዊ አባላትን ዋስትና ከለከለ

$
0
0

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

ethiopia-blue-party-300x164በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የካዛንቺስ 6ኛ ፖሊስ በእስር ላይ የሚገኙትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የፍርድ ቤት ትዕዛዝን በመሻር ዋስትና ከለከለ፡፡

ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስ ሊቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ የፈጸመውን የሽብር ድርጊት ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ላይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳትና በመሳተፍ›› ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የፓርቲው አባላት ዛሬ ሚያዝያ 30/2007 ዓ.ም ጠዋት በቄራ የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ቀርበው የ6000 ብር የሰው ዋስትና ተፈቅዶላቸው ነበር፡፡

በእነ ወይንሸት ሞላ የምርመራ መዝገብ የተካተቱ አምስት ሰዎች ፍርድ ቤት ቀርበው ዋስትና ከማግኘታቸው በፊት ፖሊስ ‹‹ምርመራየን አልጨረስኩም፣ ተጠርጣሪዎች በዋስ ቢወጡ በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጡ ይችላሉ›› እና ሌሎች ተደጋጋሚ ምክንያቶችን በማቅረብ ዋስትና እንዳይፈቀድ ለፍርድ ቤቱ ጥያቄ አቅርቦ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ፍርድ ቤቱ ከሀገር ሊወጡ ይችላሉ የሚለውን ምክንያት ባለመቀበል ከዋስትናው ጋር ለኢምግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ የሚል ደብዳቤ እንዲጻፍ ትዕዛዝ በመስጠት የ6000 ብር ዋስ አቅርበው እንዲወጡ ሊፈቅድ ችሏል፡፡

በዚህ መሰረት የተጠርጣሪ ቤተሰቦች ዋስትናውን ጨርሰው ለማስፈታት በሄዱ ጊዜ ፖሊስ ‹‹ሰኞ ይግባኝ ብለን ፍርድ ቤት ስለምናቀርባቸው ሊፈቱ አይችሉም›› በሚል ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ ተጠርጣሪዎቹ በእስር እንዲቆዩ አድርጓል፡፡

በእነ ወይንሸት የምርመራ መዝገብ የተካተቱት አምስት ሰዎች ወይንሸት ሞላ፣ ዳንኤል ተስፋዬ፣ ኤርሚያስ ጸጋየ እና ማስተዋል ፈቃዱ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ሲሆኑ፣ በዚሁ መዝገብ ላይ ፖሊስ የፓርቲው አባል እንደሆነች የሚገልጸው፣ እሷ ግን አባል አለመሆኗን የገለጸች ቤተልሄም አቃለወርቅም ትገኛለች፡፡

The post ፖሊስ የፍ/ቤት ትዕዛዝን በመሻር የሰማያዊ አባላትን ዋስትና ከለከለ appeared first on Zehabesha Amharic.

“ነብስ ይማር ቦቴንግ”! (አዋዜ፡አለምነህ ዋሴ ዜና)

በአይሲኤስ የተገደሉትን ቤተሰቦች ያልረዱት ኣላሙዲን ሶስት ዘፋኞችን ሚሊየነር አደረጉ

በጋሞጎፋ ዞን በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ ነው

$
0
0

ethiopia-blue-party-300x164በጋሞጎፋ ዞን በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እየታደኑ እየታሰሩ መሆኑን የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡ ከትናንት ሚያዝያ 30/2007 ዓ.ም ጀምሮ ጋሞ ጎፋ ዞን ጎፋ ወረዳ ሳውላ ከተማው ውስጥ በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች መታሰራቸውን የጋሞ ጎፋ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ በትናንትናው ዕለት በጋሞጎፋ ዞን ዳራማሎ ወረዳ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 17 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታስረዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጋሞጎፋ ዞን ቦንኬ ወረዳ ለፖሊስ ‹‹ለሰማያዊ ፓርቲ የሚቀሰቅስ ማንኛውም አካል ላይ እርምጃ ውሰዱ›› የሚል ትዕዛዝ መተላለፉን የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡

The post በጋሞጎፋ ዞን በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

መርካቶ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ወድቃለች

$
0
0

ህልማቸው በሜዲትራንያን ባህር የተዋጠው 7ቱ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
ከኤልሳቤት እቁባይና አለማየሁ አንበሴ

በቅርቡ በሜዲትራኒያን ባህር ከዘጠኝ መቶ በላይ ሰዎችን አሳፍራ ስትጓዝ ሰጥማ 28 ተጓዦች ብቻ በህይወት በተረፉባት ጀልባ ላይ ተሳፍረው ከነበሩት መካከል በአደጋው የሞቱት የሰባት ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አሳዛኝ መርዶ የተሰማው ከትላንት በስቲያ ነበር፡፡ የሰባቱም ሟቾች የትውልድ ሰፈር ደግሞ በአዲስ አበባ መርካቶ በሚገኘው የአባኮራን ሰፈር ውስጥ ነው፡፡ በትላንትናው ዕለት የሟቾች ቤተሰቦችን ለማነጋገር ወደ አካባቢው ስንሄድ ሰባት ድንኳኖች ተርታውን ተተክለው ቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድና ጓደኞች ለቅሶ ተቀምጠው ነበር፡፡
merkato
ከሊቢያ ባህር ዳርቻ ተነስታ ጣሊያን ልትደርስ ስትል በሰጠመችው ጀልባ ውስጥ ተሳፍረው ከነበሩት የአባኮራን ሰፈር ልጆች መካከል ዘመን ኢብራሂም የተባለው ወጣት በአስገራሚ ሁኔታ ህይወቱ ሊተርፍ ችሏል፡፡ የጀልባዋን መስጠም አስመልክቶ በአልጀዚራ በተሰራጨ ዘገባ፣ ልጁ ከአደጋው ተርፎ በእርዳታ ሰራተኞች ድጋፍ ሲደረግለት ታይቶ ነበር። ይሄኔ ነው አብረውት የሄዱት የሰፈሩ ልጆች የት ገቡ የሚለው ጥያቄ በቤተሰብና በጓደኞች ዘንድ የተነሳው፡፡ ቀደም ሲል በተመሳሳይ መንገድ በባህር ተጉዘው ጣሊያን የገቡ የሰፈር ልጆች ባደረጉት ማጣራት ግን ከዘመን ኢብራሂም በስተቀር ሁሉም ባህር ውስጥ ሰጥመው እንደሞቱ ተረጋግጧል ተብሏል፡፡ ወጣቱ ዘመን ኢብራሂም ተዓምራዊ በሚመስል ሁኔታ ነው ህይወቱ የተረፈው፡፡ ወደ ባህሩ ሲወድቅ በአጋጣሚ ውሃው ላይ ስትንሳፈፍ ያገኛትን አንዲት ጀሪካን ይዞ ለ2 ሰዓታት ያህል ራሱን ለማዳን ጥረት ሲያደርግ ከቆየ በኋላ ነው የነፍስ አድን ሰራተኞች የደረሱለት፡፡ እስከዚያው ግን ብዙ በመሰቃየቱ አሁንም በሙሉ ጤንነት ላይ እንደማይገኝ ጓደኞቹ ነግረውናል፡፡ ዘመን ኢብራሂም አሁን የሚገኘው በጣሊያን ነው ተብሏል፡፡መጋቢት 1 ቀን 2007 ዓ.ም የራሳቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ኑሮ ለማሻሻል አውሮፓን አልመው ከሰፈራቸው የወጡት 9 ወጣቶች ሲሆኑ ስምንቱ በአደጋው እንደሞቱ ቢነገርም የአንደኛው ወጣት ወላጆች ግን “ልጃችንን በቲቪ አይተነዋል፤ አልሞተም” በማለት መርዶውን አልተቀበሉትም፡፡

አብዱል ጅላል ወጉ ወይም በሰፈር ስሙ ሙራድ የ25 ዓመት ወጣት ሲሆን በቀን ስራና በሱቅ በደረቴ ይተዳደር ነበር፡፡ ኑሩ መሀመድ የ25 ዓመት ወጣት ሲሆን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በሳይኮሎጂ የትምህርት ክፍል አንድ አመት ተምሮ ቤተሰብ ለመርዳት ትምህርቱን አቋርጦ ነው የተሰደደው፡፡ አብዱልከሪም ዘይኒ ደግሞ የ20 ዓመት ወጣት ሲሆን በቀለመወርቅ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ ነበረ፡፡ ሰይድ ይመር የ22 ዓመት ወጣት ሲሆን በተለያዩ የጉልበት ስራዎች ራሱንና ቤተሰቦቹን ያስተዳድር ነበር ተብሏል፡፡ አሊ መሀመድ የ26 ዓመት ወጣት ነበር፡፡ የሚሰራበት ሱቁ እንዲፈርስ በመወሰኑ ነው እቃዎቹን ሸጦና ገንዘብ ተበድሮ ለስደት የወጣው፡፡ ነጃ ሳቢር አወል የ24 ዓመት ወጣት ሲሆን የተለያዩ ተባራሪ አነስተኛ የንግድ ስራዎችን በመስራት ይተዳደር ነበር፡፡ እንድሪስ አደም ደግሞ የ18 ዓመት ወጣት ሲሆን ከኢንፎኔት ኮሌጅ በቴክኒክና ሙያ ተመርቆ ስራ አጥ እንደነበር ከአካባቢው ያሰባሰብነው መረጃ ያመለክታል፡፡ የእነዚህ ወጣቶች መርዶ ሰሞኑን ቢነገርም ወላጆች፣ ቤተሰቦችና ጓደኞች መሸበር የጀመሩት ግን በሊቢያ በአይኤስ የተገደሉት ኢትዮጵያውያን መርዶ ከተሰማ ጊዜ አንስቶ ነው፡፡ በየጊዜው ወጣቶቹ በአይኤስ እጅ ወድቀዋል የሚል መረጃን ጨምሮ ብዙ ያልተጣሩ ወሬዎች ይመጡ ስለነበር፣ ቤተሰብና ጓደኞች በስጋት ውስጥ ነው የከረሙት። አብዱ ሀሰን አሊ የተባለው የሟቾቹ አብሮ አደግ መርዶውን እንዲያረዳ ከጣሊያን ሲደወልለት ሊሸከመው የማይችል ዱብ እዳ እንደወረደበት ነበር የቆጠረው፡፡ “ ማን ማንን ሊያፅናና ነው?” የሚል ከፍተኛ ጭንቀትና ፍርሀት ውስጥ ገብቶ እንደነበር ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡

ሆኖም መርዶው በድንገት ደርሶ ቤተሰብ ከሚጎዳ በሚል የአካባቢውን ሽማግሌዎች ሰብስቦ መርዶው ከትላንት በስቲያ እንዲነገር ማድረጉን ገልጿል፡፡ በመርካቶ አባኮራን ሰፈር መርዶው ለቤተሰብ ከተነገረበት ሰአት ጀምሮ በከፍተኛ ሀዘን የተዋጠ ሲሆን ሰባቱም ሟቾች ጎረቤታሞች በመሆናቸው በመደዳ በተጣለው ሰባት ድንኳን ሰዎች ሀዘን እየደረሱ ነው፡፡ ይሄ አሳዛኝ ክስተት ለመላው ኢትዮጵያውያን መሪር ነው – በተለይ ደግሞ ለወላጆችና ቤተሰቦች፡፡ ህልማቸው በሜዲትራኒያን ባህር የተዋጠው ወጣቶች ወላጆች እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሲሆን ብዙዎቹ ልጆቻቸው የሚጦሯቸው ናቸው፡፡ መተዳደሪያ ያላቸው ደግሞ ከእጅ ወደ አፍ የሚባል ዓይነት ነው፡፡ በጥበቃ፣ በፅዳት፣ ልብስ በማጠብ፣ ጉሊት በመቸርቸርና እንጀራ በመጋገር ነው የሚተዳደሩት፡፡ ልጆቻቸው ሊቢያ፣ ቤንጋዚ ሲደርሱ ወደ አውሮፓ ለመሻገር በመቃረባቸው ገንዘብ እንዲልኩላቸው ጠይቀው፣ ከሰፈር ሰዎች ተዋጥቶና አንዳንድ ወላጆች በዋስ ተበድረው እንደላኩላቸው ለማወቅ ችለናል፡፡ ወጣቶቹ ሊቢያ ለመድረስ እያንዳንዳቸው ወደ 80ሺ ብር የሚጠጋ ገንዘብ እንደፈጀባቸው ታውቋል፡፡ በህይወት የተረፈው የዘመን ኢብራሂምን ወላጆች ለማግኘት ብንሞክርም ልጁ ወላጆቹን ያጣው በለጋ እድሜው እንደነበርና ጎረቤቶች እንዳሳደጉት ነዋሪዎች ነግረውናል፡፡ በጓደኞቻቸው ላይ ያጋጠመው አደጋ ያስደነገጣቸው አብሮ አደጎቻቸው በግራ መጋባት መንፈስና በተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ያሉ ሲሆን አሁንም ጣሊያን መግባት የቻሉ ሁለት የሰፈሩ ልጆች ወደ ሌላ ከተማ ለመሻገር ሁሉም የቻለውን አዋጥቶ እንዲልክላቸው በመማፀናቸው የአካባቢው
ነዋሪዎች የሚችሉትን እያደረጉ መሆኑን ገልፀውልናል፡፡

ምንጭ – በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ

The post መርካቶ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ወድቃለች appeared first on Zehabesha Amharic.


አላሙዲ በኦሮሚያ ክልል የተገኘው ከፍተኛ ክምችት ያለው የወርቅ ማዕድንን ሊያወጡ ነው

$
0
0

ቀጣዩ ዘገባ የተገኘው ዛሬ በኢትዮጵያ ታትሞ ከተሰራጨው ሪፖርተር ጋዜጣ ነው

ብሔራዊ ማዕድን ኮርፖሬሽን በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ዳዋ ዲጋቲ ቀበሌ በሚገኘውና በልዩ መጠሪያው ኦኮቴ ተብሎ በሚጠራው ሥፍራ ያገኘው ከፍተኛ ክምችት ያለው የወርቅ ማዕድን ላይ ሥራ ሊጀምር መሆኑን፣ የኮርፖሬሽኑ ባለቤትና ባለሀብት ሼክ መሐመድ ሁሴን ዓሊ አል አሙዲ ሚያዝያ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. ገለጹ፡፡
al amudi and abadula gemeda
ሼክ አል አሙዲ ከፍተኛ የወርቅ ክምችት መገኘቱን የገለጹት፣ ሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ በማዕድንና በአግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ የስምንት ቢሊዮን ብር ማስፋፊያ ፕሮጀክት መጀመሩን አስመልክቶ በሸራተን አዲስ ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ነው፡፡

ብሔራዊ ማዕድን ኮርፖሬሽን ላለፉት 15 ዓመታት ባደረገው ጥናት የወርቅ ክምችቱ መገኘቱን የተናገሩት ባለሀብቱ፣ ‹‹የማዕድን ሥራችን እየሰፋ ነው፡፡ ቦታው ትልቅ የወርቅ ልማት ያለበት ነው፡፡ ትልቅ የወርቅ ክምችትም አግኝተናል፡፡ ለሚድሮክ ጎልድ ትልቅ ፕሮጀክት ከመሆኑም በተጨማሪ ኢትዮጵያን የሚያስጠራ ፕሮጀክት ነው፤›› ብለዋል፡፡

የተገኘው የወርቅ ክምችት ለሚቀጥሉት 15 ዓመታት ከ20 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለአገሪቱ ገቢ የሚያስገኝ መሆኑን ጠቁመው፣ ሁሉም ዝርዝር ጥናት እየተጠናቀቀ በመሆኑ፣ በቅርቡ ወደ ሥራ እንደሚገባም ሼክ አል አሙዲ ገልጸዋል፡፡ ሌላው በትግራይ ክልል ስለተገኘው የማዕድን ክምችት ገልጸው፣ ብዙ ወርቅ ባይኖርበትም የዚንክ፣ የሊድና የብር ክምችት መገኘቱንና ወደ ምርት ለመግባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሶዳ አሽ ፕሮጀክት እንዳላቸውና ማምረት መጀመራቸውንም አክለዋል፡፡

በሌላ በኩል በዶ/ር አረጋ ይርዳው ዋና ሥራ አስፈጻሚነት የሚመራው ሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ወደ ላቀ ስኬት የሚያሸጋግረውን አዲስ ፕላን መንደፉን ገልጾ፣ የወርቅ ማዕድንና አግሮ ፕሮሰሲንግ ማስፋፊያ የስምንት ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል፡፡

ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዶ/ር አረጋ እ.ኤ.አ ከ2015 ጀምሮ ቴክኖሎጂ ግሩፑ ተግባራዊ ማድረግ የሚጀምረው ዕቅድ ከ15 እስከ 20 ዓመታት የሚያገለግል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በስምንት ቢሊዮን ብር ወጪ የሚስፋፉት ፕሮጀክቶች የወርቅ ማዕድን ልማት፣ የተቀናጀ ዘመናዊ የዶሮ ዕርባታ፣ በመስኖ የተደገፈ ዘመናዊ የከብት መኖ (አልፋ አልፋ) ልማትና የተቀናጀ የወተትና የሥጋ ልማትን እንደሚያካትቱ አስረድተዋል፡፡

የማስፋፊያ ፕሮጀክቶቹ በሦስት ክልሎች እንደሚከናወኑ የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ 4.2 ቢሊዮን ብር (55 በመቶ የሚሆነው) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ሥራ፣ ቀሪው በአማራ ክልል ለሚካሄደው አግሮ ፕሮስሲንግ (የዶሮ እርባታ) እና በኦሮሚያ ክልል ለሚካሄደው አግሮ ፕሮሰሲንግ (የመኖ፣ የወተትና የሥጋ) ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች የሚውል መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የማስፋፊያ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ከሦስት እስከ አምስት ዓመታት የሚወስድ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

በማዕድንና በአግሮ ፕሮሰሲንግ የሚደረገው ኢንቨስትመንት ሥራው ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራው ሲገባ፣ በየዓመቱ ከምርት ሽያጭ 3.5 ቢሊዮን ብር ገቢ እንደሚገኝና በልማቱ ዕቅድ ዘመን 61. 90 ቢሊዮን ብር የሽያጭ ገቢ ሊገኝ እንደሚችል ዕምነታቸው መሆኑን ዶ/ር አረጋ ተናግረዋል፡፡ ከልማቱ በታክስ፣ በሮያሊቲና በሌሎች ክፍያዎች በየዓመቱ 880 ሚሊዮን ብር ለመንግሥት ገቢ እንደሚደረግ ገልጸው፣ በተወጠነው የኦፕሬሽን የዕቅድ ዘመን (ከ15 እስከ 20 ዓመታት) በጠቅላላው 14.85 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ገቢ ሊሰበሰብ እንደሚቻል አስረድተዋል፡፡ ቴክኖሎጂ ግሩፑ ቅድሚያ የሚሰጣቸው የልማት ዘርፎች የወርቅ ማዕድንና አግሮ ፕሮስሲንግ መሆናቸውን የጠቆሙት ዶ/ር አረጋ፣ ማዕድንን በሚመለከት ዋናው ተዋናይ ሚድሮክ ወርቅ ኩባንያ መሆኑንና አግሮ ፕሮስሲንጉን በሚመለከት ደግሞ ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ሚድሮክ ወርቅ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት አሥር ዓመታት በመተከል አካባቢ ሰፊ የማዕድን ፍለጋ ሲያካሂድ ቆይቶ፣ በቂ የወርቅ ክምችት መኖሩን ካረጋገጠ በኋላ ባህር ዶልቢር ሚኒራልስ ኢንዱስትሪ አድቫይዘርስ በተባለ የእንግሊዝ ኩባንያ የአዋጭነት ጥናቱን ማስጠናቱን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡ አሥር ዓመታት የፈጀውን የማዕድን ፍለጋ ግን ኢትዮጵያውያን የኩባንያው ሠራተኞች ማከናወናቸውን አክለዋል፡፡ ኩባንያው በለገደንቢ፣ በሳካሮ፣ በሻኪሶና በረጂ ከተሞች አካባቢ የወርቅ ማምረቻ እንዳሉት ይታወቃል፡፡ ለአሥር ዓመታት ባደረገው የማዕድን ፍለጋ 310 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጉንም ዶ/ር አረጋ አክለዋል፡፡ ሚድሮክ ጎልድ በመተከል አካባቢ ያገኘውን የወርቅ ማዕድን ልማት በ200 ሚሊዮን ዶላር ወይም 4.2 ቢሊዮን ብር ወጪ እ.ኤ.አ. በ2015 እንደሚጀምርም ጠቁመዋል፡፡

The post አላሙዲ በኦሮሚያ ክልል የተገኘው ከፍተኛ ክምችት ያለው የወርቅ ማዕድንን ሊያወጡ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

መድረክ በዶ/ር መረራ እና በቡልቻ ደመቅሳ አማካኝነት የተሳካ የምርጫ ቅስቀሳዎችን በኦሮሚያ ከተሞች እያደረገ ነው (ይናገራል ፎቶ)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የመድረክ አንዱ አካል የሆነው ኦፌኮን በኦሮሚያ ከተሞች የተሳኩ የምርጫ ቅስቀሳዎችን እያደረገ ነው:: ምንም እንኳ በገዢው ፓርቲ አባላት እና የደህንነት ሰዎች የመድረክ አባላት ከፍተኛ ውክቢያ እየተፈጸመባቸው ቢሆንም በአምቦ, አሪሲ, በወለጋ, በሻሸመኔ በአዳማና በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ሕዝቡ ግልብጥ ብሎ በመውጣት ለኦህዴድ/ኢሕአዴግ ቦታ እንደሌለው አሳይቷል:: በኦሮሚያ ክልል እየተደረጉ ባሉት ቅስቀሳዎች ዶ/ር መረራ ጉዲና እና ኦቦ ቡልቻ ደመቅሳ ከአባሎቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ጋር የሰሯቸውን ታሪኮች በፎቶ ይመልከቱ::
mederek
;

ambo merera

ambo 2

ambo 3

merera

dr merara

merera gudina 2

omromo 2

merara 3

bulcha

merera 3

merera 4

The post መድረክ በዶ/ር መረራ እና በቡልቻ ደመቅሳ አማካኝነት የተሳካ የምርጫ ቅስቀሳዎችን በኦሮሚያ ከተሞች እያደረገ ነው (ይናገራል ፎቶ) appeared first on Zehabesha Amharic.

መድረክ በኦሮሚያ ክልል ኦህዴድን እያንቀጠቀጠ ነው * ዶክተር መረራ ለቢቢኤን ይናገራሉ (ያልታዩ ቪዲዮችንም አካተናል)

“አይሲኤስ ወገኖቻችንን ሲገል እኛን ለማለያየት አስቦ ቢሆንም እኛ ግን አንድ ሆነን እየተረዳዳን ነው”–ጆሲ መልቲሚዲያ

$
0
0

jose in ze house1

ወንድማችን ጆሲ የሰማዕታት ቤተሰቦች ጋር ሀዘን በመድረስ ለቤተሰቦች ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር ባሰባሰበው ገንዘብ ሲረዳ ቆይቷል። ከማንም በፊት ለወገን ደራሽነቱን ያስመሰከረው ጆሲ የሱን ፈለግ ተከትለው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የእርዳታ እጆቻቸውን ሲዘረጉ ቆይተዋል።

አሉን የምንላቸው ከበርቴ የሀገራችን ሚዲያዎች እንኳን መስራት ያልቻሉትን በራሱ ወጪ እያንዳንዱ ቤተሰብ ጋር በሞጓዝ የተቻለው ሲረዳ ቆይቷል ይህ ሳያንስ ትኩረት እንዲያገኙ አስችሏል።

ጆሲ ከአዲስ አበባ ጎንደር ከዛ ትግራይ ከትግራይ ደግሞ ወልቂጤ እየዞረ ያዘኑትን ሲያረጋጋ ሲረዳ የቆየ ብርቅዬ ልጃችን ነው። አሁንም በአዲስ አበባ ሰማዕት ብርሃኑ ጌታነህ ቤተሰቦች ጋር በመሄድ ታሪክ መስራቱን ቀጥሏል።

ከዚህ በታች የምትመለከቱት ፅሁፍ የጆሲ መልዕክት ነው።
jose in ze house

የሁለት ልጆቿን አባት ፤የትዳር አጋሯን በሞት ከተጠነጠቀች፤ በሀዘን የተቆራመደችና ባዶ ቤት የታቀፈችን ሴት ማፅናናት በእርግጥ ከባድ ነው፡፡ ዛሬ ሁሉም ነገር ለእርሷና ለሁለት ልጆቿ ጨለማ ነው፡፡ ምክንያቱም የልጆቿን አባት ነውና በአይ ኤስ የግፍ ግድያ ያጣችው፡፡

ባለቤቷ ና እሷ ቋሚ ገቢ የሌላቸውና የግለሰብ ቤት ተከራይተው የሚኖሩ ሲሆን፤እሷ ኑሮአቸውን ለማሸነፍ በተለያየ ጊዜ ወደ አረብ ሀገራት ለስራ ሄዳ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካላት ነበር የተመለሰችው፡፡እሷ ውጪ ሀገር በነበረችበት ወቅት ሁለቱን ህፃናት የማሳደግ ኃላፊነት የወደቀው አሁን በሕይወት በሌለው ብርሃኑ ጌታነህ ላይ ነበር፡፡

ብርሃኑ የባለቤቱን፤የሚወዳቸውንና የሚሳሳላቸውን የሁለት ህፃናት ልጆቹን ሕይወት ለመቀየር አስቦ፤ ከግለሰብ ለተከራየው ቤት የሁለት ወር ኪራይ ቅድሚያ ከፍሎ ለባለቤቱ፤ለቤት አከራዮቹና ለቅርብ ወዳጆቹ ድሬድዋ ለስራ እንደሚሄድ ተናግሮ ተሰናብቶ ወጣ ፡፡ ግን ያመራው ወደ ሊቢያ ነበር፡፡ ካሰበው ሳይደርስ፤ህልሙን ሳያሳካ ፍቅራቸውን ያልጠገበውን ሁለት ልጆቹንና ባለቤቱን ጥሎ በሊቢያ በረሃ ውስጥ በአይ ኤስ በግፍ ተሰዋ፡፡
jose in z house

ጆሲ መልቲሚዲያ ሀዘንተኞቹን በቅንነት ለመደገፍ ከተነሱት ያሬድ ሹመቴና መሐመድ ካሳ ጋር በመሆን አዲስ አበባ በተለምዶ አዋሬ ተብሎ በሚጠራውና ብርሃኑ ከግለሰብ ተከራይቶ ከባለቤቱና ከሁለት ህፃናት ልጆቹ ጋር ይኖርበት ወደነበረው ቤት ሄዶ የተሰማውን ሀዘን ገልፆ ፤ ለባለቤቱና ለቅርብ ወዳጆቹ መፅናናትን ተመኝቶ ABC የመኪና ኪራይ በእርዳታ የለገሰውን ብር 40.000(አርባ ሺ ብር) ለባለቤቱ አስረክቧል ፡፡

በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉትንና እያደረጉ ያሉትን ግለሰቦችና ድርጅቶችን በመላው ኢትዮጽያውያን በተለይም ቤተሰቦቻቸውን በሞት በተነጠቁ ወገኖች ስም እናመሰግናለን ፡፡በነገራችን ላይ የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉትን ግለሰቦችና ድርጅቶች ስም የምንጠቅሰው ሌሎች ቅን አሳቢዎች አርያነታቸውን እንዲከተሉ በማሰብ እንደሆነ ለመግለፅ እንወዳለን ፡፡

ብርሃኑ ጌታነህ ጥሏቸው የሄደው ህፃናት የ 8 እና የ 4 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ናቸው፡፡ህፃናቱ መማር አለባቸው፡፡ለእዚህ ደግሞ የትምሕርት ቁሳ ቁስ ሊሞላላቸው ይገባል ፡፡ ቋሚ የሆነ መጠለያም ያስፈልጋቸዋል ፡፡ይህ ይሟላላቸው ዘንድ የሁላችንንም ድጋፍ ይሻሉ፡፡
jose in the house

አይ. ኤስ የተባለው ፅንፈኛ ቡድን በኢትዮጽያውያን ወገኖቻችን ላይ ጭካኔ የተሞላበት የግፍ ግድያ ሲፈፅም ዓላማው በልዩነት እንድንጋጭ ፤እርስ በእርስ እንድንናቆር ፤ፍቅራችን እንዲከስምና አንድነታችን እንዲላላ ወጥኖ ቢሆንም እኛ ግን ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችንን አፅንተንና ከመራራቅ ይልቅ ተቀራርበን ሀዘን ከጎዳቸው ወገኖቻችን በተለይም የቤታቸውን ምሶሶ ካጡት ከብርሃኑ ባለቤትና ከሁለቱ ህፃናት ጎን ልንሰለፍ ይገባል፡፡…ይህ የጆሲ መልቲሚዲያ መልዕክት ነው፡፡
ፈጣሪ ሁላችንንም ያፅናናን ፡፡

ጆሲ መልቲሚዲያ

The post “አይሲኤስ ወገኖቻችንን ሲገል እኛን ለማለያየት አስቦ ቢሆንም እኛ ግን አንድ ሆነን እየተረዳዳን ነው” – ጆሲ መልቲሚዲያ appeared first on Zehabesha Amharic.

“በቃኝ”–ሃይሌ ገብረሥላሴ

$
0
0

haile retires zehabesha gebresilase

(ዘ-ሐበሻ) ላለፉት 25 ዓመታት ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ በአትሌቲክስ መድረክ ስሟን ከፍ አድርጎ ሲያስጠራ የከረመው አትሌት ሃይሌ ገብረሥላሴ ሩጫ በቃኝ አለ::

አትሌቱ በታላቁ የማንቸስተር ሩጫ 16ኛ ሆኖ ከጨረሰ በኋላ ለቢቢሲ በሰጠው መግለጫ “ካሁን በኋላ የሩጫ ውድድር በቃኝ” ብሏል::

ዘ-ሐበሻ ያሰባሰበችው መረጃ እንደሚያመለክተው የ42 ዓመቱ ጎልማሳ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴኤ 2 ጊዜ የኦሎምፒክ ሜዳሊያዎችን; ስምንት ግዜ የዓለም ሻምፒዮናነት ክብርን እንዲሁም 27 ጊዜ የዓለም ሪከርዶችን በመስበር ታሪክ ሰርቷል::

“ከሩጫ ውድድር ካሁን በኋላ መሳተፌን ባቆምም በግሌ መሮጤን ግን አላቆምም; ከመሮጥ መቆጠብብም የለም ምክንያቱም ሕይወቴ ነው” ያለው ኃይሌ ከዚህ በፊትም ሩጫ አቁሜያለሁ ብሎ በድጋሚ ወደ ውድድር መምጣቱን ዘገባው ጨምሮ ጠቅሷል::

The post “በቃኝ” – ሃይሌ ገብረሥላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 2784 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>