730 ቀናት ለሃይማኖት ነፃነት (730 Days For Religious Freedom) ዘጋቢ ፊልም ይፋ ሆነ
Hiber Radio: ሱዳን በአገሯ የኢትዮጵያ አማጺያንን እያሰለጠነች መሆኑ ተገለጸ
የህብር ሬዲዮ የካቲት 23 ቀን 2006 ፕሮግራም
እንኳን ለአድዋ ድል 118ኛው በዓል አደረሳችሁ!!
ዶ/ር አክሎግ ቢራራ የቀድሞው የዓለም ባንክ የኢኮኖሚ አማካሪ ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ቃለ ምልልስ(ሙሉውን ያዳምጡ)
<...የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ሕዝቦች ድል ነው ይሄን ማንም አይነጥቀንም ። ዛሬ ለሚረገጠው መብታችን ግን አባቶቻችን አንድ ላይ እንደቆሙት በጋራ መቆም አለብን ...>
አቶ ስዩም መንገሻ የአንድነት ዋና ጸሐፊ የአድዋን 118ኛ በዓልን በአዲስ አበባ ስላከበሩበት ሁኔታ ተጠይቀው ከሰጡት ምላሽ(ሙሉውን ያዳምጡት)
<<...ለረዳት አብራሪው ሀይለመድህን አበራ ፊርማ ማሰባሰብ ጀምረናል ።ፊርማው ለስዊዝ ባለስልጣናት የሚቀርብ ነው...>>
አቶ ጴጥሮስ አሸናፊ ረዳት አብራሪው እንዲፈታ ጥረት የሚያደርገው ግብረ ሀይል አባል ለህብር ከሰጡት ቃለ ምልልስ የተወሰደ
የህብር ሬዲዮ አራተኛ ዓመት በዓል ልዩ ሪፖርት
ሌሎችም ዝግጅቶች
ዜናዎቻችን
- ሙስና ኢትዮጵያን እያጠፋት መሆኑን የቀድሞው የዓለም ባንክ የኢኮኖሚ አማካሪ ገለጹ
- ሱዳን በአገሯ የኢትዮጵያ አማጺያንን እያሰለጠነች መሆኑ ተገለጸ
- ኢትዮጵያውያን ግፍ በዛብን ብለው የሳውዲን እስር ቤት ሰብረው ወጡ
* ጩኸትና የጥይት ተኩስ ተሰምቷል
- የአድዋ ድልን መዘከር ብቻ ሳይሆን በአንድ ላይ ቆመው ለመብታቸው እንዲታገሉ ጥሪ ቀረበ
- ተቃዋሚዎችም እንዲተባበሩ ተጠይቋል
- ኩዌት ኢትዮጵአውያን የጉልበት ሰራተኞችን አልቀበልም አለች
- ረ/አብራሪ ሀይለመድህንን የስዊዝ መንግስት ጥገኝነት እንዲሰጠው የሚጠይቅ ፊርማ መሰብሰብ ተጀመረ
- የመጀመሪያው ድሪም ላይነር አብራሪና የአየር መንገዱ ም/የስራ ሀላፊ በፈቃዳቸው ለቀቁ ተባለ
- አንድነት በባህር ዳር ያደረኩትን ተቃውሞ አዲስ አበባን ጨምሮ በ12 የአገሪቱ ከተሞች ይቀጥላል አለ
ሌሎችም ዜናዎች አሉ
የዋሽንግተንና የአዲስ አበባ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየተተቸ ነው
“በሙስና በእምነት ማጉደል በማታለልና በአመለካከት የሚለዩን ዝም በማሰኘት ሐይልን የያዛችሁ በተሳሳተ የታሪክ ገጽታ ላይ ነው ያላችሁት! ቡጢያቹን የምትፈቱ ከሆነ እጅ እንዘረጋላችሗለን” ያሉት ኦባማ አንባገነናዊ ቡጢያቸዉን ካልፈቱ…አንባገነናዉያን ጋር እጃቸዉን ዘርግተዉ ሲጨባበጡ መታየታቸዉ ትዝብት ላይ እየጣላቸዉ ነዉ!
ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 24/2006 (ቢቢኤን) ፦ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉን ገደብየለሽ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማመላከት ያደረጋቸዉን ጥናቶች ዋቢ በማድረግ በየካቲት 20/2006 ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።መሰረቱን አርሊንግተን ቨርጂኒያ ያደረገዉ ፖለቲኮ የሚባለዉ ጋዜጣ/መጽሔት የኦባማ አስተዳደር የኢትዮጵያ መንግስትን ከመሰሉ ለነጻነት ምቹ ካልሆኑ አገራት ጋር ያለዉ ምጸታዊ የዲፕሎማሲ ቁርኝትንም ይተቻል።
ከቀዝቃዛዉ ጦርነት ጀምሮ የዩናይትድ እስቴትስ መንግስታት ዜጎቻቸዉን ከሚጨቁኑ አገራት ጋር ግንኙነት ለመመስረት እምብዛም እንደማይጥሩ ፖለቲኮ እየገለጸ፤ለሚዛናዊነቱ ተስፋ የተጣለበት የኦባማ ካቢኔ ከሌሎቹ የዩናይትድ እስቴትስ ፕሬዝዳንቶች በባሰ መልኩ ለዜጎቻቸዉ ደህነነት ምቹ ካልሆኑ 25 አገራት ጋር ግንኙነት አለዉ ሲል የኦባማን የብሐራዊ ደህነነትና ጥበቃ አማካሪ የሆኑትን ሱዛን ራይስ ንግግርን በዋቢነት ያቀርባል። ራይስ “ግልፅ እንሁን አንዳንዴ እኛ አጥብቀን የምንይዛቸዉን ዉድ የሆኑ መብቶችን ከማያከብሩ መንግስታት ጋር የስራ ግንኙነት አለን” በማለት በባለፈዉ የነሐሴ ወር መናገራቸዉን ፖለቲኮ ይገልጻል።
ፖለቲኮ ለነጻነት የማይመቹ ብሎ ከጠራቸዉ 25 አገራት ዉስጥ ኢትዮጵያን በቁጥር 11 ላይ ያስቀመጠ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማሪያም ደሳለኝ ይመሯታል የምትባለዋ ኢትዮጵያ የጸረ-ሽብር ህጓን ፖለቲከኞችን፣አክቲቪስቶችን፣መንግስትን ተጠያቂ የሚያደርጉ አካላትን ለማሰር እንደ ማህተም ትጠቀምበታለች ሲል ተጠያቂ ያደርጋል።ፖለቲኮ አክሎም የመለስ ዜናዊ አስተዳደር በ1999 ሶማሊያን በመዉረር እራሱን ለዩናይትድ እስቴትስ ግልጋሎት ማቅረቡንያስረዳል። ይህንንኑ አጋጣሚ በመጠቀም በአሜሪካ የሰለጠኑ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከብሔር ብሔረሰቦች የተነሱ አማጺያንን ለማስቆም የጦርነት ወንጀል መፈጸማቸዉ በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ክስ ቢቀርብበትም ዋሽንግተን አዲስ አበባን በዲፕሎማሲ “እቅፍ-እቅፍቅፍ” እያደረገች መቀጠሏን ገልጿል።
ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትን ይጥሳሉ ከሚባሉት ጭቋኝ አገራት ጎራ ብትመደብም ፤እንደ አዉሮፒኣይኑ ቀመር በ2008 ብቻ ከዩናይትድ እስቴትስ 969 ሚሊዮን ዶላር በእርዳታ ተቀብላለች!
በኢትዮጵያ ዉስጥ ቀጣይ የሆነ የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ግድያ፣እስር፣የሐይማኖትነጻነትን መነፈግ፣የፕሬስ ነጻነት መመንመን፣የመማርና ማስተማር ሒደት ነጻነት በመንግስት መዳፍ ዉስጥ መግባት፣የመደራጀት-የመሰባሰብ-ሐሳብን በነጻ የመግለጽ ሁለንተናዊ መብት፣ የፍርድ ቤት አሰራር መበላሽትና በስልጣን መባለግን በመተንተን የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በየካቲት 20/2006 አመታዊ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል። የኦባማ አስተዳደር አካል የሆነዉ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አሳቃቂ የሆነ የመብት ረገጣ ኢትዮጵያ ዉስጥ መኖሩን እያወጀ የኦባማዉ ቤተ-መንግስት ኢትዮጵያን ከመሰሉ በአንባገነናዉያን ከሚመሩ አገራት ጋር “መለስ-ቀለስ” ማለቱ እያስተቸዉ ነው። የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱን የሚመሩት ጃን ኬሪ አገራቸዉ ከስህተት የጠራች አለመሆኗን ያስረዳሉ።
“ዛሬ ስለ ሌሎች አገራት ያለዉ ሪፖርት ይፋ ለማድረግ ብንመጣም፤ እዚሁ አገራችን ላይ እራሳችንን በከፍተኛ መልኩ ተጠያቂ እናደርጋለን! እንከን የለሽ አለመሆናችንን እናዉቃለን” ጃን ኬሪ።
ጃን ኬሪ መስሪያቤታቸዉ ይፋ ያደረገዉ የሰብዓዊ መብት ሪፖርት ዋሽንግተን ዲሲ ባሉ የመስሪያ ቤቱ አባላት ጥናት ብቻ የተዘጋጀ ሳይሆን በእያንዱ አገራት ያሉ ኤምባሲዎችና ቆንስላ ጽ/ቤቶች ተሳታፊ መሆናቸውን ሲያስረዱ “በመላዉ አለም ያሉ ኤምባሲዎችና ቆንስላ ጽ/ቤቶች በጥናት እንደዚሁም እነዚህን ጽሁፎችን በመጻፍ አክቲቪስቶችን በመቅረብ መንግስታትን በማናገር የኤንጂኦና የሚዲያ ሪፖርቶችን በመተንተን አያሌ ሰአታትን አባክነዋል”ሲሉም ገልጸዋል።
ኬሪ ለነጻነትና ለመብት በሚደረግ ጥረት ዉስጥ ግለሰባዊ ሚና የጎላ መሆኑን መሆኑንም ይገልፃሉ።ከተለያዩ አገራት የለዉጥ ተምሳሊት የሚሏቸዉን ግለሰቦችን ስም በማንሳት የኢትዮጲያዉን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሚናን አድንቀዋል “እስክንድር ነጋ ሐሳብን በነጻ ስለመግለጽ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚጽፍ ነው” ብለዋል።
በሚያዚያ 4/2004 የፔን አሜሪካን ሽልማትን ያገኘዉ እስክንድር ነጋ አለም አቀፋዊ ትኩረትን ያገኘ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ነዉ። የኢትዮጵያ መንግስት በሽብር ፈጠራ ወንጅሎት ከመስከረም 3/2003 ጀምሮ በእስር ላይ ይገኛል።
የዩናይትድ እስቴስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ነጻነትን ከሚነጥቁ ጥቂቶች ጋር ሳይሆን ነጻነትን ከተነፈጉ ብዙሗን አጋር በመሆን አብሮ እንደሚቆም ኬሪ ቃላቸዉን እያደሱ ይናገራሉ “ዛሬ ቃላችንን በድጋሚ ለማረጋገጥ እንወዳለን! ክብርን ከሚነፍጉ ጥቂቶች ጋር ሳይሆን ክብርን ከሚሹ ብዙሗን ጋር አብረን ለመቆም ዝግጁ መሆናችንንም ለመግለጽ እንወዳለን!”በማለት ቢያስረዱም መንግስታቸዉ ከጨቋኝ አንባገነናዊያን ጋር በሚያደርገዉ ዲፕሎማሲያዊ ቅርርብ ተጠያቂ እየሆነ ነው።
በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ብዙ ቃልኪዳን የገቡት በራክ ኦባማ ቃሊኪዳናቸዉ አለተፈጸመም። በተመሳሳይ መልኩ ያሁኑ የዉጭ ጉዳይ መስራያ ቤት ሐላፊ ጃን ኬሪም ሆኑ የቀድሞዋ ሒላሪ ክሊንተን ከአንባገነናዊያን ጋር ያለዉን ግንኙነት ሲያደረጁ እንጂ ሲያመነምኑ አልተስተዋለም በማለት በርካታ ምሁራን፣ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ ተንታኞች ወቀሳ ያቀርቡባቸዋል።
በጥር 12/2001 ቃለመሃላ የፈጸሙት ፕሬዝዳንት ኦባማ ሰላምና ክብርን ለሚሹ የአለማችን ዜጎች የርሳቸዉ መመረጥ ብስራት እንደሆነ አመላክተዉ ነበር። ከትላላቅ የአለማችን መዲናዎች ጀምሮ ወላጅ አባታቸዉ እስከመጡበት የኬኒያ መንደር የተስፋ ቃል ነበራቸዉ! እንዲም በማለት ስሜትን በሚነካ መልኩ ተናግረዉ ነበር…
“ከትላልቆቹ መዲናዎች እስከ አባቴ የተወለደባት መንደር ዛሬ ለሚመለከቱን ህዝቦችና መንግስታት፤ አሁን አሜሪካ የእያንዳንዱ አገር የእያንዳንዱ ግለሰብ ወዳጅ ናት! ሰላምና ክብርን ለሚፈልጉ ሴቶችና ህጻናት ዳግም ለመምራት ዝግጁ ነን” ፕሬዝዳንት በራክ ኦባማ።
ኦባማ ምንጫቸዉ ለሆነችዋ አፍሪካ ፕሬዝዳንታዊ ሐይላቸዉን በመጠቅም ያበረከቱት አስተዋፅኦ አናሳ ነዉ።ፕሬዝዳንቱ ቃለመሃላቸዉን ሲፈጽሙ ስልጣንን በማጭበርበር-በሙስናና የሐሳብ ልዩነትን በማፈን በሚቆናጠጡ አንባገነናዉያን ላይ ጣታቸዉን ቢቀስሩም ከነዚህ ምቹ ያልሆኑ አሳፍሪ መንግስታት ጋር እርሳቸዉም ይሁን ካቢኔአቸዉ ዲፕሎማሲያዊ ገደብን አለማበጀቱ አጠያያቂ እየሆነ ነዉ።
በአሜሪካዋ መዲና በዋሽንግተን ዲሲ ጥር 12/ 2001 ቀዝቃዉ አየር በጭብጨባ እየሞቀ ብዙዎች እያለቀሱ ኦባማ ለአንባገነናዊያን መልእክት አስተላልፈዋል።
“በሙስና በእምነት ማጉደል በማታለልና በአመለካከት የሚለዩን ዝም በማሰኘት ሐይልን የያዛችሁ በተሳሳተ የታሪክ ገጽታ ላይ ነው ያላችሁት! ቡጢያቹን የምትፈቱ ከሆነ እጅ እንዘረጋላችሗለን” ያሉት ኦባማ አንባገነናዊ ቡጢያቸዉን ካልፈቱ አንባገነናዉያን ጋር እጃቸዉን ዘርግተዉ ሲጨባበጡ መታየታቸዉ ትዝብት ላይ እየጣላቸዉ ነዉ።
ብዙ የተገቡ ቃልኪዳስኖች ተግባራዊ ሳይሆኑ በየካቲት 20/2006 ከዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአመቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሲታወጅ “ከነጻነት ፈላጊዎች ጋር እንቆማለን!” የሚል ቃልኪዳን ተገብቷል።የዩናይትድ እስቴትስ መንግስት ባወጣዉ የሰብዓዊ መብት ሪፖርት የኢትዮጵያን መንግስት “ጨቋኝ-አፋኝ-አሳሪ-ገዳይ-ኢዲሞክራሲያዊ” መሆኑን ይፋ አድርጓል። ፖለቲኮ ጋዜጣ/መጽሔት ይህ ሪፖርት በወጣበት ማግስት የኦባማ አስተዳደር ኢትዮጵያን ከመሰሉ ለዜጎቻቸዉ ምቹ ካልሆኑ አገራት ጋር ይወዳጃል ሲል ይተቻል።
የዲሞክራሲ ተምሳሊት ነን የሚሉ የምእራቡ አገራት ለአንባገነናዊያን ዲፖሎማሲያዊ ከለላ መስጠታቸው የጥቅም ትስስር ወይስ ምጸታዊ የሆነ የዲፕሎማሲ ጨወታ? የሚለዉ ጥያቄ ቢነሳም …ትችቱእንደቀጠለ ነዉ።
በአላሙዲ የሚደገፈው ፌዴሬሽን ዲሲን ጥሎ በሚኒሶታ የዘንድሮውን ዝግጅት ሊያደርግ ነው
“ዲሲን ለቀው መሄዳቸው ለእኛ ኢትዮጵያውያን ትልቅ ድል ነው”
- በዲሲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን
(በዲሲ አላሙዲንን ለመቃወም በከተማው ሲዘዋወር የነበረው መኪና ይህን ይመስል ነበር)
(ዜና ትንታኔ) ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተሰባሰቡበትን ፌዴሬሽን ለሁለት ለመክፈል ተንቀሳቅሷል የሚባለው የወያኔ/ኢሕአዴግ ሥርዓት በአላሙዲ ስፖንሰርነት የሰሜን አሜሪካውን አመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል ለመክፈል ቢጥርም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ነባሩን ፌዴሬሽን በማመከተል አሸናፊ መሆናቸው ባለፉት ሁለት ዓመታት በዳላስ እና በዋሽንግተን ዲሲ ታይቷል።
በሼህ መሃመድ አላሙዲ የሚደገፈውና የወያኔ ፌዴሬሽን እየተባለ የሚጠቀሰው aesaone ራሱን ተለጣፊ አድርጎ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ዓመታዊ ዝግጅታቸውን በሚያደርጉበት ሳምንት ላለፉት 2 ዓመታት ሲያደርግ ባዶ ስታዲየም ከመታቀፍ ውጭ የሕዝብን ቀልብ ሊያገኝ እንዳልቻለ በግልጽ የታየ ጉዳይ ነው። እንደ ዋሽንግተን ፖስት ያሉ ሚዲያዎች ሳይቀሩ 2 ሚሊዮን ዶላር የወጣበት ዝግጅት የተገኘው ሰው ቁጥር ያስገርማል እስከማለት ዘግበው ነበር። ኢትዮጵያውያኑ ይህንን የአላሙዲ እግር ኳስ ቦይኮት በማድረጋቸው በስታዲየሙ ከሚገኘው ሰው ይልቅ ከውጭ ሆኖ የሚቃወመው ሰው ይበልጥ እንደነበር በተደጋጋሚ በሚዲያዎች መዘገቡም አይዘነጋም።
በሼህ አላሙዲ የሚደገፈው ፌዴሬሽን ለ3 ተከታታይ ዓመታት በዋሽንግተን ዲሲ የኳስ ውድድሩን እንደሚያደርግ ቀድሞ የገለጸ ቢሆንም፤ በተለይ አምና በዲሲ በተደረገው ዝግጅት ኢትዮጵያዊያኑ የአላሙዲ አፍ በደም ተጨማልቆ የሚያሳይ ፎቶ በትልቅ መኪና ተሰቅሎ በከተማዋ ሲንቀሳቀስ፤ አላሙዲ ባረፉበት ሆቴል አጠገብ ቆሞ ሲውል፤ ሆቴላቸው ውስጥ ሳይቀር ሕዝቡ አላሙዲንን እየተቃወመ የኳስ ውድድራቸውን “በደማችን ጨዋታ ይብቃ” በሚል ስያሜ በመስጠት ከተቃወማቸው በኋላ አላሙዲ ያልጠበቁት ጉዳይ ስለሆነ ወዲያውኑ ውድድሩን አቋርጠው ወደ መጡበት አፍረው እንደተመለሱ በወቅቱ በተለያዩ ሚዲያዎች ተዘግቧል።
አሜሪካ ያለን ኢትዮጵያውያን በገንዘብ አንገዛም፤ እኛ የደም ገንዘብ አንበላም፤ ከደም ገንዘብ ጋርም አንተባበርም በሚል ይህን የስፖርት ፌስቲቫል ቦይኮት ካደረጉ በኋላ የአላሙዲው ፌዴሬሽን ኳሱን ለ3 ዓመት ከከፈለበት የዋሽንግተን ዲሲው RFK ስታዲየም በመቀየር ወደ ሚኒሶታ እንደተዟዟረ የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች አስታውቀዋል።
ከውስጥ አዋቂዎች መረጃ እንደተረዳነው አላሙዲ እንዲህ ያለ ተቃውሞ ይደርስብኛል ብለው ሳያስቡ በዋሽንግተን ዲሲ አፍረው ተመልሰዋል፤ ይህን ተከትሎም ዋናውን የኢትዮጵያውያን ፌዴሬሽኑ ገንጥለው የወጡትን አመራሮች ይኸው የአላሙዲ ፌዴሬሽን ያባረረ ሲሆን በዲሲ ላለፉት 2 ዓመት የታየውን ባዶ ስታዲየምና ተቃውሞ በሚኒሶታ አያጋጥመንም በሚል ኳሱ ዘንድሮ በሚኒሶታ ይደረጋል። በዚህም መሠረት ከጁን 29 እስከ ጁላይ 5 በሚኒሶታ ይህ ቶርናመንት እንደሚካሄድ ለማረጋገጥ ተችሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በዲሲ የአላሙዲንን ኳስ ቦይኮት በማድረግ “ላለፉት 2 ዓመታት ያስተባበሩ ወገኖች ይህ ለኢትዮጵያውያን ትልቅ ድል ነው፤ የኛን ቦይኮት ፈርተው መፈርጠጣቸው ያስደስታል፤ በሚኒሶታም ተመሳሳይ ቦይኮት እንደሚገጥማቸው እንተማመናለን” በሚል በሶሻል ሚዲያዎች እየገለጹ ነው። እንደነዚህ አስተያየት ሰጪዎች “ለ3 ዓመት ኮንትራት ፈርመው በ2 ዓመታቸው ለቀው መውጣታቸው የኢትዮጵያውያን የትግል ውጤት ነው።”
ኢትዮጵያ እየከሳች አላሙዲ በሃብት እየወፈሩ ነው፤ የዓለማችን 61ኛው ቢሊየነር ሆኑ
(ዘ-ሐበሻ) ታዋቂው የዓለማችን የቢዝነስ መጽሔት ፎርብስ በየዓመቱ የዓለማችንን ቢሊየነሮች ደረጃ የሚያሳውቅበትን መረጃ ይፋ አደረገ። ባለፈው ዓመት የዓለማችን ሁለተኛው ሃብታም የነበሩት የማይክሮሶፍት ባለቤት ቢል ጌትስ የዓለማችን አንደኛ ቢሊየነር ሲሆኑ የፌስቡክ ባለቤት ማርክ ዙከምበርግ 21ኛው የዓለማችን ቢሊየነር ሆኗል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በመሬት ነጠቃ የሚከሰሱት ሼህ መሀመድ አላሙዲ የዓለማችን የሃብታምነት ደረጃቸው ከዓመት ዓመት እድገት እያሳየ አምና ከነበሩበት የ65ኛ ደረጃ 4 ደረጃዎችን በማሻሻል የዓለማችን 61ኛው ሃብታም ሆነው በመጽሔቱ ተቀምጠዋል። እንደ ፎርብስ ገለጻ የ8 ልጆች አባት የሆኑት በአባታቸው የሳዑዲ፤ በእናታቸው ደግሞ ኢትዮጵያዊ የሆኑት አላሙዲ $15.3 ቢሊዮን አላቸው።
ከሳዑዲ አረቢያ ሃብታሞች መካከል ሁለተኛው የሆኑት አላሙዲ የወያኔ/ኢሕአዴግ ደጋፊ ከመሆናቸውም በላይ፤ ከስር ዓቱ ጋር በፈጠሩት ስር የሰደደ ወዳጅነት በአድልዎ አብዛኛው የኢትዮጵያ ወሳኝ የንግድ ተቋማት በርሳቸው ስር እንዲያዙ ትልቅ ውለታ እንደተዋለላቸው በተደጋጋሚ እንደሚተቹ የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ። ምንም እንኳ ሼኩ በነዳጅ ዘይት ሽያጭ ላይ የተሰማሩ ቢሆኑም በተለይም የኢትዮጵያን ወርቅ በእርሳቸው ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ የሰውዬው ሃብት ከእለት ወደ ዕለት እንዲጨምር አስችሎታል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ።
የፕላኔታችን 10ሩ ቢሊነሮች የሚከተሉት ናቸው።
1ኛ. ቢል ጌትስ 76 ቢሊዮን ዶላር
2ኛ. ቻርሎስ ሳሊም ሄሉ 72 ቢሊዮን ዶላር
3ኛ. አማሪኮ ኦርቴጋ 64 ቢሊዮን ዶላር
4ኛ. ዋረን ብፌት 58.2 ቢሊዮን ዶላር
5ኛ. ላሪ ኤልሰን 48 ቢሊዮን ዶላር
6ኛ. ቻርለስ ኮች 40 ቢሊዮን ዶላር
7ኛ. ዳቪድ ኮች 40 ቢሊዮን ዶላር
8ኛ. ሼልደን አንደርሰን 38 ቢሊዮን ዶላር
9ኛ. ክርስቲ ዋልተን እና ቤተሰቦቿ 36.7 ቢሊዮን ዶላር
10ኛ. ጂም ዋልተን 34. 7 ቢሊዮን ዶላር
የፌስቡክ ባለቤት ማርክ ዙከርበርግ በ28.5 ቢሊዮን ዶላር 21ኛ፣ አላሙዲ በ15.3 ቢሊዮን ዶላር 61ኛ፣ ቸልሲ ስፖርት ክለብ ባለቤት ኢብራሞቪች በ9.2 ቢሊዮን ዶላር 137ኛ ሆነዋል።
(ሰበር ዜና) አንድ ሰው ከተገደለ በኋላ ሹፌሮች ባደረጉት አድማ ከአዲስ አበባ ጅቡቲ የሚወስደው መንገድ ከተዘጋ 3 ቀን ሆነው
(ዘ-ሐበሻ) ከአዲስ አበባ ጅቡቲ የሚወስደው መንገድ ከተዘጋ 3 ቀን እንደሞላው በአካባቢው የከባድ ሹፌር አሽከርካሪዎች ለዘ-ሐበሻ ገለጹ። እነዚህ ሹፌሮች እንዳስታወቁት ይህ መንገድ የተዘጋው የከባድ መኪና ሹፌሮች ባደረጉት አድማ የተነሳ ነው።
ለዘ-ሐበሻ መረጃ ያቀበሉት ሹፌሮች እንደገለጹት ለከባድ መኪና አሽከርካሪዎቹ የሥራ ማቆም አድማ ምክንያት የሆነው አንድ ሹፌር ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ መንገድ ላይ በመገኘቱ የተነሳ ነው። በገዋኔ አካባቢ ይህ መንገድ እንደተዘጋ የገለጹት ሾፌሮቹ መንገዱ በመዘጋቱ የተነሳ የቆሙት መኪኖች ብዛት በኪሎ ሜትር እንደሚቆጠር አስታውቀዋል።
የስራ ማቆም አድማ ያደረጉት እነዚሁ ሹፌሮች ጥያቄያቸው የደህነንት ዋስትና እንደሆነ የገለጹት ምንጮቹ በአሁኑ ወቅት በፖሊስ ተከበው እንደሚገኙ የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
የኢሕአዴግ መንግስት ህጋዊ በሆነ መንገድ ለዕረፍት ከሳውዲ አረቢያ ወደ ኢትዮጵያ በሚገቡ ወገኖቻችን ላይ የጉዞ እገዳ ጣለ
ኢትዮጵያ ሃገሬ ከጂዳ
ኢትዮጵያውያኑ የእረፍት ግዜያቸውን ዱባይ እና ባህሬን ለማስላፍ ተገደዋል!ከሳውዲ አረቢያ ወደ ሃገራቸው ለዕረፍት አሊያም ለተለያዩ አስቸኳይ የስራ ጉዳዮች በሚጓዙ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ወደ መጡበት እንዳይመለሱ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግመ ንግስት የጉዞ እገዳ መጣሉን ምንጮች አስታወቁ። የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት እየወስደ ያለው እርምጃ አያሌ ወገኖቻች በሰው ሃገር ያፈሩትን ቀዋሚ እና ተንቀሳቃሽ ንብረቶቻቸውን ያሳጣ ዜጎች ህጋዊ ሆነው ለመኖር የሚያስችሉ መብቶቻውን የነፈገ ከመሆኑም በላይ አብዛኛውን ተጓዥ ለምዝበራ እና ለተጨማሪ ወጪ የዳረገ አሰራር መሆኑንን የሚገልጹ እነዚህ ምንጮች በባዕዳን ሃገር ህጋዊ በሆነ መንገድ የሚኖረውን ወገናችንን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ እርምጃ መሆኑ አክለው ገልጸዋል።
አዲስ አበባ ኤርፖርት ላይ በኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ደህንነት ሃይሎች እየተፈጸመ ያለው የጉዞ እገዳ ህጋዊ የሆነ መስረት የሌለው መሆኑን የሚናገሩ የእገዳው ሰላባዎች አንዳንድ ተጓዦች የቪዛ ግዜያቸው መቃጠሉን ተከትሎ ህገወጥ፡ በሆነ መንገድ ባህር አቋርጠው ወደ ሳውዲ አረቢያ ለመግባት መገደዳቸውን ተናግረዋል። መንግስት አዲስ አበባ ኤርፖርት ላይ እyeተፈጸመብን ያለው ወከባ ሳውዲያኑ ከሚፈጽሙብን ግፍ እና በደል የከፋ መሆኑንን የገለጹ አንድ ተበዳይ ለይለፍ 5 ሺህ ብር እጅ መንሻ መክፈላቸውን ጠቅሰው ወደ ሳውዲ ዓረቢያ ህጋዊ በሆነ መንገድ መግባት የሚያስችለን ህጋዊ ቪዛ እያለን ከሃገር ሃገር የመጓጓዝ ህገ መንግስታዊ መብታችን በህገወጦች ተጭፍልቋል ብለዋል።
ይህ በዚህ እንዳለ ለዕረፍት ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት እቅድ ይዘው የነበሩ ወገኖቻች በጉዞ እግደዳው ምክንያት የእረፍት ግዚያቸውን ጓረቤት ሃገራት ለማሳለፍ መገደዳቸውን በማውሳት ኤርትራውያንን ጨምሮ የሌላ ሃገር ዜግነት ያላቸው ተጓዦች ያለምንም ስጋት በነጻነት ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡም ሆነ ሲወጡ ኤርፖርት ላይ በደህንነት ሃይላቱ የሳውዲ የመኖሪያ ፈቃድ (ኢቃማ) እንደማይጠየቁ ጠቅሰው የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መግንስት እገዳውን የጣለው በኢትዮጵያን ላይ ብቻ መሆኑንን አረጋግጠዋል ።
መንግስት የሳውዲን መኖሪያ ፈቃዱ (ኢቃማ) ያልያዘ ኢትዮጵያዊያን ላይ የጉዞ እገዳ መጣሉ በጣም አሳፋሪ እና እርምጃው ጥናት ያልተደረገበት መሆኑንን የሚናገሩ ምንጮች የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ.መንግስት በሳውዲ አረቢያ ስለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አኗኗር በቂ ግንዛቤ እና መረጃ የሌለው መሆኑንን ያሳያል ብለዋል ። በሳውዲ አረቢያ ህግ አንድ የውጭ ሃገር ዜጋ የስራ ግዜውን ጨርሷ አሊያም ለእረፈት ወደ ሃገሩ ሲመለስ የመኖሪያ ፈቃዱን (ኢቃማውን) ለአሰሪው (ለከፊሉ) የማስረከብ ግዴታ እንዳለበት የሳውዲ አረቢያ ህግ ይደነግጋል ።
የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች ቅሬታቸው ገለፁ (ከአብርሃ ደስታ)
ባሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል የዉኃና አፈር ጥበቃ (Water and Soil Conservation, ማይን ሓመድን ዕቀባ) ተግባራት የሚከናወኑበት ግዜ ነው። ህዝብ ስራው ትቶ ተገዶ በፕሮግራሙ ይሳተፋል። ለፖለቲካ ሲባል ህዝብ በፍላጎቱ ተሳተፈ ተብሎ ሪፖርት ይቀርባል። እውነታው ግን ሌላ ነው። በየዓመቱ ህዝብ ሳያምንበት ተገዶ ይሰራል። በግዜው ያልሰራ እስከ ሦስት መቶ (300) ብር ተቀጥቶ ይሰራል። በዚሁ ምክንያት ብዙ ሌሎች የግል ሥራዎች ይቆማሉ። ዜጎች ብዙ ኪሳራ ይደርስባቸዋል።
የዉኃና አፈር ጥበቃ ሥራ የጉልበት ስራ ነው። መስራት የሚችል ይሰራል፣ ወይ እንዲሰራ ይገደዳል። በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ጣብያ ሩባ ፈለግ ግን ለየት ያለ ጉዳይ ተከስቷል። የዓፅቢ ወንበርታ ህዝብ በህወሓት የትጥቅ ትግል ወቅት ንቁ ተሳታፊ የመኖሩ ያህል ባከባቢው ብዙ አካል ጉዳተኞች (የቀድሞ ታጋዮች) አሉ። በጉልበት ስራ መሰማራት አይችሉም። ምክንያቱም አካላቸው ጎድሏል። እናም በጡረታ ገንዘብ በገጠር ህይወት ነው የሚኖሩ። የአካል ጉዳተኞች መሆናቸው ታውቆ ላለፉት ሃያ ሦስት (23) ዓመታት በዉሃና አፈር ጥበቃ ሥራ ተሳትፈው አያውቁም። ምክንያቱም አካላዊ ቁመናቸው አይፈቅድላቸውም፤ ግማሾቹ ዓይናቸው የጠፋ ግማሾቹ እግራቸው የተቆረጠ ወዘተ ናቸው።
አሁን ግን ለመጀመርያ ግዜ በተለየ ሁኔታ አካላቸው የጎደሉ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች በዉኃና አፈር ጥበቃ ፕሮግራሙ እንዲሳተፉ በመንግስት አካላት እየተገደዱ ይገኛሉ። ለምን አሁን እነሱን ማስገደድ ተጀመረ? የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ በመልካም አስተዳደር እጦት ምክንያት በመንግስት አካላት ላይ ተቃውሞ አስነስቶ ነበረ። ህወሓቶች የቀድሞ ታጋዮቹ ዒላማ አድርገው በዉኃና አፈር ጥበቃ እንዲሳተፉ ያስገደዱበት ምክንያትም ህዝብ ፀረመንግስት ሲነሳ የቀድሞ ታጋዮቹ ከመንግስት ጎን ከመሰለፍ ይልቅ የህዝቡን ጥያቄ በመደገፋቸው ነው። ታጋዮቹ ዓፈና በዝቷል፤ ለዚህ አይደለም መስዋእት የከፈልነው፣ ፍትሕ ጠፍቷል ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎች በማንሳታቸው ነው።
አሁን የድሮ ታጋዮቹ በግዝያቸው በፕሮግራሙ ባለመሳተፋቸው የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸው ለብቻቸው እንዲሳተፉ ይደረጋል። የገንዘብ ቅጣቱ እስከ ሦስት መቶ ብር ይደርሳል። ሦስት መቶ ብር ደግሞ መክፈል አይችሉም፤ ግድቡም መገደብ አይችሉም። ምክንያቱም ታጋዮቹ የሚተዳደሩት በጥሮታ ገንዘብ ነው። የጥሮታ ገንዘቡ ደግሞ ከሦስት መቶ ብር በላይ አይደለም። ታድያ ሦስት መቶ ብር (የጥሮታ) ለመንግስት ከፍለው በምን ሊተዳደሩ? ምን በልተው ሊገድቡ? በግድቡ ለመሳተፍም ይከብዳቸዋል። ምክንያቱም ግድብ የጉልበት ስራ ስለሆነ። አካላቸው አይፈቅድላቸውም፤ ምክንያቱም አካል ጉዳተኞች ናቸው።
በዚሁ ምክንያት በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ሩባፈለግ ጣብያ ከባድ ዉጥረት ነግሷል። በጣብያው (ንኡስ ወረዳ) እስካሁን ድረስ 963 ዜጎች በፕሮግራሙ ባለመሳተፋቸው ምክንያት ክስ ተመስርቶባቸዋል። ክስ ከተመሰረተባቸው ዜጎች ከ100-150 የሚደርሱ ሰዎች ተቀጥተዋል። ሌሎችም ቅጣታቸው እየተጠባበቁ ነው። የአከባቢው ህዝብ የካቲት 13, 2006 ዓም ይህ የመንግስት ካድሬዎች ተግባር በመቃወም “ሰሚ የለም ወይ?!” በማለት በጭኾት ተቃውሞውን አሰምቶ ነበረ።
የቀድሞ ታጋዮቹ ግን መንግስትን ክፉኛ እየወቀሱ ነው። አካላቸው በመጉደሉ ምክንያት ምንም ዓይነት የጉልበት ስራ መስራት የማይችሉ የመንግስት ተግባር ስለተቃወሙ ብቻ አሁን በፕሮግራሙ እንዲሳተፉ እየተገደዱ ካሉ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች መካከል ስማቸው እንዲጠቀስ ፍቃደኛ ከሆኑ (1) ሃምሳአለቃ ሃይለማርያም ገብረእግዚኣብሄር፣ (2) ሃምሳአለቃ አታኽልቲ ገብረኪሮስና (3) አስራአለቃ ወልዴብርሃ ገብረመድህን ይገኙባቸዋል። እነዚህ ሰዎች ደርግ ከወደቀ ከ1983 ዓም ጀምሮ በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት በምንም ዓይነት የመንግስት የጉልበት ስራ ተሳትፈው አያውቁም። አሁን መቃወም በመጀመራቸው ግን እየተገደዱ ይገኛሉ። አሁንም ቢሆን በጉልበት ሊገድቡ እንደማይችሉ የታወቀ ነው። የመንግስት ጥረት ግን ታጋዮቹ መንግስትን መቃወም እንደማያዋጣቸው ተገንዝበው ተቃውሞአቸውን እንዲያቆሙ ለማስገደድ ብቻ ነው። መንግስትን ከደገፉ ግን ነፃ ይሆናሉ። አይገደዱም። እንዲህ ነው የህወሓት ተቃውሞን የማፈን ስትራተጂ።
ቀደም ሲል የህወሓት ካድሬነታቸው በማቆማቸው ምክንያት መሳርያቸውን (ጠመንጃቸውን) በመንግስት አካላት ተነጥቀዋል። በአካላዊ ጉዳት ምክንያት ከህወሓት ዉትድርና ቢወጡም ጠመንጃቸው ግን ይዘውት ነበር የሚኖሩ። ጠመንጃቸው ይፈልጉታል። ምክንያቱም (አንድ) ራሳቸው የሚከላከሉበት ነው። ለብዙ ዓምታት ከነሱ ጋር የኖረ ስለሆነ ማንነታቸው አድርገውታል። እናም ጠመንጃቸውን ሲነጠቁ insecurity ይሰማቸዋል። ትልቅ የሞራል ውድቀት ይሰማቸዋል። የሞራል ኪሳራ ይደርስባቸዋል። ህወሓትም ይህን ያውቃል። እናም ነጠቃቸው። (ሁለት) ጠመንጃቸው በትንንሽ ከተሞች የሚገኙ ሃብታም የህወሓት ካድሬዎች የቤት ዘበኞች በመሆን ስራ የሚያገኙበት ነው። ጠመንጃ ከሌላቸው በዘበኝነት የመቀጠር ዕድል አያገኙም። ስለዚህ ስራ እንዳያገኙ ስለተፈለገ ነው። ስራ ካላገኙ በመንግስት ጥገኛ ይሆናሉ። ጥገኛ ከሆኑ ደግሞ መንግስትን ይደግፋሉ እንጂ አይቃወሙም። መንግስትን ካልተቃወሙ ደግሞ ህወሓት የፈለገውን ዓፈና የማድረስ መብት አገኘ ማለት ነው። ስለዚህ የዚህ ሁሉ ዓላማ ተቃውሞውን በማዳከም ህዝብን መጨቆን የሚቻልበት መንገድ ማመቻቸት ነው።
በብዙ የትግራይ አከባቢዎች የዉኃና አፈር ጥበቃ ፕሮግራም እየተሰራበት ያለ ሲሆን ባከባቢው ተገኝቶ በፕሮግራሙ ያልተሳተፈ ገበሬ መሬቱ እየተነጠቀ ይገኛል (እንደ ቅጣት መሆኑ ነው)። ነገሩ እንዲህ ነው። የህወሓት ካድሬዎች ማዳበርያ ለመሸጥ ሲባል ገበሬውን በአስገዳጅ እንዲገዛ ያደርጋሉ። ማዳበርያ ካልገዛ ይታሰራል፣ የመንግስት አገልግሎት አያገኝም፣ መሬቱም ይነጠቃል። ገብሬውም እነዚህ ሁሉ ቅጣቶች መሸከም ስለማይችል የማዳበርያ ዕዳ ይገባል። ማዳበርያውን ለመግዛት ገንዘብ ከተለያየ ተቋማት ይበደራል። ብድሩ ለመመለስ በከተሞች አከባቢ ወይ ሌላ ራቅ ያለ ቦታ በመሄድ ተጨማሪ ስራ ይፈልጋል። ዕዳውን ለመክፈል ስራ ፍለጋ ከቀዩ ይርቃል። ካድሬዎች ደግሞ “ባከባቢው እያለማ አይደለም” በሚል ምክንያት መሬቱ ተወስዶ ለሌላ ካድሬ ይሰጣል። ገበሬው ለዘላለሙ ከቀዩ ይፈናቀላል። ምክንያቱም መሬት የመንግስት ነው። መሬት የኔ ነው ብሎ ፍርድቤት ሂዶ መከራከር አይችልም። ሁሉም ነገር በሕግ ሳይሆን በመመርያ ነው የሚሰራው። እናም ህዝብ ችግር ላይ ወድቋል።
የታጋዮቹ ጉዳይ ግን አሳሳቢ ነው። ታጋዮቹ አካላቸው ጎድሏል። እኛን ከጨቋኞች ነፃ ለማስወጣት ሲሉ መስዋእት ከፈሉ። ለኛ ሲሉ አካላቸው ጎደለ። አሁን መስራት አይችሉም። መቃወምም እንዳይችሉ እየተደረጉ ነው። እነሱ የቤት ስራቸው ጨርሰዋል። ለኛ ሲሉ አካላቸው የጎደሉ ወገኖች አሁን እኛ ልንተባበራቸው ይገባል። እኛ ልንታገልላቸው ይገባል። እኛ ነፃ ልናወጣቸው ይገባል። ምክንያቱም እነሱ ዓቅሙ የላቸውም፤ እንደ ድሮ ሩጠው ጫካ መግባት አይችሉም። ከዚሁ ዓፋኝ ስርዓት እንገላግላቸው።
It is so!!!
በኢሕ አዴግ ውስጥ አለመተማመኑ በዝቷል፤ አንድነት በመዋቅሬ ውስጥ ገብቷል በሚል ግምገማ ሊጀምር ነው
ኢህአዴግ የአንድነት ፓርቲ ኃይሎች በአደረጃጀቴ ሰርገው ገብተተዋል በሚል ግምገማ ለጀምር መሆኑ ታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ጽ/ቤት የአንድ-ለ-አምስት የአደረጃጀት አመራሮች በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች የሚገኙ የአንድ-ለ-አምስት የአደረጃጀት አመራሮችን በመሰብሰብ “አንድነት ፓርቲ የአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀታችን ውስጥ አስርጎ ያስገባቸው ኃይሎች በጊዜ በግምገማ ካልተራገፉ ቀጣዩ ምርጫ ከቁጥጥር ውጪ እንደማይሆን ማንም እርግጠኛ መሆን አይችልም፡፡” ማለታቸውን በስብሰባው ላይ የተሳተፉ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ተናግረዋል፡፡
ምንጮቹ ጨምረው እንደተናገሩት ኢህአዴግ የአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀቱን የሚያስተባብሩ ከፍተኛ ካድሬዎችን አንድ-ለ-ሰላሳ ማደራጀት መጀመሩን ተከትሎ አንድነት ፓርቲ አስርጎ ያስገባቸው ኃይሎች አሉ በመባሉ ካድሬዎች እርስ በእርስ መሰላለል እና አለመተማመን ጀምረዋል፡፡ ይህ በካድሬዎቻቸው መካከል የተጠፈጠረው ትርምስ ያሰጋቸው የኢህአዴግ የአዲስ አበባ ጽ/ቤት አመራሮች ለክፍለ ከተማ አመራሮቻቸው አንድነት ሊይዝብን የሚችለው 30 በመቶ የሚሆነውን ህዝብ ነው የተቀረውን በኮንዶሚኒየም ፣ በአነስተኛ ጥቃቅንና በየአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀት ይዘነዋል ብለዋቸዋል፡፡ ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ መረጃ የሰጡት የስብሰባው ተሳታፊዎች 750ሺ የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢ፣ 30ሺ የኮንዶሚኒየም እጣ ተጠባባቂዎች ኢህአዴግን ነው የሚመርጡት በሚል ከመድረክ የቀረበው መደምደሚያ እንዳላሳመናቸውም ተናግረዋል፡፡
ጉዳዩን በሚመለከት ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ከአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የደረሰው ዶክሜንት እንደሚያስረዳው ፓርቲው የአዲስ አበባ አደረጃጀቱን ኢህአዴግ በዘረጋው ልክ 138 ያደረሰ ሲሆን በአሁኑ ጊዜም የወረዳ ደረጃና የሴል አደረጃጀቶቹን በኢህአዴግ የአደረጃጀት ቁጥር ልክ የማድረግ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ያመለክታል፡፡
በንፋስ ስልክ ላፍቶ የመንግስት ታጣቂው የባለ3 ልጆች ባለትዳሮችን በጥይት ደብድቦ ገደለ
ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው
በንፋስ ስልክ ላፍቶ የመንግስት ታጣቂው የ3 ልጆችን ባልና ሚስትን በጥይት ደብድቦ መግደሉ ተሰማ። ድርጊቱ የተፈፀመው ትላንት ከቀኑ 9.30 አካባቢ ነው ተብሏል።
አዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ውስጥ ልዩ ስሙ መካኒሳ አቦ ማዞሪያ በሚባል አካባቢ አንድ የመንግስት ታጣቂ የሶስት ልጆች ወላጆች የሆኑትን ባልና ሚስት በአውቶማቲክ መቺንገን በጥይት ደብድቦ ገድሏቸዋል።
የአካባቢው ሰዎች እና የሟች ዘመዶች በጋራ በመሆን የቀብሩን ስነ- ሥርዓት ለማስፈጸምና የመንግስት ታጣቂው የወሰደው እርምጃ ለማውገዝ እና በየጊዘው በአካባቢው የሚፈጸመውን የመንግስት ታጣቂዎች እርምጃ እና በህብረተሰቡ ላይ የደረሰውን ግፍ በጋራ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ለማጋለጥ በህብረት ድምጻቸውን ለማሰማት ሲሞክሩ በፈደራል ፖሊስ የተበተኑ ሲሆን በአካባቢው ላይ የአዲስ አበባ የፖሊስ ሃይሎች ተሰማርተዋል።
የፈደራል ፖሊስ አመራሮች የአከባቢውን ህዝብ የፖለቲካ አጀንዳ ያለው ሲሉት የፈረጁት ሲሆን ቀብሩ ሳይፈጸም ህዝቡን በማስፈራራት እና በዛቻ ያባረሩት ሲሆን የሟች ዘመዶች የኢትዮጵያ ህዝብ ይህን ጉዳችንን ሳይሰማና ሳያውቅልን አንቀብርም ብለው አስከረኖቹ ወደ መኖሪያ ቤት ተመስልሷል።
ለዘ-ሐበሻ ዘግየት ብሎ በደረሰን መረጃ ቀብሩ በነገው እለት ይፈጸማል።
“በዜጎች ላይ የመብት ጥሰት እየፈጸሙ ያሉ የመንግስት ተቋማት አና አስፈጻሚዎች በህግ ሊጠየቁ ይገባል”–አንድነት
ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
የአሜሪካ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያ ቤት እ.ኤ.አ በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተፈፀሙ ያላቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ሪፖርት ተመልክተነዋል፡፡ በሪፖርቱ የተካተቱት የመብት ጥሰቶች አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ በተደጋጋሚ ያጋለጣቸው እና ከፍተኛ ትግል እያደረግንባቸው የሚገኙ አስከፊ ተግባራት እንደሆኑ ቢታወቅም የቆምንለት ዓላማ እና እየታገልነው ያለው ስርዓት በሌሎች ዘንድም ድርጊቱ የታወቀ መሆኑን ያረጋገጥንበት ነው፡፡ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በሪፖርቱ ያካተታቸው እንደተጠበቁ፣ የተፈጸሙ እና እየተፈጸሙ ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ከዚያም የላቁ እንደሆኑ አንድነት በተጨባጭ ያውቃል፡፡
የኢህአዴግ መንግሥት ዜጎችን በማፈን፣ ሚዲያዎችን በመዝጋት፤ ለህግ የበላይነት ቁብ በማጣት፤ ድብቅ በሆኑ እስር ቤቶች ዜጎችን በማጎር፤ በጥርጣሬ ያዝኳቸው የሚላቸውን ዜጎች በራሳቸው ላይ እንዲመሰክሩ በማስገደድ፤ በማሰቃየት፤ በማስፈራራት፤ በመግደልና አስገድዶ ከሀገር በማሰደድ የተመሰከረለት ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከገዥው የኢህአዴግ መንግሥት የተለየ አመለካከት ያላቸውና ስርዓቱን የሚተቹ ዜጎች የመከራ ገፈት የሚጋቱባት ሀገር እንደሆነች መቀጠሏም ከዜጎቿም ሆነ ከዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ የተሰወረ አይደለም፡፡
ቀደም ሲል በግፍ ታስረው ከሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አንዷለም አራጌ እና ናትናኤል መኮንንን ከመሳሰሉ ብርቱ ሰላማዊ ታጋዬቻችን በኋላ እንኳን በቅርቡ የፓርቲያችን የቀድሞ ዋና ፀሐፊና የአሁኑ የብሔራዊ ም/ቤት አባል የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ ሃሳባቸውን በመጽሔት ጽፈዋል ተብለው ለእስር መዳረጋቸው የስርዓቱ አፋኝነት መቋጫ ያጣ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ሌላኛው አባላችን አቶ አለማየሁ ለፌቦ ከፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማግስት ጀምሮ ወደ ደቡብ ክልል ሲመለሱ የፓርቲ አባል በመሆናቸው ብቻ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ለ27 ቀናት መታሰራቸው፤ በኦሮሚያ በደቡብ እና በሰሜናዊት ኢትዮጵያ በተለየ ሁኔታ አባሎቻችን በአመለካከታቸው ብቻ ከስራ እየተፈናቀሉ መሆኑ፤ ጋዜጠኞች እና የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ዛሬም በእስር ላይ መሆናቸው፤ ከዚህ በተጨማሪ ሙስና፤ የመሬት ቅርምት፤ የዜጎች መፈናቀል እና ህገ ውጥ አሰራር በበኩሉ ከስርዓቱ ጋር የተገነባ መሆኑ ሀቅ ነው፡፡
በሪፖርቱ የተዘረዘሩትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መድገም ባያስፈልግም በዚህች ሀገር የተንሰራፋው ህገ ወጥነት ይቀየር ዘንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ የሲቪክ ተቋማት፤ ድፕሎማቲክ ማህበረሰቡ እና የሚመለከተቸው አካላት ህጋዊ በሆነ ሁኔታ በመንግሥት ላይ ጫና እንዲያሳድሩ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ ይህ ሁሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ባለበት ‹‹ጤነኛ እንደሆነ መንግሥት ›› ራሱን ለመቁጠር እንደሚያስቸግረው እንረዳለን፡፡ በመሆኑም የፖለቲካ ምህዳሩን ለሁሉም እኩል በማድረግ፤ የፀረ ሽብር፤ የፕሬስ፤ የበጎ አድራጎት እና ማህበራት ማደራጃ፤ ህጎችን በመቀየር፤ የሊዝ አዋጁን እና በተሻሻለው የወንጀለኛ መቅጫ የተካተተውን የፕሬስ ነጻነት የሚገፋ አንቀጽ በመሰረዝ፤ ከዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት ላይ እጁን በማንሳት ከሚመጣበት የህዝብ ቁጣም ሆነ የታሪክ ተወቃሽነት ቢያመልጥ መልካም ነው እንላለን፡፡ አንድነት፣ በሀገራችን ያሉትን የፖለቲክ ችግሮች በዉይይት ለመፍታት በኢሕአዴግ እና በተቃዋሚዎች መካከል ሁሉም አሸናፊ የሆኑበትና ቅንነት ያለበት ውይይት እንዲደረግ፣ ፍላጎት እንዳለው በተደጋጋሚ በገለጸው መሰረት፣ ኢሕአዴግ ወደ መሃል ሜዳ መጥቶ ለዉይይት እንዲዘጋጅም እንጠይቃለን።
በሪፖርቱ የተዘረዘሩ እና ሌሎችም የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በሚመለከት ግን በተለይ የተወካዮች ምክር ቤት፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮምሽንና የእንባ ጠባቂ ተቋማት ከፓርቲ ወገንተኝነት በፀዳ መልኩ መርምረውና አጣርተው የመብት ጥሰት የፈጸሙትን የመንግስት አካላት ለፍትህ ማቅረብ ግዴታቸው መሆኑን አንድነት ፓርቲ ያሳውቃል፡፡
ከሁሉም በላይ ዋነኛ የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሆናችሁ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ያላችሁ መላው የሀገራችን ዜጎች ሰፊው ህዝብ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት እንጂ ከጥቂት አምባገነን መሪዎች መብት የሚለምን አለመሆኑን በመገንዘብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ስርዓቱን ለመታገል በአንድ ድምጽ ከጎናችን እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
የአሜሪካ መንግሥትም ቢሆን አንዲህ ዓይነቱን ከአሜሪካ ባህልና እሴት ጋር የሚቃረኑ ዘግናኝ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተደጋጋሚ በየዓመቱ ሪፖርት ከማውጣት ባሻገር ትርጉም ያለው ጫና በማሳደር ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን ለዴሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብት መከበር ሊቆም ይገባል ብለን እናምናለን፡፡
ዘለዓለማዊ ክብር ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን!!!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
የካቲት 26 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት ከወጣ በኋላ በኢትዮጵያ የፀረ-ሽብር፣ የፕሬስና የሲቪል ማኅበረሰብ ሕጎቹ ማወዛገባቸውን ቀጥለዋል
“መፈክር በተሰማ ቁጥር መፈክሩን ተከትለን አንነጉድም” አቶ ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚኒሰትሩ ቃል አቀባይ
የ2013 የስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት መውጣትን ተከትሎ ባለፉት አምስት ዓመታት ሲያወዛግቡ የነበሩት የፀረ-ሽብር፣ የመገናኛ ብዙሃን እና የበጎ አድራጎትና ማኅበራት (የሲቪል ማኅበረሰብ) ሕጎች ማወዛገባቸውን ቀጥለዋል።
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መ/ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) በየዓመቱ በሚያወጣው ሪፖርት ላይ በሕጎቹ የሀገሪቱን ሕዝቦች ስብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ላይ ጫና እንደሚያደርጉ ሲጠቅስ መቆየቱ ይታወሳል። መንግስት በበኩሉ የፀረ-ሽብር ሕጉ በሀገሪቱ ላይ ያንዣበበውን የሽብር አደጋ ለመግታት አስፈላጊ መሆኑን፣ የፕሬስና ሕጉም ሀሳብን የመግለፅ ነፃነትን ለማስፋት እንዲሁም የሲቪል ማኅበረሰብ አዋጁም በሀገሪቱ የውስጥ ጉዳይ የውጪ ጣልቃ ገብነትን ለመግታትና ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራትን ለማበረታታት መሆኑን ሲገለፅ ቆይቷል።
ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሕጎች የሀገሪቱን ዴሞክራሲያዊ ሂደት እያሽመደመደና የፖለቲካ ዓላማ ያዘሉ፣ የገዢውን ፓርቲ የስልጣን ዘመን የሚያረዝሙ በማለት ሲቃወሙ ቆይተዋል።
ከሰሞኑንም ይሄው ጉዳይ እንደ አዲስ ተነስቶ እያወዛገበ ነው። በመንግስት በኩል ሕጎቹን የማሻሻል ሁኔታ በራሱ መንገድ የሚያየው መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል።
“በእኛ እምነት ሕጎቹን መቀየር የሚያስፈልግ ከሆነ በሂደት ከታለመላቸው ዓላማ አንፃር ያመጡት ስኬት ተመዝኖ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በራሱ መንገድ (Organic Process) መልሶ የሚያያቸው ይሆናል” ያሉት አቶ ጌታቸው ከዚህ ውጪ ሕጎቹን በደፈናው ከመቃወም በስተቀር በዝርዝር የመጣ ጉዳይ የለም ብለዋል። ከዚህ ይልቅ ሕጎቹን ለማስቀየር መፈክር ማሰማቱ እንደማይጠቅም ገልፀዋል።
አቶ ጌታቸው “መፈክር በተሰማ ቁጥር መፈክሩን ተከትለን የምንነጉድበት ምክንያት የለም” ብለዋል።
በአንድነት ለዴሞክራሲ ለፍትህ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው በበኩላቸው ፓርቲያቸው ገዢው ፓርቲ በሕጎቹ ላይ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመነጋገር ፈቃደኛ ከሆኑ በደስታ እንደሚቀበሉት ተናግረዋል።ምንም እንኳ ፓርቲያቸው ለስርዓት ለውጥ የሚታገል ቢሆንም፤ ኢህአዴግን ጨምሮ በውጪ ሀገር በሚገኙ በሕግ ካልተከለከሉ በስተቀር ከማንኛውም የዴሞክራሲ ኃይል ጋር ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ገንቢ ውይይት ማድረግ እንፈልጋለን። ኢህአዴግም በማንኛውም የሕግና የፖሊሲ የሀሳብ የበላይነት ለማግኘት ፍረጃውን በመተው፣ ፓርቲዎችን በማናናቅና ሕዝባዊ መሠረታቸውን ሳይክድ እስከመጣ ድረስ በሕጎቹ ላይ ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለመነጋገር እንዲያመችም ሕጎቹን በጅምላ ከመቃወም ባለፈ በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ለመነጋገርም እንደሚፈልጉ ገልፀዋል። ሕጎቹን በጅምላ የሚቃወሙትም አዋጆቹ የወጡበትን መሰረታዊ ፍላጎት (Intention) ዴሞክራሲንና ሕገ-መንግስቱን የሚጥሱ በመሆኑ ነው ብለዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ሊዘጋ ነው፤ ዘንድሮ አንድም ተማሪ አልተመዘገበም
ዘሪሁን ሙሉጌታ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበው፦
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎችን በማጣቱ የትምህርት ክፍሉ አደጋ ላይ መውደቁን እያሳዘናቸው መሆኑን የታሪክ መምህራንና ተመራማሪዎች ገለፁ። ሀገሪቱ ጥንታዊና መካከለኛ ታሪኮች ባለቤት ብትሆንም በአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚገኘው የታሪክ የትምህርት ክፍል ሊዘጋ መቃረቡ እያነጋገረ ነው።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል የሚያስተምሩ መምህራንና የታሪክ ተመራማሪዎች “ታሪክ ዳቦ አይሆንም” በሚል የተሳሳተ አመለካከትና የ70/30 የትምህርት ፖሊሲ የፈጠረው ችግር መሆኑን በመግለፅ አሰራሩን አምርረው ተችተዋል። ከታሪክ በላይ ዳቦ የሚሆን የለም። ታሪክ የአንድ ሀገር የማንነትና የእውቀት መሠረት መሆኑ እየታወቀ የትምህርት ክፍሉ በተማሪ እጦት በአደጋ ላይ መገኘቱ እንደሚያስቆጣቸው መምህራኑና የታሪክ ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል።
ሰሞኑን ዩኒቨርሲቲው የታሪክ ትምህርት የተከፈተበትን 50ኛ ዓመት ባከበረበት ወቅት በ2006 ዓ.ም አንድም የታሪክ ተማሪ ያልተመዘገበበት መሆኑ አሳፋሪም አሸማቃቂም መሆኑን የጠቀሱት ባለሙያዎቹ ችግሩን ለማስተካከል ትኩረት እንዲሰጠው ጠይቀዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ፕሬዝዳንት ዶ/ር በለጠ ብዙነህ ስለጉዳዩ ተጠይቀው የታሪክ ትምህርት ክፍሉ እየተዳከመ መምጣቱን አምነዋል። ለዚህም በዋናነት የሚጠቀሰው ምክንያት በታሪክ ትምህርት የሚመረቁ ተማሪዎች በመስኩ ስራ አናገኝም በሚል አመለካከት ዲፓርትመንቱን ባለመምረጣቸው ነው ብለዋል። ከዚህ ባለፈ በታሪክ ትምህርት የተመረቁ ተማሪዎች የታሪክ መምህር የመሆን ፍላጎት ባለማሳደራቸው ወደ ሌሎች ትምህርቶች እያተኮሩ በመሆኑ ነው ብለዋል።
ዩኒቨርስቲው በ70/30 ፕሮግራም መሰረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጠቅላላው በማኅበራዊ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ በ2006 የትምህርት ዘመን ወደ 600 ብቻ ተማሪ መመዝገቡን ያስታወሱት ዶ/ር በለጠ እነዚሁ 600 ገደማ ተማሪዎች በሶሻል ሳይንስ ለ20 ዲፓርትመንቶች መከፋፈላቸውን ነው ያስረዱት። ከዚህም ውስጥ ተማሪዎቹ የተሻለ የሥራ ዕድል ወደሚያስገኝላቸው የትምህርት አይነት ነው የሚያተኩሩት ብለዋል።
የታሪክ ትምህርት መዳከም እንደ ሀገር ስለሚያመጣው ተፅዕኖ የተጠየቁት ዶ/ር በለጠ፤ ተፅዕኖ መፍጠሩ አይቀሬ መሆኑን ይስማሙበታል። ነገር ግን በመላው ሀገሪቱ በቅርቡ በተከፈቱ 32 ገደማ ከሚሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ወደ 17 ዩኒቨርሲቲዎች የታሪክ ትምህርት ስላላቸው በዘርፉ የሚመረቁ ተማሪዎችን ቁጥር በአንፃራዊነት ሊደግፈው እንደሚችል ተናግረዋል። ነገር ግን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያለው ሁኔታ ግን የታሪክ ትምህርት የሚማሩ ተማሪዎች ቁጥር ማነስ ግን አስጊ መሆኑ ተናግረዋል። ሁኔታውም በዚሁ ከቀጠለ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ የታሪክ መምህራን ላናገኝ የምንችልበት አደጋም ይታየኛል ብለዋል። በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የታሪክ ትምህረት እንደ አንድ የትምህርት አይነት እየተሰጠ በመሆኑ በዩኒቨርሲቲዎች ያለው የታሪክ ተማሪዎች እጥረት መታየቱ ወደፊት የታሪክ መምህራን ላናገኝ እንችላለን ሲሉም ዶ/ር በለጠ ስጋታቸውን ገልፀዋል።
ከአመለካከት ጋር በተያያዘ “ታሪክ ዳቦ አይሆንም” የሚለው አተያይ ችግር መፍጠሩን የጠቀሱት ዶ/ር በለጠ የታሪክ ትምህርት ከገበያና ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጋር ብቻ የተያያዘ በመሆኑ ይሄንን አመለካከት ለመለወጥ ብዙ መስራት እንዳለብን እንረዳለን ብለዋል። በቀጣይም የክፍለ ትምህርቱን ህልውና ለማስቀጠል የmajor/miner ፓኬጅ ማጠናቀር እንደሚገባ ጠቅሰዋል። ለምሳሌ ታሪክን በዋናነት ተምሮ ጋዜጠኝነት ወይም ቋንቋን በሁለተኛ ደረጃ እንዲማር በማድረግ የስራ አማራጭን ለመፍጠር መሞከር አለበት ብለዋል። አሁን ባለው የካሪኩለም ሁኔታ የmajor/miner ፓኬጅ አለመኖሩ ለተማሪዎቻችን አማራጭ እንድንሰጣቸው አላደረገም ብለዋል።
የሀገሪቱ ታሪክ በአግባቡ ባልተጠናበትና ባልተተነተነበት ሁኔታ የታሪክ ትምህርቱ መዳከሙ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው። ገዢው ፓርቲ ከሚመራበት ልማታዊ አቅጣጫም ጋር በማያያዝ የታሪክ ትምህርት መዳከሙን የሚተቹም አካላት አሉ።
በዳላስ የምትነዳው መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ ሕይወቷ ያለፈው ኢትዮጵያዊት ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈጸማል
(ዘ-ሐበሻ) በዳላስ ቴክሳስ ባለፈው ቅዳሜ ማርች 1 ቀን 2013 ዓ.ም የምትነዳው መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ ሕይወቷ ያለፈው ወጣቷ ኢትዮጵያዊት ሜላት ማሞ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ረፋዱ ላይ እንደሚፈጸም ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች አመልክተዋል።
ከባቡር ጋር ተጋጭታ ሕይወቷ የማለፉ ዜና በዘ-ሐበሻ ከተዘገበ በኋላ በዓለም የተለያዩ ክፍሎች ተሰራጭተው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሃዘናቸውን በስፋት ሲገልጹ የሰነበተ ሲሆን በዳላስም ኢትዮጵያውያኑ በከፍተኛ ሃዘን ላይ እንደሚገኙ የደረሱን መረጃዎች አመልክተዋል። በጣም ተግባቢና ሃገር ወዳድ እንደነበረች የሚነገርላት ወጣቷ ሜላት ሕይወቷ በአሰቃቂ ሁኔታ ማለፉ ከተሰማ በኋላ ባለፈው እሁድ በዳላስ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ ም ዕመናን በለቅሶና በጸሎት አስበዋት ውለዋል።
የወጣት ሜላት ማሞ የቀብር ስነሥርዓት ዛሬ የሚፈጸም ሲሆን ከጠዋቱ በ10 ሰዓት በዳላስ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ ፍትሃት ስነስርዓት ከተካሄደ በኋላ ረፋዱ ላይ ከጠዋቱ 11 ሰዓት በሬስትላንድ የመቃብር ሥፍራ የቀብር ስነስርዓት ይደረጋል። ምናልባት በዳላስ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን በቀብሩ ላይ መገኘት ከፈለጋችሁ አድራሻው፡ Restland Cemetary – 13005 Greenville Ave, Dallas, TX 75243 መሆኑን ዘ-ሐበሻ ከሥፍራው ያገኘችው መረጃ ያመለክታል።
ዘ-ሐበሻ የሜላት አደጋ እንደተሰማ የዘገበችውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ቀብሩ የሚደረግበት ቦታ ካርታው የሚከተለው ነው፦
የአፍሪካ መሪዎች ለምን ቶሎ ይሞታሉ? –በ6 ዓመት ውስጥ 10 የአፍሪካ መሪዎች ሞተዋል
ቢቢሲ እንደጻፈው – አድማስ ሬዲዮ እንዳቀናበረው።
አንድ የአገር መሪ ፣ ገና በሥልጣን ላይ እያለ መሞቱ የተለመደ አይደለም። ነገር ግን ካለፈው 2008 ዓ.ም ወዲህ በዓለም ላይ 13 የአገር መሪዎች ገና ቢሯቸው እያሉ ሲሞቱ፣ ከዚያ ውስጥ 10 ያህሉ የአፍሪካ መሪዎች ናቸው። አፍሪካ ውስጥ መሪዎች ለምን ሥልጣን ላይ እያሉ ይሞታሉ?
በ 2012 ዓ.ም ብቻ አራት የአፍሪካ መሪዎች ቢሯቸው ውስጥ እያሉ ህይወታቸው አልፏል (የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የጋናው ፕሬዚዳንት፣ የማላዊ ፕሬዚዳንት፣ የጊኒ ቢሳዎ ፕሬዚዳንት) ። የመሪዎቹ ሞት ለጋዜጠኞች ደግሞ አዲስ የምርምር መንገድ ከፍቷል፣ – የአፍሪካ መሪዎች ለምን ቢሯቸው እንዳሉ ይሞታሉ?
“ሌሊት ስልክ ከተደወለልኝ፣ በቃ አንድ የአፍሪካ መሪ ሞቷል ማለት ነው ብዬ ማሰብ ጀምሬያለሁ” የሚለው የደቡብ አፍሪካው ዴይሊ ማቭሪክ ዜና አውታር ጋዜጠኛ ሲሞን ኤሊሰን ነው። እናም ይህን ጥያቄ ይዞ የትኛው መሪ በስንት ዓመቱ፣ በምን ምክንያት ሞተ? የሚለውን ምርምር ማድረጉን ቀጠለ።
ከ 2008 ወዲህ ብቻ 10 የአፍሪካ መሪዎች ሥልጣን ላይ እንዳሉ ህይወታቸው አልፏል። እነሱም ….
1- የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ፣ ዕድሜ 57 የሞት ምክንያት ድንገተኛ ኢንፌክሽን፣ የሞቱበት ወር ኦገስት 2012
2- የጋናው ፕሬዚዳንት ጆን አታ ሚልስ ፣ ዕድሜ 68፣ የሞት ምክንያት የጉሮሮ ካንሰር፣ የሞቱበት ወር ጁላይ 2012
3- የማላዊው ፕሬዚዳንት ቢንጉ ዋ ሙታሪካ ፣ ዕድሜ 78፣ የሞት ምክንያት ካርዲያክ አሬስት፣ የሞቱበት ወር ኤፕሪል 2012
4- የጊኒ ቢሳዎ ፕሬዚዳንት ኤም ቢ ሳኒሃ ፣ ዕድሜ 64፣ የሞት ምክንያት የቆየ በሽታ፣ ለረዥም ጊዜ ታመው ቆይተው። የሞቱበት ወር ጃንዋሪ 2012
5- የሊቢያው ፕሬዚዳንት ሙ አመር ጋዳፊ ፣ ዕድሜ 69፣ የሞት ምክንያት በአማጺዎች ተገድለው፣ የሞቱበር ወር ኦክቶበር 2011
6- የናይጄሪያው ፕሬዚዳትን ኦማሩ ያር አዱአ፣ ዕድሜ 58፣ የሞት ምክንያት የኩላሊትና የልብ ህመም፣ የሞቱበት ወር ሜይ 2010
7- የጋቦን ፕሬዚዳንት ኦማር ቦንጎ፣ ዕድሜ 73፣ የሞት ምክንያት የልብ ድካም፣ የሞቱበት ወር ጁን 2009
8- የጊኒ ቢሳዎ ፕሬዚዳንት ጄ ቢ ቪየራ፣ ዕድሜ 69፣ የሞቱበት ምክንያት ተገድለው፣ የሞተበር ወር ማርች 2009
9- የጊኒ ፕሬዚዳንት ላንሳና ኮንቴ፣ ዕድሜ 74፣ የሞቱበት ምክንያት እስካሁን አልተነገረም፣ የሞቱበር ወር 2008፣
10- የዛምቢያ ፕሬዚዳንት ሌቪ ማዋናዋሳ፣ ዕድሜ 59፣ የሞቱበት ምክንያት ስትሮክ፣ የሞቱበት ወር 2008
እንግዲህ ከየትኛውም የዓለማችን አህጉር በአፍሪካ ተቀማጭ ፕሬዚዳንቶች በብዛት ህይወታቸው አልፏል። ከአፍሪካ ውጭ፣ በተመሳሳይ ወቅት ህይወታቸው ያለፈው የዓለም መሪዎች ሶስት ብቻ ሲሆኑ እነሱም የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ ታመው፣ የፖላንድ ፕሬዚዳንት ላች ካሲንኪ በአውሮፕላን አደጋ እና የባርባዶስ ፕሬዚዳንት ዴቪድ ቶምሰን በካንሰር በሽታ ናቸው።
ከዝርዝሩ እንደሚታየው አፍሪካውያን መሪዎች ከሌሎቹ የዓለማችን አገሮች ይልቅ ዕድሜያቸው የገፋ ነው። ምናልባት አፍሪካውያን መሪዎቻቸው ሸምገል ያሉ እንዲሆኑ ይፈልጉ ይሆን? ሲል ይኸው ጋዜተኛ ሲሞን ኤሊሰን ይጠይቃል።
በዓለም ላይ ያሉ መሪዎችን ዕድሜ በአማካይ አውጥተን ስንመለከት፣ አፍሪካውያን ሸምገል ያሉ ሆነው ይገኛሉ። የዓለም መሪዎች በአህጉር ተከፋፍለው አማካይ ዕድሜያቸው ሲሰላ አፍሪካውያን መሪዎች በአማካይ ዕድሜያቸው 61፣ ኤዥያውያን 61፣ አውሮፓ 55፣ ሰሜን አሜሪካ 59፣ ደቡብ አሜሪካ 59፣ እንዲሁም አውስትራሊያ 58 ሆነው ተገኝተዋል።
በሌላ በኩል በአፍሪካ ለረዥም ጊዜ በህይወት የመቆየት መጠን (ላይፍ ኤክስፔታንሲ) አነስተኛ መሆኑ ይታወቃል። ይህም ከአህጉሪቱ የድህነት እና የበሽታ ታሪክ ጋር ይያያዛል። መሪዎች ሥልጣን ከያዙ በኋላ የተመቻቸ ኑሮ ቢኖራቸውም፣ ያደጉበት ህይወት በችግርና በሽታ የተጠቃ የድህነት ኑሮ ከሆነ እስከመጨረሻው ለረዥም ጊዜ የመቆየት ዕድላቸው ላይ ለውጥ እንደሚኖረው በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የዘር ጉዳይ ጥናት ሃላፊ ዶክተር ጆርጅ ሌሰን ይናገራሉ። ስለዚህም አፍሪካውያን መሪዎች በጊዜ ህይወታቸው ቢያልፍ፣ ከአህጉሪቱ ችግር ጋር የተያያዘ ምክንያት ሊኖረው ይችላል ማለት ነው።
በ2009 ዓ.ም በተደረገው ጥናት የአፍሪካውያን አማካይ በህይወት የመኖርያ ዕድሜ 75 ሲሆን፣ የየአሜሪካውያን 82፣ የአውሮፓውያን 81፣ የፓስፊክ አገሮች 80፣ የ ኤዥያውያን 77 ነው። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች በጊዜ ሞት ቢያጠቃቸው ላይገርም ይችላል።
እንግዲህ የአፍሪካ መሪዎች በሥልጣን ላይ እያሉ የመሞታቸው ነገር አዲስ ባይሆንም፣ ብዙዎቹ በህይወት እያሉ ያስተካከሉት ነገር ከሌለ ድንገት ሲሞቱ ሥልጣኑን ለመያዝ የሚደረግ ሽኩቻ በህዝቡና በአገሪቱ ላይ ችግር ይፈጥራል .. ሲሉ ተንታኞቹ ይናገራሉ።
የጋዜጠኛ ብርቱካን ሃረገወይን ባለቤት የሆኑት ከፍተኛው የመንግስት ፕሮቶኮል ሹም ከስልጣናቸው ተነሱ
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት ከፍተኛ የፕሮቶኮል ዋና ሹም ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ በላይ ግርማይ ከስልጣን መነሳታቸውን የቅርብ ምንጮች ገለፁ። የሕወሐት አባል የሆኑትና ከ1990ዓ.ም ጀምሮ የጠ/ሚ/ሩ እንዲሁም የፕሬዝዳንቱ ፕሮቶኮል ሹም ሆነው በአቶ መለስ ዜናዊ ተሾመው ሲያገልግሉ መቆየታቸውን ያስታወቁት ምንጮች የአቶ በላይ ቢሮ በውጭ ጉዳይ ሚ/ር ውስጥ እንደነበረ ጠቁመዋል።
የቀድሞ ፕ/ት ነጋሶ ጊዳዳ፣ የጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ እንዲሁም የፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የፕሮቶኮል ሹም ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን ያስታወሱት ምንጮቹ፣ የውጭ አገር ባለስልጣናት፣ አምባሳደራትና ሌሎች አካላት ወደ ጠ/ሚ/ሩም ሆነ ፕሬዝዳንቱ ከመግባታቸው በፊት ጉዳያቸው በአቶ በላይ ግርማይ በኩል ያልፍ እንደነበር አያይዘው ገልፀዋል። ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ሕይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ለ14 አመት በከፍተኛ ፕሮቶኮል ሹምነት ሲያገለግሉ ዘ-ሐበሻ የቆዩት አቶ በላይ ለአቶ መለስ ከነበራቸው ታማኝነትና ቀረቤታ አንፃር ከጠ/ሚ/ሩ ሞት በኋላ በነበራቸው ስልጣን ብዙም ደስተኛ እንዳልነበሩ የጠቆሙት ምንጮች አክለውም በሕወሐት ውስጥ ተፈጥሮ ከቆየው የቡድን ልዩነት ጋር በተያያዘ አቶ በላይ ግርማይ ከሃላፊነት እንዲነሱ በነደብረፂዮን መወሰኑን አስታውቀዋል።
በሌላም በኩል ለአቶ በላይ ግርማይ ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንደሚሉት በገዛ ፈቃዳቸው እንደለቀቁ ይጠቁማሉ። የአቶ መለስና የወ/ሮ አዜብ ታማኝ ከሚባሉት የአገር ውስጥ ደህንነት ዋና ሃላፊ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል ከስልጣን ተነስተው በሙስና እስር ቤት መወርወራቸውን፣ እንዲሁም የቤተመንግስት የደህንነትና ጥበቃ ዋና ሃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈሪ ቀጥሎ ከስልጣን የተነሱ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን አቶ በላይ ግርማይ እንደሆኑ ምንጮቹ ገልፀዋል።
አቶ በላይ ግርማይ የጋዜጠኛ ብርቱካን ሃረገወይን ባለቤት ሲሆኑ፣ ጋዜጠኛ ብርቱካን በኢትዮጲያ ራዲዮና ቴሌቪዥን በሃላፊነት ተመድባ የምትሰራና አቶ መለስ ዜናዊን ብዙ ጊዜ ለብቻዋ ቃለምልልስ ታደርግ እንደነበረ፣ እንዲሁም ከጠ/ሚ/ሩ ጋር ወደ ተለያዩ አገራት አብራ ትጓዝ እንደነበረ ምንጮቹ አመልክተዋል።
የምትነዳው መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ ሕይወቷ ያለፈው ኢትዮጵያዊት ወጣት ቀብር በዳላስ ተፈጸመ (የቀብር ፎቶዎች ይዘናል)
(ዘ-ሐበሻ) ባለፈው ቅዳሜ ሕይወቷ በአሰቃቂ ሁኔታ ያለፈው ኢትዮጵያዊቷ ሜላት ማሞ ዛሬ በዳላስ ከተማ የቀብር ሥነ-ሥርዓቷ ተፈጸመ። በወጣቷ ቀብር ላይ ከ500 ሰው በላይ መገኘቱንም የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከስፍራው አስታውቀዋል።
ዘ-ሐበሻ በሁለት ዜናዎች እንደገለጸችው ከባቡር ጋር የምትነዳው መኪና ተጋጭቶ ሕይወቷ ያለፈው ሜላት ማሞ በዳላስ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ፍትሃት ከተደረገላት በኋላ በበሪ’ስላንድ የመቃብር ቦታ (Restland Cemetary) አስከሬኗ አርፏል።
በስፍራው የነበረው ሕዝብ በከፍተኛ ሃዘን ተውጦ ሃዘኑን ሲገልጽ እንደነበር የገለጹት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች በተለይም በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ጥቃትና ግድያ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመውጣት ለወገኖቿ ያላትን ፍቅር መግለጿን በማስታወስ ሃዘናቸውን በጥልቀት ሲገልጹ እንደነበር ጠቅሰዋል።
ወጣቷ ሜላት ማሞ የ4 ዓመት ወንድ ልጅ እናት እንደሆነችም ተያይዞ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ዛሬ የቀብር ስነስርዓቷ ሲፈጸም የሚያሳየውን ፎቶዎች ከዳላስ የዘ-ሐበሻ ተባባሪዎች ልከውልናል – እነሆ።
ስለሜላት ከዚህ ቀደም የዘገብናቸውን 2 ዘገባዎች ተጨማሪ መረጃዎች ይሰጧችኋል፤ ሊንኮቹን እነሆ
1ኛ. በዳላስ የምትነዳው መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ ሕይወቷ ያለፈው ኢትዮጵያዊት ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈጸማል
2ኛ. በዳላስ የምትነዳው መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ ሕይወቷ ያለፈው ወጣት ኢትዮጵያዊት ናት ተባለ
(ሰበር ዜና) መርዝ ተሰጥቷቸዋል የተባሉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ አረፉ
(ዘ-ሐበሻ) መርዝ ተሰጥቷቸው ነው ለዚህ የበቁት የተባሉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
ለህክምና ብዙ ገንዘብ ወጣባቸው በሚል ሕገወጥ በሆነ መንገድ ከስልጣናቸው እርሳቸው ባላወቁበት በፈቃዳቸው እንደለቀቁ ተደርጎ የተነገረባቸው የኦሮሚያው ክልል ፕረዚዳንት ኦቦ አለማየሁ አቶምሳ በተሰጣቸው የተመረዘ ምግብ ምክንያት የጀመራቸው በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ ጸንቶ በተደጋጋሚ በተለያዩ ሃገራት ህክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ዛሬ ግን በባንኮክ ታይላድ ለህክምና በሄዱበት ሆስፒታል ሕይወታቸው አልፏል።
በ45 ዓመታቸው በታይላንድ ባንኮክ ሕይወታቸው ያለፈው ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ በምን ምክንያት የተመረዘ ምግብ እንደተሰጣቸው ባይታወቅም ከርሳቸው ጋር ምግቡን በልቶ የነበረ ግለሰብም እስካሁን በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኝ ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ለዘ-ሐበሻ ቅርብ የሆኑ የኦነግ የመረጃ ምንጮች “ኦህዴድን የድሮው ኦህዴድ እንዳይሆን ሊያደርጉ የሚችሉ ሰው ስላልነበሩ በሕወሓቶች መርዝ እንዲሰጣቸው ተደርጓል” የሚል አመለካከት ያላቸው መሆኑን ገልጸው ሕወሓት አቶ ዓለማየሁን ቀጠፋቸው ሲሉ ይተቻሉ”፡
ከየካቲት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በባንኮክ ህክምና ላይ የከረሙት በምስራቅ ወለጋ ቢሎ ቦሼ ወረዳ ከአባታቸው አቶ አቶምሳ ሚጃ እና ከእናታቸው ወይዘሮ አየለች ብሩ በ1961 ዓ.ም ተወለዱት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ ሕይወታቸው በእንዲህ ያለ ሴራ ማረፉ በኢሕአዴጎች መካከል አለመተማመንን ሊፈጥር እንደሚችል የተለያዩ የፖለቲካ ታዛቢዎች እየገለጹ ነው።
የኦህዴድ/ኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አቶ ዓለማየሁን “ላለፉት 24 ዓመታት የኦሮሞ ህዝብ እና መላው የአገሪቱ ህዝቦች ዛሬ ለደረሱበት የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ተጠቃሚነት እንዲበቁ በቁርጠኝነት የታገሉ ነባር ታጋይ ነበሩ” ካለ በኋላ በ1981 ዓመተ ምህረት የደርግን ስርዓት ለመገርሰስ ሲካሄድ የነበረውን የትጥቅ ትግል መቀላቀላቸውን፣ ከ1988 እስከ 1994 ድረስም የኦህዴድ ማዕከላዊ ፅህፈት ቤት እና የድርጅቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ማገልገላቸውን፣ ከ2002 ዓመተ ምህረት ጀምሮ የኦህዴድ ሊቀመንበር ሆነ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር መሆናቸውን ጠቅሷል። ሆኖም ግን ድርጅቱ እንደተጠበቀው አቶ አለማየሁ በተመረዘ ምግብ መሞታቸውን ከሴራው በስተጀርባ ማን እንዳለ ያስቀመጠው ነገር አለመኖሩን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ለዘ-ሐበሻ በደረሱ መረጃዎች ቀጣዩ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አስቴር ማሞ ይሆናሉ የሚለው ግምት ሚዛን እየደፋ ነው።
በመንግስት ታጣቂው በጥይት ተደብድበው የተገደሉት ባልና ሚስት ፎቶ ተገኘ
እብሪተኛ የመንግስት ታጣቂዎች ለሚቀጥፉት የሰው ህይወት መንግስት ተጠያቂ የሚሆነው መቼ ነው?
ከዳዊት ሰለሞን
የመንግስት ታጣቂዎች በተለያዩ አጋጣሚዎች ደማቸው በትንሽ በትልቁ እየፈላ ሲቪል ዜጎችን የሚጨርሱበት አጋጣሚ ከቀን ቀን እየጨመረ ነው፡፡
የባህር ዳሩን ዘግናኝ እልቂት ለጥቆ ቂርቆስ ቤ/ክ አካባቢ ሁለት ሰዎችን በጥይት በመምታት የወሲብ ደምበኛው እንደነበረች የተነገረላትን ሴት ሲገድል አብሯት የነበረውን ማቁሰሉ አይዘነጋም፡፡የታክሲ ሹፌሩ አልጭንህም ስላለው የታጠቀውን ሽጉጥ በመምዘዝ ለፍቶ አዳሪውን በአጭር አስቀርቶታል፣አራት ኪሎ ቤተ መንግስት አቅራቢያ በሚሄድ መኪና የተርከፈከፈ ጥይት ስንቱን እንዳስቀረ እግዜር ይወቀው ፡፡በየአካባቢው እንዲህ አይነት ዘግናኝ ዜናዎችን መስማት አዲስ አይደለም፡፡
ከትናንት በስቲያ በላፍቶ ክፍለ ከተማ አቦ ማዞሪያ አካባቢ በምስሉ የምትመለከቷቸውን የሶስት ልጆች ወላጆች እብሪተኛው ታጣቂ በጥይት በመደብደብ ገድሏቸዋል፡፡ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡እሰየው ነው ፡፡ግን በቃ?እነዚያን ሶስት ህጻናት ማን ነው የሚያሳድጋቸው?ግለሰቡን አምኖ ክላሽ ያስታጠቀው አካል የማይጠየቀውስ እስከመቼ ነው?
መንግስት የመኪና አሽከርካሪዎች የሶስተኛ ወገን ኢንሹራንስ እንዲገቡ እያስገደደ መሆኑ በመኪኖቹ አደጋ ለሚደርስበት ሰው አንዳች ነገር ነውና ይበረታታል፡፡መንግስት በነካ እጁ የሚያስታጥቃቸው ሰዎች ለሚያደርሱት የመብት ጥሰት ኢንሹራንስ ይግባ!!!በእኔ እምነት ስለ ተገደሉት ወላጆችና ወላጅ አልባ ስለሆኑት ልጆች መጮህ የሁላችንም ግዴታ ነው።
“ኢመማና የካቲት፣ የማህበሩ ውጣውረድ በጨረፍታ”–በስደት የሚገኙ መምህራን አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ
ዘመን በመቁጠር ሂደት የወርና የሁኔታ ግጥምጥሞሽ ይከሰታል። በሰነድ የተያዘ ማስረጃ እንደሚያሳየው የካቲት 14 ቀን 1941ዓ.ም “የመምህራን ኅብረት” በደግማዊ ምኒልክ ት/ቤት በአዲስ አበባ ተቋቋመ። የወቅቱ የኅብረቱ ሊቀመንበርም አቶ ሚሊዮን ነቅነቅ ነበሩ። ይህ የመምህራን ኅብረት ስያሜውን እንደያዛ እስከ 1954 ዓ.ም ድረስ ቀጥሏል። ኅብረቱ ከየትኛውም አካል መንግሥትን ጨምሮ አደናቃፊ ኃይል ሳይገጥመው እንዲያውም ድጋፍ እየተደረገለት ነበር እዚህ ወቅት ድረስ የቀየው። ምዝገባ ፣ በሕግ የመታወቅና ያለመታወቅ ጥያቄም አልተነሳም ነበር። ኅብረቱ በ1953 ዓ.ም የዕውቅናና የምዝገባ ጥያቄ ተነስቶ በዚያውም አፈናና የመንግሥት ጣልቃገብነት ተጨምሮበት ጉዞው አስቸጋሪ ሆነ።