Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all 2784 articles
Browse latest View live

“በሐረር ከተማ በደረሰው ቃጠሉ ከዛም የክልሉ ፖሊስ በንጹሃን ዜጎች ላይ ጉዳት ማድረሱን በቸልታ አንመለከተውም”–አንድነት

$
0
0

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

Harar City
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

በሐረር ክልል ሕዝብ ላይ የደረሰውን ከፍተኛ ጉዳት አንድነት በቸልታ አይመለከተውም

የካቲት 30 ቀን 20006 ዓ.ም በታሪካዊቷ የሐረር ከተማ በጀጎል ሸዋበር በደረሰው ቃጠሎ እና ከዚያም በኋላ የክልሉ ፖሊስ በወሰደው እርምጃ በዜጎች ላይ ጉዳት መድረሱ የፓርቲያችንን አመራሮች፣ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጪ ያሉ አባላትና ደጋፊዎችን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡

ምንም እንኳን የቃጠሎው መንስኤ ተጣርቶ ይፋ ያልተደረገ ቢሆንም በጀጎል ሸዋ በር እየደረሰ ያለው ተደጋጋሚ ቃጠሎ ድንገቴ ነው ለማለት የሚያስደፍር አይደለም፡፡ በተለይም በየካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም የተነሳውን ቃጠሎ በተገቢ ፍጥነት ለመቆጣጠር የክልሉ መንግስት ፍላጎት ያልታየበት መሆኑ፤ ይልቁንም ግሬደር መኪና አስጠግቶ ቦታውን ለማፅዳት መሞከሩ አጠያያቂ ነው፡፡ የክልሉ መንግስት ቃጠሎውን ለመቆጣጠር ተገቢውን ሁሉ ባለማድረጉ የጉዳቱ ሰለባ የሆነው ህዝብ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖበት ክፉኛ እንደ ተማረረ በዚሁ ምክንያትም ቁጣ ተቀስቅሶ ፖሊስ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ጉዳት ማድረሱንም በክልሉ የሚገኙ የፓርቲያችን አመራሮች መረጃውን አድርሰውናል፡፡

በመሆኑም ፓርቲያችን የክልሉ መንግስት ትክክለኛው የቃጠሎ መንስኤ በአስቸኳይ ተጣርቶ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ፤ በማንኛውም ምክንያት ኃላፊነታቸውን በብቃት ያልተወጡ የመንግስት ኃላፊዎች በግልፅ ለተጠያቂነት እንዲቀርቡ፤ የክልሉ ፖሊስ በህዝቡ ላይ የወሰደው የኃይል እርምጃ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ይፋ እንዲደረግ፤ የክልሉ ፖሊስ በወሰደው የኃይል እርምጃ ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ብዛትና የጉዳቱ መጠን በአስቸኳይ ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ ተገቢ ህክምና እና ካሳ እንዲከፈላቸው፤ ይህንን የፈጸሙ አካላትም ለፍርድ እንዲቀርቡ በአጽንኦት እንጠይቃለን፡፡

በአንድነት ፓርቲ በኩል ይህንኑ በህዝብ ላይ የደረሰ ጉዳት ለማጣራትና ለመከታተል በስራ አስፈጻሚው አስቸኳይ ግብረ ኃይል ተቋቁሟል፡፡ ግብረ ኃይሉ ወደ ቦታው በማቅናት ጉዳዩን ካጣራ በኋላ የደረሰበትን መረጃ እና በፓርቲያችን የሚወስደውን ተጨማሪ አቋም በተመለከተ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር
መጋቢት 4 ቀን 2006 ዓ.ም


በሴቶች ሩጫ ላይ በመንግስት ላይ ተቃውሞ አሰምታችኋል የተባሉ 7 ሴቶች እና 3 ወንዶች ፍርድ ቤት ዋሉ

$
0
0


ከዳዊት ሰለሞን

በሴቶች ሩጫ ላይ በመንግስት ላይ ተቃውሞ አሰምታችኋል የተባሉ 7 ሴቶች እና 3 ወንዶች ፍርድ ቤት ቀረቡባሳለፍነው ሳምንት ታላቁ ሩጫ ባዘጋጀው የሴቶች ውድድር ላይ በመሳተፍ ተቃውሞ በማሰማታቸው ለእስር የተዳረጉት ሰባት ሴቶችና ተባባሪ ተደርገው የታሰሩ ሶስት ወንዶች ዛሬ በነበራቸው ቀጠሮ መሰረት ቀበና በሚገኘው ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡

ታሳሪዎቹ በአንድ ፖሊስ ጣብያ ውስጥ የከረሙ ቢሆንም ፖሊስ ወደ ፍርድ ቤቱ በመጀመሪያ ያመጣው ወንዶቹን ነበር፡፡ሴቶቹ ለሰዓታት ዘግይተው በሩጫው ወቅት ለብሰውት የነበረውን ባለ ሙሉ ቢጫ ቀለም ቲ ሸርት እንደለበሱ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡

ዳኛው ከተሰየሙ በኋላ ከሳሽን በመወከል የቀረቡ ሁለት ፖሊሶች ‹‹ምርመራችንን ባለማጠናቀቃችን ተጨማሪ የሰባት ቀን የምርመራ ግዜ ይፈቀድልን››በማለት ጠይቀዋል፡፡የተከሳሾች ጠበቃ(የጋዜጠኛ ርዕዮት ወላጅ አባት አቶ አለሙ ጎቤቦ) ፖሊስ ደምበኞቼን በእስር ለማቆየት ካለው ፍላጎት እንጂ ወንጀሉ ተፈጸመ የተባለው በአደባባይ በመሆኑ ተጨማሪ ምርመራ አያስፈልገውም ስለዚህ ደምበኞቼ ጉዳያቸውን በውጪ ሆነው እንዲከራከሩ ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ያክብርልኝ››በማለት ተከራክረዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ የመናገር እድል እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ሲፈቀድላቸው ‹‹ሲቪል የለበሱ ሰዎች እየመጡ በሌሊት ጭምር ከታሰሩበት ቤት እንዲወጡ በማድረግ እንገድላችኋለን፣ከአሸባሪዎች ጋር መስራታችሁን አቁማችሁ አብራችሁን ስሩ፣በመጥረጊያ አናትሽን ብልሽ የሚደርስልሽ አይኖርም››የሚሉ ማስፈራሪያዎችን እንዳደረሱባቸው በመግለጽ ዋስትና ይሰጠን ሲሉ አቤት ብለዋል፡፡

ፖሊሶቹ በተከሳሾች የቀረበው ሐሰት መሆኑን በመግለጽ ‹‹ሴቶቹ ለምሳሌ ወደዚህ ለመምጣት የቆዮት የለበሱትን ቲሸርት እንዲለውጡ ሲነገራቸው እምቢ በማለታቸው ነው፡፡ በመኪና ላይ ይጨፍሩ ነበር፡፡እስር ቤት ውስጥም ሌሎች እስረኞችን ያነሳሳሉ ››ብለዋል፡፡

ቲሸርቱ በፍርድ ቤት እንዳይለበስ ያልታገደ በመሆኑ መልበስ መብታቸው ነው ያሉት አቶ አለሙ ‹‹ደምበኞቼን ፖሊስ በፈለገው ጊዜ ሊያገኛቸው የሚችል በመሆኑ በእስር መቆየታቸው ተገቢ አይደለም››ብለዋል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጡት ዳኛው ‹‹ፖሊስ የእስረኞቹን መብት ማክበር ግዴታው ነው ስለዚህ የተባለው ነገር እንዳይደገም በማለት የዋስትና መብታቸውን ሳይጠብቁ ለፖሊስ ተጨማሪ አራት ቀን በመፍቀድ ተጠርጣሪዎቹ ወደ ፖሊስ ጣብያ እንዲመለሱ አዘዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ታሪክ ሊሆን ነው

$
0
0

ከሰሜን ኮከብ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ክፍል ( ዲፓርትመንት) መዳከሙን ስሰማ በጣም አዘንኩ። ዲፓርትመንቱ እኔ በነበርኩበት ጊዜም ፣ ከዘርና ከሃይማኖት ጋር በተያያዘ፣ ብዙ ችግሮችን ያስተናግድ ነበር። ኢህአዴግ ” ዲፓርትመንቱ የነፍጠኛው መመሸጊያ ዋሻ ሆኗል” በሚል ብሄር ብሄረሰቦች በብዛት እንዲገቡበት ይወተውት ነበር። አንድ የአማራ ተወላጅ ተማሪ ከፍተኛ ነጥብ ቢያመጣም፣ ከሌላው ብሄረሰብ ሰው ካልታጣ በስተቀር፣ መምህር ሆኖ የመቀጠር እድል አልነበረውም። በ1992 ዓም ነው፣ሁለት ሰቃይ ጓደኞቼ መምህር ለመሆን ያመለክታሉ። በጊዜው የዲፓርትመንቱ ሃላፊ የነበሩት ትግራዋይ ዶክተር ፣ሰቃዮቹን ትተው፣ አንድ የኦሮሞ እና አንድ የትግራይ ተወላጅ ምሩቃንን ይቀጥራሉ። አዲሶቹ ተቀጣሪዎች የነበራቸው ድምር ነጥብ ( Cumulative GPA) ጓደኞቼ ከነበራቸው ነጥብ በጣም ያነሰ ነው። በእንዲህ አይነቱ አሰራር ልባቸው የተሰበረው ጓደኞቼም እስከ ሴኔቱ ድረስ ክስ መሰረቱ፣ በመጨረሻ ያገኙት መልስ ግን ” የብሄር ተዋጽዎን ለመጠበቅ ሲባል የተወሰደ እርምጃ ነው” የሚል ነበር።
ለታሪክ ዲፓርትመንት መዳከም ዋናው ምክንያት የዘር ፖለቲካ የትምህርት ስርዓቱን መቆጣጠሩ ነው።
addis ababa un
በታሪክ ክፍለ ጊዜ ተማሪዎች ብሄርና ፖለቲካ ለይተው ሲደባደቡ አስታውሳለሁ ። የተወሰኑ የኦሮሞ ወይም የትግራይ ተወላጆች የተጻፉ ታሪኮችን ወይም ስያሜዎችን ለመቀበል እየተቸገሩ ከአስተማሪዎች ጋር ዘወትር ይጣሉ ነበር ። መምህራን “ማስተማር አልቻንልም” ብለው ስራ እስከማቆም የደረሱበት ጊዜም ነበር። ያም ሆኖ በማይነር ( በሁለተኛ ትምህርት) ከሚማሩት ውጭ፣ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ታሪክ ያጠኑ ነበር ። ታሪክ ለመማር የመጡ ሌሎች አፍሪካውያንና ጥቁር አሜሪካውያንም ነበሩ። ተማሪው ከመብዛቱ የተነሳ ተወዳድሮ የማለፊያ ነጥብ ለማምጣት እጅግ ጭንቅ ነበር። አስተማሪዎችም የተማሪውን ፈተና አርመው በጊዜ ለመመለስ ይቸገሩ ነበር።

አንድ ገጠመኜን ላውጋችሁ። ነፍሳቸውን ይማርና ፕ/ር ሁሴን አህመድ የማጠቃለያ ፈተና ይፈትኑናል። የቀረቡልን ጥያቄዎች 4 ሲሆኑ መልስ መስጠት የሚጠበቅብን ለሁለቱ ብቻ ነው ። ለጥያቄዎቹ መልስ መጻፊያ ይሆን ዘንድ እያንዳንዳቸው 4 ገፆችን የያዙ ሁለት “ሉክ” ወረቀቶች ታደሉ። የጥያቄዎችን ማነስና የገፆችን መብዛት ስመለከት ” ምንድነው የምጽፈው” እያልኩ መጨነቅ ጀመርኩ። እኔ “የሸመደድኩትን” እያጠነጠንኩ ገና አንድ ገጽ ጽፌ ሳልጨረስ ከሁዋላየ የተቀመጠው ተማሪ 8ቱን ገጽ ጨርሶ ወረቀት እንዲጨመረው ጠየቀ፤ ሌሎችም እንዲሁ እያከታተሉ ወረቀት ጠየቁ፣ “በቃ ተሸውጃለሁ” ማለት ነው እያልኩ በድንጋጤ ወረቀቱን ለመሙላት ስል ብቻ እጽፋለሁ። መጀመሪያ ወረቀት ይጨመርንልን ያሉት ጓደኞቼ፣ የተጨመረላቸውንም ወረቀት ጨርሰው በድጋሜ ጠየቁ። አስተማሪውም “የመጨረሻ ወረቀታችሁ ነው” ብሎ አስጠንቅቆ ሰጣቸው። ” ፕሮፌሰር እኔ ጋ አራት የተረፉ ገጾች አሉና ከፈለጉ ልስጣቸው” ለማለት ሲዳዳኝ አንዱ ፈተናውን ጨርሶ ተነሳ፣ በዚህን ጊዜ ልቤ ከሁለት ተከፈለ፣ “ኤፍ” እንደምቅምም ገባኝ። ተስፋ የቆረጠ ሰው ማሰብ አይገደውምና መጻፌን አቁሜ ” እውነት ፕሮፌሰር የዚህን ሁሉ ታማሪ ወረቀት ያርመው ይሆን?’ እያልኩ ከራሴ ጋር ሙግት ጀመርኩ።
ትንሽ ቆይቶ ፕሮፈሰሩ ” you are left with 20 minutes only ” አሉ። በ 20 ደቂቃ ውስጥ፣ አንዳንዴም ቀረርቶ እየጨመርኩበት፣ 7 ገጾችን ጽፌ ለመምህሩ አስተያየት መስጫ ይሆን ዘንድ ግማሽ ገጽ አስተርፌ ተነሳሁ። ” ከሁለት ሳምንት በሁዋላ ፕ/ር ሁሴን ” ከ20 ገጽ በላይ የጻፋችሁ ተማሪዎች ወረቀታችሁን ወስዳችሁ እንደገና ጽፋችሁ አምጡ ብለው ሲያዙ ክፍሉ በሳቅ ተናጋ። እግዚሄር ይመስገን ውጤቱም እንደፈራሁት ሳይሆን ቀረ። ከ14 ዓመታት በሁዋላ ይህ የታሪክ ዲፓርትመንት ሰው አልባ ሆነ። ባለታሪኩዋ አገሬ ታሪክ አልባ ስትሆን ተሰማኝ።

በጎንደር አድማ መርታችኋል የተባሉ 6 ታክሲ ሹፌሮች በእስር ቤት እየተንገላቱ ነው

$
0
0

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)


ክሱን ከፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ለማገናኘት የሞከረው ፖሊስ አልተሳካለትም
ምንሊክ ሳልሳዊ :- በጎንደር ከተማ የታክሲ ሹፌሮች የስራ ማቆም አድማ ላይ ተቃውሞ አሰምታችኋል አድማውን መርታችኋል በሚል ሰበብ የታሰሩ 6 ሰዎች እንዳሉ ከአከባቢው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል:: ከአንድ ወር በፊት የጎንደር ከተማ የታክሲ ሹፌሮች አዲሱን የትራፊክ የቅጣት ደንብ በመቃወም የስራ ማቆም አድማ መምታታቸውን ተከትሎ አድማውን አስተባብረዋል በሚል ሰበብ ተፈጥሮ ከየመንገዱ ከስራቸው እና ከየቤታቸው ታፍነው የተወሰዱ የታክሲ ሹፌሮች በእስር ቤት ውስጥ እየተሰቃዩ መሆኑን ለወሕኒ ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ገልጸዋል::

ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት ቀርበው የዋስትና መብታቸው ሳይከበር ወደ እስር ቤት የተመለሱት የታክሲ ሹፌሮች ከሰማያዊ ፓርቲ የመጣ ትእዛዝ ነው የስራ ማቆም አድማ ያደረጋችሁት በሚል ጉዳዩን ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር በሃሰት ለማገናኘት በፖሊሶች በሃይል ለማሳመን ጥረት ቢደረግም እንዳልተሳካ ምንጮቹ ገልጸው እስካሁን ምንም አይነት መረጃም ሆነ ማስረጃ መርማሪዎች በማጣታቸው በስራ ማቆም አድማ ላይ የተሳተፉ የታክሲ ሹፌሮችን በታሰሩት ላይ እንዲመሰክሩ በጥቅም እያግባቧቸው መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል::

በአድማው ወቅት የታክሲ ባለንብረቶችም የታሪፍ ማስተካከያ አለመደረጉን በመቃወም የታክሲ ሹፌሮቹን ተቀላቅለው የነበር ሲሆን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባለስልጣናት ሾፌሮቹና ባለንብረቶቹ ወኪል ልከው እንዲነጋገሩ በጊኤው የጠየቁ ቢሆንም ሹፌሮቹ “የክልሉ መንግስት ወከሎችን በተደጋጋሚ የማሰር ልምድ ስላለው ወኪል አንልክም” ብለው እንደነበር ይታወሳል::

የነአርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አዲስ ሃይማኖት “ቅዱስ ኤልያስ ይዞት የመጣውን መፅሐፍ” ቤተ ክርስትያን እንድትቀበል ጠየቀ

$
0
0

Jemanesh Solomon
ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንደዘገበው የነአርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አዲስ ሃይማኖት “ቅዱስ ኤልያስ ይዞት የመጣውን መፅሐፍ” ቤተ ክርስትያን እንድትቀበል ጠየቀ። የጋዜጣው ዘገባ እንደወረደ ይኸው፦

መጽሐፉ ለአቡነ ማትያስና ለጠ/ሚ ኃይለማርያም እንዲደርሳቸው ተደርጓል
ደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠ/ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታናሁ እና ለተመድ ተልኳል

ከተፃፈ ከ2 ሺህ ዓመታት በላይ አስቆጥሯል የተባለውንና ስለ ቅዱስ ኤልያስ መምጣት ምስጢር የሚተነትነውን መጽሐፍ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተቀብላ ወደተለያዩ ቋንቋዎች በማስተርጎም ምዕመናኖችን እንድታስተምር፣ “ማህበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” ለቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በጻፈው ደብዳቤ ጠየቀ፡፡

ማህበሩ፤የመጽሐፉን ኮፒዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እና ለብፁዕ አቡነ ማትያስ ህዝቡን እንዲያስተምሩበት ከሚያሳስብ ደብዳቤ ጋር መላኩን አስታውቋል፡፡
አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አባል የሆነችበት ማህበረ ሥላሴ፤“ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን ለሁለት ሺህ ዘመን ስትጠብቀው የቆየችውን ምስጢራዊ መጽሐፍ በአደራ የመረከብና ለዓለም ሁሉ የማሳወቅ ፅኑ ኃላፊነትን ይመለከታል” በሚል ርዕስ ለፓትርያርኩ፣ በግልባጭ ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እንዲሁም ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔትናሁ እና ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት በፃፈው ደብዳቤ “ማህፈድ ብርህት ዘዲዮስቆሮስ አንበሳ” በሚል ርዕስ በግዕዝ ቋንቋ የተፃፈውን መጽሀፍ፣ የቤተ-ክርስቲያኗ ሊቃውንት ተቀብለው ምእመናኑን ስለ ቅዱስ ኤልያስ እና ትክክለኛይቱ ሰንበት እንዲያስተምሩበት አሳስቧል፡፡

ደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር የተላከው ኢትዮጵያና እስራኤል በመንፈሣዊ አሰራር አንድ ስለሚሆኑበት ሁኔታ ለማመልከት ነው ያሉት የማህበሩ አመራሮች፤ለተባበሩት መንግሥታት የተላከውም መልእክቱ ለዓለም ሁሉ እንዲዳረስ ስለሚፈለግ ነው ብለዋል፡፡
ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት እንደተፃፈ የሚነገርለት መጽሐፉ፤ ስለ ቀዳሚት ሰንበት ምንነትና ዘለዓለማዊነት በግልፅ እንደሚያብራራ እንዲሁም የኢትዮጵያና የእስራኤልን አንድነትና ትንሳኤ ምስጢር ተንትኖ እንደሚያስረዳ ተጠቁሟል፡፡
ማህበሩ በላከው መልዕክት፣ ቅዱስ ኤልያስ ከብሄረ ህያዋን ይዞት የመጣውን መጽሀፍ፣ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት እንዲመረምሩት፣ በተለያዩ ቋንቋዎች እንዲተረጎምና እንዲታተም፣ ምዕመናንም እንዲያነቡት የማድረግ ግዴታ ፓትርያርኩ እንዳለባቸው ያሳስባል፡፡ “ይህ ሳይሆን በእንቢተኝነትና በቸልታ ለዘመናት በተስፋ የተጠበቀውን ይህን መጽሀፍ እንዳይቀርብ ቢያደርጉ፣ ከብሄረ ህያዋን የመጣው ቀናኢ ነቢይ ዓለምን ሁሉ እየገሰፀ ባለበት ኃያል፣ ስልጣኑ ፅኑ ፈራጅነቱና ቁጣው የሚፈርድ መሆኑን አረጋግጠን እንነግርዎታለን” ብሏል፡፡ “ለቤተ-ክርስቲያኒቱ ሲኖዶስ እና ካህናት ጥፋትና የመጨረሻው ውድቀት ነው” ሲልም ለመፅሃፉ ትኩረት እንዲሰጥ ማህበሩ አበክሮ አሳስቧል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ የፓትርያርኩን ጽ/ቤት እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጽ/ቤት በስልክ አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

የስርዓቱ ደጋፊ የሆነችው ድምጻዊት ሃመልማል አባተ ለሁለተኛ ጊዜ ከአሜሪካ አፍራ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰች

$
0
0

በአፍቃሬ ወያኔነቷ የምትታወቀው ድምጻዊት ሃመልማል አባተ አዲስ አልበሟን ለማስመረቅና የተለየያዩ ኮንሰርቶችን ለመሥራት ወደሰሜን አሜሪካ መጥታ የነበረ ቢሆንም በደረሰባት ቦይኮት በተመልካች እጦትና በፕሮሞተሮች መጥፋት አፍራ ወደ አዲስ አበባ መመለሷ ታወቀ።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ በሰብአዊ መብት ጥሶትና ንጹሃንን በእስር ቤት ያሰቃያል እየተባለ በዓለም አቀፍ ተቋማት ጭምር የሚነገርለትን የወያኔ/ኢሕአዴግ ስርዓት በመደገፍ የምትታወቀው ድምጻዊት ሃመልማል አባተ በዋሽንግተን ዲሲ ከፍተኛ ገንዘብ ወጥቶ በቨርጂኒያ ክሪስታል ከተማ በሂልተን ሆቴል የሲዲ ማስመረቂያ ኮንሰርት አዘጋጅታ 55 ሰዎች ብቻ የተገኙ ሲሆን አንድም አርቲስት በሲዲ ምርቃቱ ላይ አለመገኘቱ አነጋጋሪ ሆኗል። በተለይ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ በርካታ አርቲስቶች የሚገኙ እንደመሆኑ መጠን በሃመልማል አባተ ሲዲ ምርቃት ኮንሰርት ላይ አንድም አርቲስት አለመገኘቱ ኢቢኤስ የተባለው ቲቪ ሳይቀር እንዳስገረመው በወቅቱ መዘገቡ ይታወሳል።

(ሃመልማል በዲሲ አዘጋጅታቸው የነበረውና በተመልካች ድርቅ የተመታው የሲዲ ምርቃት ኮንሰርት ፍላየር ይህ ነበር)

(ሃመልማል በዲሲ አዘጋጅታቸው የነበረውና በተመልካች ድርቅ የተመታው የሲዲ ምርቃት ኮንሰርት ፍላየር ይህ ነበር)


ሃመልማል በወያኔ/ኢህአዴግ እየተረገጠ ያለውን ሰፊውን ሕዝብን ክዳ ለመሬት ቀሚው፣ ለመሬት ሻጩ፣ ለበዝባዡ፣ ለጨፍጫፊውና ለሰብአዊ መብት ረጋጩ ወያኔ ተቆርቋሪ ሆና በመቅረቧ ከጥቂት ዓመታት በፊት` በጀርመን ሃገር የሙዚቃ ኮንሰርት አዘጋጅታ ሕዝቡ ቦይኮት በማድረጉ 18 ሰዎች ብቻ የተገኙ ሲሆን ከ3 አመት በፊትም እንዲሁ ወደ ሚኒሶታ በመምጣት ኮንሰርት አዘጋጅታ ከ12 ያነሰ ሰው ብቻ በመገኘት በተመልካች ድርቅ ተመትታ ወደ ሃገሯ ተመልሳለች፤ ያሉት የመረጃ ምንጮች ሃመልማል ከስርዓቱ ጋር ያላት የጥቅም ግንኙነት የተረሳላት መስሎ ወደ አሜሪካ በድጋሚ ብትመጣም በዋሽንግተን ዲሲ 55 ሰዎች ተግኝተው አሳፍረዋታል። በዲሲ ኮንሰርት ሲዘጋጅ እስከ 5 ሺህ ሰው እንደሚገባ ልብ ይሏል።

ሃመልማል በዳላስ ከተማ በፋሲል ደመወዝ ስም በመጠቀም፤ (ሕዝቡ የፋሲል ደመውዝ አድናቂ በመሆኑና እርሱን ተከትሎ በመግባቱ) በኮንሰርቱ ላይ ቁጥሩ ጨመር ያለ ሰው ቢገባም በሎስ አንጀለስ ከተማ የቀድሞ ባለቤቷ እና የልጇ አባት በሚያስተዳድረው ሮዝሊን የሲዲ ምርቃትና ኮንሰርት ብታዘጋጅም በተመሳሳይ ቦይኮት ተደርጋ በተመልካች ድርቅ ተመትታለች። በዚህም ሞራሏ የተሰበረው ሃመልማል ከስህተቷ ተምራ ወደ ሕዝብ ከመመለስ ይልቅ ወደ ሃገር ቤት በመመለስ ነገሩን ለማብረድ ብትሞክርም እንዲህ ያለው ቦይኮትና በየከተማው ያሉ ፕሮሞተሮች ያለመጋበዝ ትግል ታግዞበት ወደ ሃገሯ ልትመለስ በቅታለች።

ዲያስፖራው ከወያኔ ጋር በጥቅም የተሳሰሩ ድምጻዊያንን ቦይኮት ማድረጉ የሚያስመሰግን ነው የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች ይህ ጉዳይ በርትቶ ሊቀጥል እንደሚገባው አስታውቀዋል። እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች የስርዓቱ ደጋፊ የሆኑ አርቲስቶች በሃገር ቤት ከወያኔ ጋር በመሞዳሞድ የሚያገኙት ጥቅም ውጭ ሲመጡ ሊያገኙ አይገባም ይላሉ። ዲያስፖራው ሃገሩን የሚያከብረውን አርቲስት እንደሚያክብረው ሁሉ ከወያኔ ጋር ለሆዱ ያደረውን ድምጻዊም በማግለል ተመልካች አልባ ማድረግ እንደሚገባው አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

ከሃመልማል አባተ ውጭ ነዋይ ደበበ፣ ሰለሞን ተካልኝና የመሳሰሉት ድምጻዊያን በዲያስፖራው ኪሳራ እንደደረሰባቸው ይታወሳል።

አንድነት እና መኢአድ የፊታችን ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም የቅድመ ውህደት ፊርማ ሊፈራረሙ ነው

$
0
0

UDJ
aeup
የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤትና የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት አባላት በጋር ባካሔዱት ስብሰባ ሁለቱ ፓርቲዎች የፊታችን ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም የቅድመ ውህደት ፊርማ እንዲያደርጉ መመሪያ ማስተላለፋቸውን ስብሰባውን የተከታተለው የፍኖተ ነፃነት ባልደረባ ዘገበ፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት እና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ላዕላይ ምክር ቤት አባላት ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2006 ዓ.ም በመኢአድ ጽ/ቤት ባደረጉት ስብሰባ የሁለቱ ፓርቲዎች በአስቸኳይ እንዲዋሀዱ መመሪያ ያስተላለፉት ሁለቱን ፓርቲዎች ፓርቲዎች ለማዋሀድ እያሸማገሉ የሚገኙ ምሁራንና ታዋቂ ግለሰቦች የተካተቱበት ኮሚቴ ያቀረባቸው የማስማሚያ ነጥቦች ከቀረቡ በኋላ እና የሁለቱም ፓርቲዎች ፕሬዘዳንቶችና የውህደት ኮሚቴ አባላት ውህደቱ የዘገየበትን ምክንያት ከዘረዘሩ እንዲሁም የሁለቱ ፓርቲዎች ምክር ቤት አባላት ሰፊ ውይይትና የመፍትሔ ሀሳብ ካቀረቡ በኋላ ነው፡፡ የቅድመ ውህደት ፊርማው በሚፈረምበት ዕለት ሁለቱም ፓርቲዎች የውህደቱን ሂደት የሚያመቻቹ ወኪሎቻቸውን እንደሚያሳውቁም የፍኖተ ነፃነት ባልደረባ ዘግቧል፡፡

ብርሃኑ ተዘራ (ላፎንቴን) በሚኒሶታ የተሳካ የሙዚቃ ኮንሰርት አቀረበ

$
0
0

tezera
(ዘ-ሐበሻ) ተበቺሳ የተሰኘውን አልበሙን በቅርቡ የለቀቀው ድምፃዊ ብርሃኑ ተዘራ (ላፎንቴን) በሚኒሶታ ትናንት ማርች 15 ቀን 2014 ዓ.ም የተሳካ የሙዚቃ ኮንሰርት አቀረበ።

በእናት ኢንተርቴይመንት እና በዲጄ ቢኬ አስተናጋጅነት በሚኒሶታ ራስ ላውንጅ በተደረገው የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ብርሃኑን ለማየት በርካታ የሚኒሶታ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በሙዚቃውም መደሰታቸውን ከተለቀቁ ቪድዮዎች መረዳት ይቻላል። ብርሃኑ አማርኛ፣ ኦሮሚያ፣ ትግርኛና ሌሎች የኢትዮጵያ ብሔረሰብ ሙዚቃዎችን የተጫወተ ሲሆን በተለይ “አምበሳው አገሳ” የሚለውን ሙዚቃ ሲጫወት የሚኒሶታ ነዋሪ የአንድነት ስሜቱን መቆጣጠር ተስኖት ሲፈነጥዝ ዘ-ሐበሻ የቀረጸችው ቪድዮ ያሳያል።

አርቲስት ብርሃኑ ተዘራን ከኮንሰርቱ በኋላ ዘ-ሐበሻ አነጋግራው በሚኒሶታ የተደረገለት አቀባበል ያማረ እንደነበርና ከፍተኛ ሕዝብ በኮንሰርቱ ላይ በመገኘቱ መደሰቱን ጠቁሟል።

ከብርሃኑ ተዘራ ጋር ያደረግነውን ቃለምልልስ እስከምናቀርብ ከሙዚቃ ኮንሰርቱ ቪድዮ አንዱን እንጋብዛችሁ።


Hiber Radio: የወቅቱን የኢትዮጵያውን አገዛዝ ጨምሮ ምዕራባውያን ለአምባገነኖች የሚሰጡት ድጋፍ ተገቢ አለመሆኑን አንድ አሜሪካዊ ምሁር ገለጹ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ መጋቢት 7 ቀን 2006 ፕሮግራም
<<...የኢትዮጵያ ሕዝብ በውስጥም በውጭም ያለው ወያኔ በምስጢር ለሱዳን የሰጠው ድንበራችን ከመካለሉና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰነድ ከመስፈሩ በፊት የተቃውሞ ድምጹን ያሰማ...>>

አቶ አገኘሁ መኮንን የድንበር ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የም/ቤት አባል ለሱዳን ስለተሰጠው የአገራችን መሬት ለህብር ከስዊዘርላንድ ከሰጡት ቃለ መጠይቅ(ሙሉውን ያዳምጡት)

<...የሚሊዮኖች ድምጽ ሁለተኛ ዙር እንቅስቃሴንም በውጭ ያለው በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብት መከበር የሚታገለው አገር ወዳድ ወገን ሁሉ መደገፍ አለበት ይሄ የአንድነት ፓርቲ ደጋፊዎች ብቻ ሳይሆን የአገር ጉዳይ ነው...>

አቶ ግርማይ ግዛው የአንድነት የሰሜን አሜሪካ የድጋፍ ማህበር ሊቀመንበር ስለ አዲሱ የሚሊዮኖች ድምጽ ሁለተኛ ዙር እንቅስቃሴ ከሰጡን ቃለ ምልልስ የተወሰደ

<...በቬጋስ የሚጘኙ ኢትዮጵያውን በየጊዜው በአገራቸው ያለውን ትግል ይደግፋሉ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነትም የአዲስ አበባውን እንቅስቃሴ በገነዘብ እንደግፋለን ስንል ከዚያ የተለየ አይደለም...>

አቶ ሰለሞን በቀለ በቬጋስ የአንድነት የድጋፍ ቻፕተር ሰብሳቢ

<...አባቶቻችን በአድዋ አንድ ላይ ሆነው መገዛት ባርነት የሚያመጣውን ውድርደት በመረዳት በአድዋ ታሪክ ሰርተዋል ይሄ ትውልድ ግን...>>

አቶ ኤልያስ ረሺድ በስዊዘርላንድ የአድዋ በዓል አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ትላንት ስላደረጉት በጄኔቭ የአድዋ በዓል አከባበር አስመልክቶ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ

<<...ኢትዮጵያውያን ብንተባበር አባቶቻችን እናቶቻችን በአደዋ ካስመዘገቡት ድል በላይ ዛሬ ማምጣት እንችላለን...>>

አቶ ኦባንግ ሜቶ ከጄኔቭ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ(ሙሉውን ያዳምጡት)

የሩሲያና የዩክሬን ውዝግብና የቀረው ምዕራብ አለም ከሩሲያ ጋር የገባበት ፍጥጫ(ልዩ ዘገባ)

<<...በኦባማ ኬር የጤና ሽፋን ኢንሹራንስ ስንገዛ በተለይ ኢንሹራንሱ የሚሰጠንን ሽፋንና የምንከፍለውን መጠን በደንብ ማወቅ ያስፈልጋል..ያልተመዘገቡ የጤና ሽፋን የሌላቸው መመዝገብ አለባቸው...>>

ዶ/ር ኤፍሬም መኮንን ከአትላንታ ስለ ኦባማ ኬር ከሰጡት ማብራሪያ

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

የወቅቱን የኢትዮጵያውን አገዛዝ ጨምሮ ምዕራባውያን ለአምባገነኖች የሚሰጡት ድጋፍ ተገቢ አለመሆኑን አንድ አሜሪካዊ ምሁር ገለጹ

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ካልተከበረ ልማት የሚባለው ዘለቄታ እንደሌለው ገለጹ

ጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ አንድ ሺህ ቀናቶች በእስር ቤት አሳለፈች

ኤርትራ ህገ ወጥ ብላ ካሰረቻቸው የመናውያን አሳ አስጋሪዎች የተወሰኑትን ለቀቀች

ከሳውዲ የኢትዮጵያውያንን ሰቆቃ እየተከታተለ የሚዘግበው የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በአገሪቱ የደህንነት ሰዎች መታሰሩ ተሰማ

አንድነትና መኢአድ ሐሙስ የቅድመ ውህደት ፊርማ ለማድረግ ወሰኑ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

በኩዌት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ አሳሳቢ ሆኗል

$
0
0

ምኒልክ ሳልሳዊ

በዚህ ሳምንት አትክሮት ማግኘት ከሚፈልጉ ወገኖቻችን በዋነኝነት በኩዌት የሚኖሩ እና በስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ናቸው:: ባሳለፍነው ቀናት በዋና ዜናነት በአገሪቱ የስፖርት ሚኒስትር መኖሪያ ቤት ውስጥ የምትሰራ ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ የአሰሪዋን ሴት ልጅ ገላለች ተብሎ የተዘገበውን ዜና ተከትሎ ኢትዮጵያውያን በስጋት ላይ ሲሆኑ እንዲሁም ተከራካሪ የዜግነት መብታቸውን የሚያስከብር ኤምባሲ መጥፋቱ እና በኤምባሲው የሚፈጸመውን ደባ በከፊል ለማየት እንሞክራለን::

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

በአሁኑ ወቅት በኩዌት ለኢትዮጵያውያን ነገሮች ሁሉ አስቀያሚ እና አስቸጋሪ እየሆኑ እንደሆን ለኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ቅርብ የሆነ ኢትዮጵያዊ ገልጿል::ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደረጉ በደሎች ተከራካሪ የመንግስት አካል እና የኤምባሲ ሰው መጥፋቱ ለአሁኑ ወንጀል መፈጸም እና ስጋት መንስኤ እንደሆነ ጠቁሟል::በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሱ በደሎች እና ከአሰሪዎቻቸው እና ከቀጣሪ ድርጅቶች ጠፍተው የሚመጡ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሃገራቸው መመለስ ሲገባው ከደላሎች ጋር በመመሳጠር ሌላ ስራ በማስገባት ችግሩ እንዲሰፋ ያደረገው እምባሲው እና ሆዳም ዲፕሎማቶቹ ናቸው ሲል ይኸው የኮሚኒቲው ሰው ገልጿል::

ኢትዮጵያውያን በኩዌት እስር ቤት እየተሰቃዩ ከፍተኛ ወጪ ከኤምባሲው እና ከኮሚኒቲው በማውጣት ደግሰው በመጨፈር ላይ በነበሩበት ሰአት ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠማቸው ሲሆን ወገኖቻችን በእስር ቤት እየተሰቃዩ ለምን እንዲህ አይነት ድግስ ይደገሳል:: አስፈላጊውን ወጪ በማድረግ ወደ ሃገራቸው የሚመለሱ ይመለሱ ያሉ ወገኖችን የተለያየ የኤምባሲ ትብብር በመከልከል ወደኤምባሲው በር እንዳይደርሱ በማገድ ከፍተኛ የሆነ የግል ጥቅምን ያማከለ በደል እየተፈጸመ መሆኑን የኮሚኒቲው ሰው አጫውቶናል::ለማንም ተደግሶ የማያውቅ ኮሚኒቲው የኢትዮጵያ ሆኖ እያለ ለሌሎች ኢትዮጵያውያን እና ግለሰቦች ሳያገለግል የትግራይ ልማት ማህበር አላማን ሲያስተምር ይውላል ሲሉ አባላቱ ይተቹታል:: የታሰሩትን ለጊዜው ተወት አድርጓቸው እና የሃገራችንን መልካም ገጽታ እናስተዋውቅ እያሉ ለዜጎች አትኩሮት በመንፈግ አሁን ላለንበት ስጋት አብቅተውናል ሲሉ ኢትዮጵያውያን በማማረር ይናገራሉ::

ኮሚኒቲው ሲቋቋም ለታሰሩ እና ለተቸገሩ መፍትሄ ይሆናል ተብሎ የነበረ ቢሆንም በስሙ መካከል ህዳሴ የሚል ቃል በመጨመር ቢሮውን ከነበረበት ቦታ ወደ ኤምባሲው ውስጥ በማዘዋወር ፖለቲካ እየሰበከ ኢትዮጵያውያንን ረስቷል ሲሉ ይናገራሉ::ሌላው ነገር ይላሉ ኢትዮጵያውያኑ ማንኛውንም ደብዳቤ በኤምባሲውም ይሁን በኮሚኒቲው ማህተም ተደግፎ ቢጻፍ በኩዌት ውስጥ ተቀባይነት የለውም ሲሉ ይገልጻሉ::የመኖሪያ ፈቃድ ለማሳደስ በእጃችን ፓስፖርት እያለ ፓስፖርቱን ለመቀበል የኩዌት መኖሪያ ፈቃድ የሚያድሰው አካል ብዙ መጉላላት እና ወከባ እንደሚፈጽምባቸው እና ይህንንም ለኤምባሲው ሪፖርት ቢደረግ የራሳችሁ ጉዳይ የሚል ዘለፋ አዘል መልስ እንደሚሰጡ ታውቋል::

በግድያ ወንጀል ተጠርጥራ የተያዘችው ኢትዮጵያዊት ተከትሎ የመኖሪያ መታወቂያዎች እንዲታደሱ መደረግ የጀመረ ሲሆን ካሁን በፊት NON KUWAITI የሚል ሲጻፍ የነበረ ሲሆን በኣሁን ሰአት ለኢትዮጵያውያን በተለየ መልኩ Ethiopian ኢትዮጵያዊ የሚል መጻፍ የተጀመረ መሆኑ ታውቋል::
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ምንም መከራከር የማይችል እና በመኪና ተገጭተው የሞቱ ታንቀው ራሳቸውን ከፎቅ ወርውረው የሞቱ ኢትዮጵያውያን ደብዛቸው እና የሞት ጉዳያቸው እንዳይነሳ ኮሚኒቴው በመሸፋፈን ለችግር እየዳረገን ነው ሲሉ በኮሚኒው ላይ አማረዋል::በ17 አመቷ ወደ ኩዌት የገባችው እና በአሁን ሰአት የ22 አመት ወጣት የሆነችው በግድያ ተጠርጥራ የተያዘችው ኢትዮጵያዊት በአሰሪዎቿ ልጆች የተደፈረች መሆኗን ለኤምባሲው ቅርብ የሆነ ግለሰብ ተናግሯል::ግድያውን ከመፈጸሟ በፊት በልጁ የተደፈረች እና ይህንን ጉዳይ ለሴት ልጂቷ ብትናገር የሚሰማት ያጣት እና የደበደቧት መሆኗን እና ይህንን ተከትሎ ወንጀሉን ፈጽማው ይሆናል የሚሉ ግምቶች በስፋት ይነገራል::

በኢምባሲው ውስጥ የሚደረገው ከፍተኛ በደል በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ሲሆን በኤምባሲው ውስጥ ከ400 እስከ 500 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን የሚገኙ ሲሆን: ከፍተኛ የሆነ መጉላላት እየደረሰባቸው ለኣእምሮ ጉዳት ለጭንቀት ለድብርት እና ለእብደት መዳረጋቸውን የገለጹ ሲሆን በኤምባሲው ውስጥ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ያለ ሲሆን ኤምባሲው ግን በድግስ እየተንበሸበሸ ኮሚኒቲው በየድህረገጹ የፌሽታ ፎቶዎችን በመርጨት ከፌሽታው ጀርባ ግን የኢትዮጵያውያን ሞት እና ሰቆቃ ለእይታ እንዳይበቃ እያደረገ ሲሆን አንድም ቀን የሞቱ እና የተበደሉ ኢትዮጵያንን ቦታ ሳይሰጥ የኢትዮጵያውያን መብት እና ነጻነት ሳያስከብሩ በአደባባይ ስንገላታ እያዩን ያላግጡብናል ያመናጭቁናል ከፖሊስ ጋር ይተባበሩብናል በማለት አቤቱታቸውን የሚሰማ አካል እንዳላገኙ እና በስጋት አጣብቂኝ ውስጥ መግባታቸውን ኢትዮጵያውያን ተናግረዋል:: ተጨማሪ ዘገባዎች ካሉ እንመለሳለን::

ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ስነምግባር ደንብ እንደማይፈርም አስታወቀ

$
0
0

በ2002ቱ ጠቅላላ ምርጫ መቃረቢያ ላይ ከ60 ያላነሱ ሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፓርቲዎችም እንገዛበታለን ብለው ከፈረሙበት በኋላም ሕግ ሆኖ የወጣው የስነ-ምግባር ደንብ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ እንደማይፈርም አስታወቀ። የፓርቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ለሰንደቅ እንደተናገሩት፤ የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብ በሀገሪቱ ፓርላማ ሕግ ሆኖ እስከወጣ ድረስ ፓርቲው እንደገና የሚፈርምበት ምክንያት የለም ብለዋል።
Yilkal Getnet
ኢህአዴግን ጨምሮ ዘጠኝ ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች በሚሳተፉበት የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለመግባት እንደ ቅድመ ሁኔታ እየቀረበ ያለው የምርጫ የስነ-ምግባር ደንብ በቅድሚያ ፈረሙ የሚባለውን “እኛ እንደቁምነገር አንቆጥረውም” ሲሉ የመለሱት ኢንጂነሩ ከኢህአዴግም ጋር የሚደረግ ማናቸውም ውይይት በቅድመ ሁኔታ ላይ መመስረት እንደሌለበት ገልፀዋል። በቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ ውይይትም ሆነ የጋራ ምክር ቤት የምክር ቤቱን ነፃነት ጥያቄ ላይ የሚጥል ስለሆነ ለመነጋገርና ለመወያየት የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብ ፊርማ እንደቅድመ ሁኔታ መቅረብ የለበትም ብለዋል።
“አሁን ተቋቁሟል የሚባለው የፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት በራሱ ብዙ ችግር ያለበት፣ ኢህአዴግና ደጋፊዎቹ ተሰብስበው የሚቀልዱበት እንጂ ሐቀኛ ሆኖ በነፃነት ውይይት የሚደረግበት ም/ቤት አይደለም” ሲሉ ኢንጂነር ይልቃል ተናግረዋል። ስለሆነም ፓርቲያቸው ለጊዜው በፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት የመሳተፍ ፍላጎት የለውም ብለዋል።

ከኢህአዴግ ጋር ለመነጋገርም ሆነ ተቀራርቦ ለመወያየት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መሆን እንዳለበት የጠቀሱት ኢንጂነሩ ሕጋዊ ፓርቲዎች ሆነን በምርጫውም እንደምንሳተፍ ሰለሚታወቅ ሌላ የተለየ ቅድመ ሁኔታ አያስፈልግም፣ ወደፊርማ የሚያስገባ ሕጋዊ መሠረት የለም ብለዋል።
ኢንጂነር ይልቃል ወደፊርማ የሚያስገባ ሕጋዊ መሠረት የለም ቢሉም፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ስነ-ምግባር ለመደንገግ በወጣው አዋጅ 662/2002 ዓ.ም አንቀጽ 21(6) እና (7) ላይ አዋጁ እንዲወጣ ተስማምተው በፈረሙ ፓርቲዎች እንደሚቋቋምና የስነ ምግባር ደንቡ ሲቀርፅ በልዩ ልዩ ምክንያት ያልተሳተፉ ሌሎች ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤቱ የሚያወጣውን የስምምነት ሰነድ መፈረም እንዳለባቸው ያስገድዳል።

ይሁን እንጂ፤ “የምንፈርመው ነገር የለም” ያሉት ኢንጂነር ይልቃል ፓርቲያቸው በዚህ ውስጥ የመሳተፍ ፍላጎት እንደሌለው አረጋግጠዋል። በምርጫውም የሚኖራቸው ተሳትፎም ደንቡን በመፈረምና አለመፈረም ላይ የተመሠረተ ሳይሆን በአጠቃላይ ገዢው ፓርቲ የፖለቲካውን መድረክ ጨምድዶ በያዘበት ሁኔታ ነው ብለዋል። አሁን ባለው ሁኔታም ምርጫው ፍትሐዊ ይሆናል ብለው እንደማያስቡ ነገር ግን መብቱን የማስከበር የሕዝቡ እንጂ የኢህአዴግ መልካም ፈቃድ አይደለም ሲሉ አስረድተዋል።
blue party
በቅርቡ ኢህአዴግ በመወከል ወደ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት አባልነት የተዛወሩት የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ደስታ አስፋው በበኩላቸው ማንኛውም ፓርቲ የፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ለመግባት በማመልከቻ መጠየቅ እንዳለበት ሀገር አቀፍ ፓርቲ መሆንና በጥር ወር 2002 ዓ.ም የወጣውን የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ስነ-ምግባር ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 662/2002 ዓ.ም መፈረም አለበት ብለዋል። ፓርቲዎቹ ወደ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሲመጡ የስነ-ምግባር ደንቡን እንዲፈርሙ የሚያስገድደው በፓርቲዎች ስምምነት ሕግ ሆኖ የወጣው አዋጅ እንጂ ኢህአዴግ አለመሆኑንም አያይዘው ጠቅሰዋል።

ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ

በጋዜጠኞች ላይ ያለ ማስረጃ የሚሰነዘሩ ውንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲቆሙ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ጠየቀ

$
0
0

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ)= ETHIOPIAN JOURNALISTS FORUM (EJF)

ጋዜጣዊ መግለጫ፦

ማህበራችን ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዶ የምዝገባ ሰርተፊኬት ለማግኘት የጀመረው እንቅስቀሴ በቅርቡ ከመንግስት አወንታዊ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ በማድረግ የተቋቋመለትን አላማ ለማሳካት እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም ከማስጠበቅና የመናገር ነፃነትን ከማበረታታት ባለፈም ከአህጉራችን አፍሪቃ ጋዜጠኞች ጋር በመተባበር የመላው አፍሪቃ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም የሚያስጠብቅና የመናገር ነፃነትን የሚያበረታታ አህጉራዊ ተቋም ለመመስረት ተነሳሽነትን ወስዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ በቅርቡም የምስራቅ አፍሪቃ ጋዜጠኞችን በማስተባበር አህጉር አቀፍ እንቅስቃሴያችንን ለማስጀመር ዝግጅት እያደረግን ነው፡፡
newspaper_for_rent
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተግባር ጋዜጠኛውን ሳይወክሉ የጋዜጠኛውን ስም የያዙት የኢጋማ፣ የኢነጋማና የኢብጋህ አመራሮች ነን የሚሉት ግለሰቦች በመቀናጀት በየሚዲያው እየቀረቡ ጋዜጠኞችንና የሚዲያ ተቋማትን ለማሸማቀቅ ያለመ ውንጀላና አሉባልታ የመንዛት ዘመቻ ጀምረዋል፡፡ ግለሰቦቹ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ቀርበው በጋዜጠኞች ላይ ከሽብር ፈጠራ እስከ ሀገር ማተራመስ የደረሰ የውንጀላ መዓት ቢደረድሩም አንዳችም ማስረጃ አላቀረቡም፡፡

ለምሳሌ የካቲት 22 ቀን 2006 ዓ.ም በታተመው አዲስ አድማስ ጋዜጣ (ቅጽ13 ቁጥር 737) ላይ ስማቸውን ደብቀው ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ጋዜጠኞች ሀገር ለማተራመስና ሽብር ለመፍጠር እየተዘጋጁ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ይሁን እንጂ “ምን ማስረጃ አላችሁ” ለሚለው የጋዜጠኛዋ ጥያቄ የመለሱት “እኛ እና እነሱ እንተዋወቃለን፡፡” የሚል አስገራሚ መልስ ነው፡፡ ይህ መሰረተ ቢስ ውንጀላ ጋዜጠኞችን ለማሸማቀቅ የተወረወረ በመሆኑ የኢጋማ፣የኢነጋማና የኢብጋህ አመራሮች ነን የሚሉት ግለሰቦች ጋዜጠኞችን እና የሚዲያ ተቋማትን ያለ ማስረጃ መወንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲያቆሙ ይጠይቃል፡፡

ejf
በመቀጠልም በሪፖርተር ጋዜጣ (የዕሁድ እትም ቅፅ 19 ቁጥር 1446) የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም “ኢጋማ በምስረታ ላይ ያለውን የጋዜጠኞች መድረክ አስጠነቀቀ” የሚል ዜና ተመልክተናል፡፡ ሆኖም በጋዜጠኞች ስም ተሰባስበው ጋዜጠኛውን የሚጠቅም አንዳች እንቅስቃሴ ሳያደርጉ ከመተኛታቸው ብዛት አልጋቸው ለረገበ ማህበራት ማስጠንቀቂያ ምላሽ በመስጠት ጊዜ በመሆኑም ምለሻችን በዝምታ መስራት ነው፡፡ የግለሰቦቹ የውንጀላ ንግግር የሚያስረዳው ከህግ፣ ከሞራል እና ከሙያዊ ስነምግባርም በላይ ራሳቸውን ለመሾም የሚፍጨረጨሩ መሆኑን ነው፡፡ ግለሰቦቹ በተለያዩ ጊዜያት መንግስት የፕሬስ ተቋማት ላይና ጋዜጠኞች ላይ የወሰዳቸውን ኢ-ህገመንግስታዊ እርምጃዎች እንደ ጋዜጠኛ ማህበር መሪ ከመኮነን ይልቅ የመንግስትን እርምጃ ሲያወድሱ ተስተውለዋል፡፡ በተጨማሪም በእስር ላይ ሆነው ህክምና በመከልከላቸው ለከፋ ስቃይ ስለተዳረጉ ጋዜጠኞችም ትንፍሽ ሲሉ አልታየም፡፡ እነዚህ የጋዜጠኛ ማህበራት መሪዎች ነን ያሉት ግለሰቦች እንደማህበር መሪ ሳይሆን እንደ ስለላ ተቋም ጋዜጠኞች እና አንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ሃገር ለማተራመስና የሽብር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው በይፋ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም

1ኛ. የሶስቱ ማህበራት መሪዎች አለን የሚሉትን መረጃ ለመንግስት በአፋጣኝ ሳይሰጡ መቆየታቸው በሀገራችን ህግ መሰረት ሊጠየቁው እንደሚገባ እንዲሁም
2ኛ. የሶስቱ ማህበራት መሪዎች በጋዜጠኞች እየተቀነባበረ ነው ካሉት የሽብርና ሀገር የማተራመስ እንቅስቃሴ ጀርባ እንዳሉ የጠቀሷቸውን ኤምባሲዎች በግልፅ ጠቅሰው ለመንግስት እና ለህዝብ እንዲያስታውቁ እንጠይቃለን፡፡

** ** **
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ)
መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም

የመብራት መቆራረጥ ያማረረው የአዲስ አበባ የሽሮሜዳ አካባቢ ነዋሪ ሰልፍ ወጣ

$
0
0

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)


በአዲስ አበባ የሚሰራጨው ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራድዮ እንደዘገበው የመብራት መቆራረጥ ያማረረው በአዲስ አበባ የሽሮሜዳ አካባቢ ነዋሪዎች ሰልፍ ወጡ።

ራድዮው እንዳነጋገራቸው ነዋሪዎች ገለጻ በአካባቢው የሚኖረው ሕዝብ በተደጋጋሚ ለሚመለከተው አካል ስሞታ ቢያቀርቡም መፍትሄ ባለማግኘታቸው ስልፍ ለመውጣት ምክንያት ሆኗቸዋል። ሰልፈኞቹ በተደጋጋሚ የሚያጋጥመውን እና ብልጭ ድርግም ከማለት ጀምሮ ለቀናት ጭራሹኑ እስከመጥፋት በሚደርሰው የኤሌክትሪክ ሃይል መማረራቸውን ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመገኘት ነው በተቃውሞ ሰልፍ ድምጻቸውን ሲያሰሙ ውለዋል ያለው ራድዮ ጣቢያው የሚመለከታቸውን የስራ ሃላፊዎች በማግኘት ምላሻቸውን ለመስማት የተደረገው ጥረት አልተሳካልኝም ሲል ዘግቧል።

በሌላ በኩል በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥን በመማረር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የተለያዩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ድምጻቸውን ለማሰማት የወጡ ሰልፈኞች ምላሸ ሳይሰጣቸው “ተበተኑ” በሚል ትእዛዝ እንዲበተኑ እንደሚደረግ ሸገር የዘገበ ሲሆን የሽሮሜዳ አካባቢ ነዋሪዎችም የሬድዮ ጣቢያው ጋዜጠኞች በቦታው ከመድረሳቸው በፊት እንዲበተኑ መደረጉን ነው አስታውቋል።

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የትራንስፖርት፣ የውሃ፣ የመብራት፣ የቴሌኮምዩኒኬሽን፣ የጋዝ እና የሌሎችም እጥረቶች ሕዝቡን እያማረሩት ከእለት ተእለት እንቅስቃሴው እየገደቡት ይገኛሉ።

የታክሲ ወረፋ በአዲስ አበባ

የታክሲ ወረፋ በአዲስ አበባ

አዲስ አበባ “ለእሪታ ቀን”እንድትዘጋጅ ተጠየቀ! “ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!!”

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ 1)በውሃ እጦት፣ 2)በኤሌክትሪክ ሀይል መቆራረጥ፣ 3)በትራንስፖርት ችግር፣ 4)በልማት ሰበብ በሚፈርሱ መኖሪያዎችና የንግድ ሱቆች የተነሳ ዜጎች እየተበደሉ በመሆናቸው፣ 5)በስልክ መስመር ችግር ና በሌሎችም ምክንያቶች የተነሳ ዛሬ የአንድነት ለፍትህና ዲሞክራሲ ፓርቲ የአዲስ አበባ ጽ/ቤት ስራ አስፈጻሚ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በከተማይቱ ደማቅ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ ይፋ አደረገ። “ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት” የሚል ርእስ የተሰጠው መግለጫ ከተማይቱ ከላይ በተጠቀሱት ችግሮች በመዘፈቋ ነዋሪው ከፍተኛ ችግር ውስጥ መውደቁን በመገንዘብ ገዢው ፓርቲ ከተማይቱን ብሎም አገሪቱን የመምራት ብቃት እንደሌለው የችግሮቹ ግዝፈት ዓይነተኛ ማሳያ ነው ብሏል፡፡
UDJ
ሙሉ መግለጫውን ዘሐበሻ እንደሚከተለው እንደወረደ አስተናግዳዋለች።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!!

መግለጫ

ሌሎች አገሮች ለዋና ከተሞቻቸው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የየአገሮቻቸው ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ማሳያ በማድረግ አለም አቀፍ ተቋማትንና ጎብኝዎችን በመጋበዝ የከተሞቻቸውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ያደርጋሉ፡፡

እንዳለመታደል ሆኖ ግን በብዙዎች የአፍሪካ አገራት የአህጉሪቱ መዲና ተደርጋ የምትጠቀሰው አዲስ አበበባችን ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደ ኋላ አየተጎተተች ለኑሮ ምቹ ከሆኑ ከተሞች ምድብ መቀላቀለ ተስኗት ለነዋሪዎቿ የማትመች የፈተና ምድር ሆናለች፡፡
UDJ 2
ኢህአዴግ ራሱን ልማታዊ መንግሥት በማድረግ ከሰየመበት ቅጽበት አንስቶ በልማት ሰበብ ዜጎች ከመኖሪያቸውና ቤተሰቦቻቸውን ከሚያስተዳድሩበት የንግድ ቦታ እንዲፈናቀሉ ተደርገዋል፡፡ በከተማይቱ እንዲነሱ የተደረጉት የንግድ ሱቆች በአብዛኛው በኪራይ ቤቶችና በቀበሌ ስም የተመዘገቡ በመሆናቸውም በሱቆቹ በመነገድ ይተዳደሩ የነበሩ ቤተሰቦች ባዶ አጃቸውን እንዲቀሩ ተደርገዋል፡፡

በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለውን የመንገድ ዝርጋታ የተነሳ የተጠና ሥራ ባለመሰራቱ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ የወጣባቸው መንገዶች ለምረቃ በበቁ በጥቂት ቀናት ልዩነት እንዲፈርሱ ተደርገዋል፡፡ የከተማው ነዋሪ ለሚጠቀምባቸው የመጓጓዣ አውታሮች ተለዋጭ መንገድ ባመዘጋጀቱም ለተጨማሪ ወጪ ተዳርጓል፡፡ ትራንስፖርት ማግኘት በሁሉም አካባቢዎች አስቸጋሪ በመሆኑ የከተማይቱ የሥራ እንቃስቃሴ ተዳክሟል፡፡ መንግሥት ‹‹የምትታለብ ላም›› በማለት የሚጠራው የኢትዮ ቴሌ ኮም አገልግሎት የለም የሚባልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ጭምር በኢትዮጵ ቴሌኮም የተንቀራፈፈ አገልግሎተ የተነሳ ባንኮችና የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለደምበኞቻቸው ተገቢውን ግልጋሎተ ማበርከት አልቻሉም፡፡

የታክሲ ወረፋ በአዲስ አበባ

የታክሲ ወረፋ በአዲስ አበባ


የከተማይቱ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር የተወሰኑ ሠራተኞች ችግር እንደሆነ ተጠቁሞ ሠራተኞች ለስንብት ቢዳረጉም የኤሌክትሪክ መቆራረጥና ለረጅም ግዜ መጥፋት የከተማይቱ ኢንዱስትሪዎች ፤ንግድ ተቋማትንና ነዋሪውን እያማረረና ህይወቱን እያመሰቃቀለ ከመሄድ ውጭ ምንም አይነት ለውጥ አልታየበትም፡፡ በከተማይቱ ውሃ ማግኘት እንደ ትልቅ እድል መቆጠር ጀምሯል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የከተማይቱ 75% ነዋሪ ውሃ እንደሚያገኝ ቢናገሩም መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን በተቃራኒው ሆኗል፡፡ ጊዜያቸውን በትምሀርት ገበታቸው ላይ በመገኘት ማሳለፍ ይገባቸው የነበሩ ተማሪዎች ውሃ ለመቅዳት ረዥም መንገድ ለመጓዝ በመገደዳቸው የትምህርት ጊዜአቸው እየተበደለ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ ከተማይቱን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የከተማይቱ ነዋሪ ለሚገፋው አስቸጋሪ ህይወት ተጠያቂ ነው፡፡ ድርጅቱ አገሪቱን የመምራት ብቃት እንደሌለውም የወቅቱ የአዲስ አበባ ሁኔታ አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከተማይቱ ነዋሪ እየገፋው የሚገኘውን ፈታኝ ህይወት በማጥናት ህዝቡን በተለይም የከተማውን እና የዙሪያ አካባቢዋን ነዋሪ በማደራጀት በቅርቡ ‹‹የእሪታ ቀን›› በማለት ሰይሞ በ1ወር ጊዜ ውስጥ ሠላማዊ ሠልፍ ለማድረግ የወሰንን መሆኑን እየገለፅን የአዲስ አበባና አካባቢዋ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፉ በሚደረግበት ቀን በነቂስ በመውጣት በስርዓቱ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ለመግለፅ እንዲዘጋጁ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው
መጋቢት 11 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ቤተክርስቲያን መምህር ግርማን ፎርጂድ ደብዳቤ በማሰራጨት ወነጀለች

$
0
0

Memeher Girma
(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን “መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ” በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡ “መምህር ግርማ ወንድሙ ከፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል” በሚል መምህር ግርማ እያሰራጩት ያለው ደብዳቤ ከቤተክርስቲያኒቱ ጽህፈት ቤት ተፈርሞ ያልወጣ የማጭበርበር ደብዳቤ ነው ሲል በአባ ገርማ (ሊቀጳጳስ/ዶ/ር) የብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርል ልዩ ጽህፈት ቤት የውጭ ግኙነት ሃላፊ ስም መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ተገልጿል።

ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም መምህር ግርማ የበተኑትንና በመላው ዓለም ከፓትርያርኩ ተዘዋውሬ ሃብተ ፈውስን እንድሰጥ ተፈቅዶልኛል የሚለውን ደብዳቤ ማስተናገዷ የሚያወስ ሲሆን አሁን ደግሞ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ የፓትሪያርኩ ልዩ ጽህፈት ቤት የወጣውን ደብዳቤ በማስተናገድ ፍርዱን ለአንባቢ ትተዋለች።

ቀጥሎም ፎርጂዱን ደብዳቤ እንዳትቀበሉት ሲል የወጣውን እና መምህር ግርማ ያሰራጩት የተባለውን ደብዳቤ በተከታታይ ለግንዛቤ አቅርበናቸዋል።

ዘ-ሐበሻ መምህር ግርማን በዚህ ህገወጥ የሆነ ደብዳቤ አሰራጭተዋል በሚል በቀረበባቸው ውንጅላ ዙሪያ ለማነጋገር ያደረገችው ሙከራ ባይሳካም እንዳገኘናቸው ሃሳባቸውን ለማቅረብ እንሞክራለን። ሆኖም ግን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች መምህር ግርማ ነሐሴ 25/2005 ዓ.ም ደብዳቤ ተጽፎልኛል ብለው ደብዳቤውን ከበተኑት ከ7 ወር በኋላ ቤተክርስቲያን ጉዳዩን ማስተባበሏ ከበስተጀርባው አንድ ጉዳይ ሊኖር እንደሚችል ይናገራሉ።

የመምህር ግርማ ደብዳቤ ፎርጂድ ነው አትቀበሉት ሲል የተጻፈው ደብዳቤ
memeher girma holy sionod

መምህር ግርማ በአቡነ ማቲያስ ሃብተ ፈውስን እንድሰጥ ተፈቅዶልኝ ደብዳቤ ተጽፎልኛል ሲሉ የበተኑት ደብዳቤ፦

Memher Girma

Memher Girma


ጋዜጠኞች ላይ ያለ ማስረጃ የሚሰነዘሩ ውንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲቆሙ እንጠይቃለን!

$
0
0

ከኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) የተሰጠ መግለጫ

ማህበራችን ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዶ የምዝገባ ሰርተፊኬት ለማግኘት የጀመረው እንቅስቀሴ በቅርቡ ከመንግስት አወንታዊ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ በማድረግ የተቋቋመለትን አላማ ለማሳካት እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም ከማስጠበቅና የመናገር ነፃነትን ከማበረታታት ባለፈም ከአህጉራችን አፍሪቃ ጋዜጠኞች ጋር በመተባበር የመላው አፍሪቃ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም የሚያስጠብቅና የመናገር ነፃነትን የሚያበረታታ አህጉራዊ ተቋም ለመመስረት ተነሳሽነትን ወስዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ በቅርቡም የምስራቅ አፍሪቃ ጋዜጠኞችን በማስተባበር አህጉር አቀፍ እንቅስቃሴያችንን ለማስጀመር ዝግጅት እያደረግን ነው፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተግባር ጋዜጠኛውን ሳይወክሉ የጋዜጠኛውን ስም የያዙት የኢጋማ፣ የኢነጋማና የኢብጋህ አመራሮች ነን የሚሉት ግለሰቦች በመቀናጀት በየሚዲያው እየቀረቡ ጋዜጠኞችንና የሚዲያ ተቋማትን ለማሸማቀቅ ያለመ ውንጀላና አሉባልታ የመንዛት ዘመቻ ጀምረዋል፡፡ ግለሰቦቹ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ቀርበው በጋዜጠኞች ላይ ከሽብር ፈጠራ እስከ ሀገር ማተራመስ የደረሰ የውንጀላ መዓት ቢደረድሩም አንዳችም ማስረጃ አላቀረቡም፡፡

ለምሳሌ የካቲት 22 ቀን 2006 ዓ.ም በታተመው አዲስ አድማስ ጋዜጣ (ቅጽ13 ቁጥር 737) ላይ ስማቸውን ደብቀው ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ጋዜጠኞች ሀገር ለማተራመስና ሽብር ለመፍጠር እየተዘጋጁ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ “ምን ማስረጃ አላችሁ” ለሚለው የጋዜጠኛዋ ጥያቄ የመለሱት “እኛ እና እነሱ እንተዋወቃለን፡፡” የሚል አስገራሚ መልስ ነው፡፡ ይህ መሰረተ ቢስ ውንጀላ ጋዜጠኞችን ለማሸማቀቅ የተወረወረ በመሆኑ የኢጋማ፣ የኢነጋማና የኢብጋህ አመራሮች ነን የሚሉት ግለሰቦች ጋዜጠኞችን እና የሚዲያ ተቋማትን ያለ ማስረጃ መወንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲያቆሙ ይጠይቀል፡፡

በመቀጠልም በሪፖርተር ጋዜጣ (የዕሁድ እትም ቅፅ 19 ቁጥር 1446) የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም “ኢጋማ በምስረታ ላይ ያለውን የጋዜጠኞች መድረክ አስጠነቀቀ” የሚል ዜና ተመልክተናል፡፡ ሆኖም በጋዜጠኞች ስም ተሰባስበው ጋዜጠኛውን የሚጠቅም አንዳች እንቅስቃሴ ሳያደርጉ ከመተኛታቸው ብዛት አልጋቸው ለረገበ ማህበራት ማስጠንቀቂያ ምላሽ በመስጠት ጊዜ በመሆኑም ምለሻችን በዝምታ መስራት ነው፡፡

የግለሰቦቹ የውንጀላ ንግግር የሚያስረዳው ከህግ፣ ከሞራል እና ከሙያዊ ስነምግባርም በላይ ራሳቸውን ለመሾም የሚፍጨረጨሩ መሆኑን ነው፡፡ ግለሰቦቹ በተለያዩ ጊዜያት መንግስት የፕሬስ ተቋማት ላይና ጋዜጠኞች ላይ የወሰዳቸውን ኢ-ህገመንግስታዊ እርምጃዎች እንደ ጋዜጠኛ ማህበር መሪ ከመኮነን ይልቅ የመንግስትን እርምጃ ሲያወድሱ ተስተውለዋል፡፡ በተጨማሪም በእስር ላይ ሆነው ህክምና በመከልከላቸው ለከፋ ስቃይ ስለተዳረጉ ጋዜጠኞችም ትንፍሽ ሲሉ አልታየም፡፡

እነዚህ የጋዜጠኛ ማህበራት መሪዎች ነን ያሉት ግለሰቦች እንደማህበር መሪ ሳይሆን እንደ ስለላ ተቋም ጋዜጠኞች እና አንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ሃገር ለማተራመስና የሽብር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው በይፋ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም

1ኛ. የሶስቱ ማህበራት መሪዎች አለን የሚሉትን መረጃ ለመንግስት በአፋጣኝ ሳይሰጡ መቆየታቸው በሀገራችን ህግ መሰረት ሊጠየቁው እንደሚገባ እንዲሁም

2ኛ. የሶስቱ ማህበራት መሪዎች በጋዜጠኞች እየተቀነባበረ ነው ካሉት የሽብርና ሀገር የማተራመስ እንቅስቃሴ ጀርባ እንዳሉ የጠቀሷቸውን ኤምባሲዎች በግልፅ ጠቅሰው ለመንግስት እና ለህዝብ እንዲያስታውቁ እንጠይቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ)

መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም

በኑሮ ውድነቱ እየተባባሰ መምጣት ኢሕአዲግ እና ሕዝቡ ይበልጥኑ ሆድና ጀርባ ሆነዋል

$
0
0

ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ

የኢህአዲግ ወያኔ መንግስት የስልጣን ወንበር በትሩን በሀይል ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የአኖኖር ሁኔታ ከእለት ወደ እለት እያሽቆለቆለ እና እየወረደ በመምጣቱ ሕዝቡ ከምቼውም ጊዜ በበለጠ በአሁኑ ወቅት ኑሮን መቋቋም በማይችልበት አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የኑሮ ውድነት ተቋቁሞ መኖር ከባድ ፈተና እየሆነባቸው እንደሆነ የችግሩ ሰለባና ተጠቂ የሆኑት ሰዎች በየጊዜው ከሚያሰሙት ሮሮና ጩኸት መረዳት ይቻላል::ይህንንም እየተባባሰ እና እየጨመረ የመጣውን የኑሮ ውድነት ተከትሎ የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ስራ አስፈፃሚ የተቃውሞ ሰልፍ ሊጠራ እንደሆነ ታውቋል:: የአንድነት ፓርቲ ሊጠራ ባሰበውና በታቀደው ሰላማዊ ሰልፉም ላይ በስርዓቱ እና በኑሮ ውድነቱ የተማረሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት በምሬት የታመቀ የብሶት ድምጻቸውን በወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ላይ እንደሚያሰሙ ይጠበቃል:: በአሁኑ ወቅት ጥቂት የስርአቱ ደጋፊዎች እና የወያኔ ካድሬዎች ካልሆኑ በስተቀር በኑሮ ውድነቱን የተነሳ ተጎጂ ያልሆነና ሕዝቡ ኑሮን መቋቋም በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ በመገኘቱ ስርዓቱን የማያማርር የህብረተሰብ ክፍል የለም ብል ማጋነን አይሆንብኝም ::

hrr2የወያኔ መንግስት የሚያራምደው ፖሊሲ የመላው ኢትዮጵያን ሕዝቡ ፍላጎት እና ጥቅም ማዕከል ያላደረገ ሲሆን የተወሰኑን የህብረተሰብ ክፍሎችን ብቻ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል :: መላውን የኢትዮያ ህዝብ እና ክልል ተጠቃሚ ያላደረገው የመንግስት የልማት ስትራቴጂ ፖሊሲ እና በመላው ሀገሪቱ ላይ በስፋት ተንሰራፍቶ ያለው ሙሰኝነት ከእለት ወደ እለት የሕዝቡ የአኖኖር ሁኔታ እያሽቆለቆለ እና እየወረደ እንዲመጣ ካደረጉት ምክንያቶች ውስጥ ተጠቃሽ ሲሆኑ ለኑሮ ውድነቱ ግንባር ቀደም ተጠያቂው መሆን ያለበት ሀገሪቱን እየመራው እና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት በፍጥነት እያሳደገ እንዳለ የሚያወራው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ነው:: በነገራችን ላይ የኢህአዲግ መንግስት በየጊዜው ስለ ሀገሪቷ ኢኮኖሚ እድገት የለመደውን የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ይለፍልፍ እንጂ ይህን በፍጥነት እያደገ ነው ብሎ ወያኔ የሚያወራለትን የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገት በተመለከተ የተባለው እድገት ከወረቀት ኣልፎ መሬት ላይ የሚታይ ነገር የለም የሚሉ ሰዎች በብዛት የሚገኙ ሲሆን ይህም ሀሳብ እኔንም ጨምሮ ብዙዎች የሚስማሙበት ጉዳይ ነው::

hr3ታስታውሱ እንደሆነ የወያኔ ቁንጮ የነበረው ሟቹ የቀደሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት በአሥር አመት ዉስጥ «ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ትችላለች። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በቀን ሶስቴ እንዲመገብ እናደርጋለን» ብለው ነበር ነገር ግን ይህ የአቶ መለስ ዜናዊ ንግግር የውሃ ላይ ሽታ ሆኖ ቀረ :: በአንጻሩ አቶ መለስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በቀን ሶስቴ እንዲመገብ እናደርገዋለን ያሉለት ኢህአዲግ ኢትዮጵያን በብቸኝነት በሀይል መግዛት ከጀመረ ወደ 23 አመታት እየተጠጋ ሲሆን በእነዚህ አመታቶች ውስጥ ምንም የተለወጠ ነገር የለም:: የወያኔ መንግስት በተቆጣጠረው በመገናኛ ብዙሃን እንደሚለፈልፉት የኢትዮጵያ ኢኮነሚው ዕድገቱ በፍጥነት ሽቅብ እየገሰገሰ ሳይሆን ወደታች እያሽቆለቆለ ይገኛል:: ምናልባት የኢኮኖሚ እድገቱ በወረቀት ስሌት ላይ ኑሮ እጅግ መራራ ከመሆኑ የተነሳ የሰዉ የአኖኖር ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ዉስጥ ዉስጡን የሚያልቁት ወገኖቻችን ብዛት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነዉ።በአሁኑ ሰአት ሕዝቡን የውሃ እጦት፣ የመብራት እጦት፣ የኔት ዎርክ ችግር፣ የትራንስፖርት እንደሚፈልገው አለማግኛት በአጠቃላይ ችግሩ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ በከፍተኛ ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል:: በይበልጥ የአዲስ አበባን ነዋሪ ክፉኛ ምሪት ውስጥ አስገብቶታል::

በአዲስ አበባ ሕዝቡ ታክሲ ለመያዝ በወረፋ ላይ

በመላው አገሪቱ አዲስ አበባን ጨምሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው የውሃ፣የመብራትና የቴሌኮም አገልግሎት ጥራት መጓደልና የአገልግሎት መቋረጥ እንዲሁም በአገሪቷ እጅግ ከፍተኛ የሆነ የዉጭ ምንዛሪ እጥረት እየታየ ሲሆን በሀገሪቱ ላይ በደረሰው በኢኮኖሚ ችግር የተነሳ ሕዝቡ ያለውን የኑሮ ውድነት መቋቋም በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ በመገኘቱ ነገሮች እየከረሩ በማንኛውም ጊዜና ሰሀት ግባታዊ ሕዝባዊ አመጽ ሊነሳና ትልቅ ችግር ሊፈጠር እንደሚችል የሚሰጉ ብዙዎች ናቸዉ።

በአሁኑ ሰአት እንደሚታየው እና መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥን ይፈልጋል ህዝቡ ሀገሪቱን እየመራ ባለው የወያኔ መንግስት ለመመራት ፍቃደኛ አይደለም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሮሮ በማሰማት ላይ ይገኛል:: በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ውስጥ ከየቦታው የሚሰማው እና የሚታያው የሰበዓዊ መብት ረገጣው አፈናና ግድያው ከጊዜ ወደ ጊዜ ተባብሶ እየቀጠለ ባለበት ሁኔታ በየቀኑ እያሸቀበ የመጣው የኑሮው ውድነቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ጋር ሆድ እና ጀርባ ሆነው እንዲቀጥሉ እያደረጋቸው ሲሆን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ የሕዝቡ ንዴትና ቁጣ በከፍተኛ ሁኔታ በመፋፋም ላይ ይገኛል::

ከዚህም የተነሳ መንግስት በየቀበሌው፣በየመስሪያ ቤቱ በሚጠራቸው ማንኛውም ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ለመገኛት ሕዝቡ ፍቃደኛ እና ደስተኛ አይደለም:: ስለዚህም የሕዝቡ ከመንግስት ጋር ሆድና ጀርባ መሆን የወያኔን መንግስት ክፉኛ ጭንቀት ውስጥ የከተተው ጉዳይ ሲሆን በመሆኑም ለመጪው 2007 ለሚደረገው ምርጫ የሕዝቡ በመንግስት ላይ ያለው ጥላቻ እየጨመረ መምጣት እራሱን የቻለ አስተዋጽኦ ሊኖረው እንደሚችል በብዙዎች ዘንድ ይገመታል::

በአዲስ አበበ የውሃ ወረፋ

የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ባለስልጣኖች በሚቀጥለው አመት ምርጫ የሕዝቡን ድምጽ እንደማያገኙ በሚገባ ቢረዱትም ነገር ግን የለመዱትን የማጭበርበር እና የሌብነት ልምዳቸውን በመጠቀም ለቀጠይም አመታት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የበላይ በመሆን ሕዝብን እየጨቆኑና እየረገጡ ለመኖር የሚያስችላቸውን ስትራቲጂ በመንደፍ እነሱ እንደሚሉት የጀመሩትን የልማት ዕቅድ ለመተግበር ሳይሆን ኢትዮጵያን የማፈራረስና ኢትዮጵያውነትን የመጥፋት ዘመቻቸውን ለማስቀጠል የሚያረዳቸውን ማንኛውንም እርምጃ ሁሉ ከመውሰድ ወደ ኋላ አንደማይሉ የተረጋገጠ ነው::

እንደ እኔ አስተሳሰብ የወያኔ ኢሕአዲግ መንግስት በምንም ታአምር በምርጫ ተሸንፉ ስልጣኑን በቀላሉ ይለቃል ወይም ስልጣኑን ለተቃዋሚዎች ያጋራል የሚል እምነቱም የለኝም::በአሁኑ ሰአት እንደምናየው እንዲሁ በቀላሉ የኢሕአዲግ መንግስት ስልጣኑን ይለቃል ወይም ለተቃዋሚዎች ያጋራል ብሎ ማሰብ የዋህነትና የማይታሰብ ጉዳይ ቢሆንም ነገር ግን ወያኔና የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆድና ጀርባ እንደሆኑ ለብዙ ጊዜ እንደማይቀጥል በምሪት እና በህልእ የተሞላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጣ ገንፍሎ ወያኔ ዳግም እንዳያንሰራራ ወደ መቃብር ይወስደዋል ብዬ አምናለው:: ስለዚህ የወያኔ መሰሪ አካሂድ ተስፋ ሳያስቆርጠን የወያኔን መንግስት በተገኛው መንገድ ሁሉ በመታገል እና በመቃወም የኢትዮጵያን ሕዝብ ነጻነት ለማረጋገጥ ትግላችንን ማቀጣጣል ይጠበቅብናል::ኢትዮጵያ በቆራጥ ታጋይ ልጆቿ ከወያኔ አገዛዝ ነጻ ትወጣለች::

ድል ለሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

gezapower@gmail.com
Image
gezahegn abebe.jpg

ህወሓቶች በዓረናና በትግራይ ህዝብ የተቃውሞ መንፈስ ደንግጠዋል፤ “እኛ ካልተመረጥን የትግራይ ማንነት ይጠፋል”እያሉ ነው

$
0
0

አብርሃ ደስታ

አብርሃ ደስታ

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ እንደዘገበው፦

ህወሓቶች በዓረና እንቅስቃሴና በትግራይ ህዝብ የተቃውሞ መንፈስ በጣም ደንግጠዋል። የዓረና ተከታታይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ተከትሎ ህወሓትም ተከታታይ ህዝባዊ ኮንፈረንስ ለማድረግ ወስኗል፤ ጀምሯልም። የህዝብ ተወካዮች ተብለው የተመረጡ የየአከባቢያቸው ህዝብ እንዲሰበስቡ መመርያ ተሰጥቷል። ይቅርታ የህዝብ ተወካዮች ሳይሆኑ የፓርቲ ተወካዮች መባል አለባቸው፤ ምክንያቱም የተመረጡት በህዝብ ሳይሆን በህወሓት ነው። የሚያገለግሉትም ለህዝብ ሳይሆን ለህወሓት ነው። ምክንያቱም በህዝብ ተመርጠው ተብለው የህዝብ ችግር ከመናገር ይልቅ የህወሓት አጀንዳ ደግፈው የሚያጨበጭቡ ናቸው። እስካሁን የመረጠውን ህዝብ ችግር የተናገረ የህዝብ ተወካይ የህወሓት አባል አላገኘሁም። በህወሓት የፖለቲካ ፍልስፍና የተማእከለ ዴሞክራሲ መሰረት አንድ አባል ከፓርቲው አስተሳሰብ ወጥቶ የፓርቲው ብልሹ አሰራሮች ባደባብይ ወይ በፓርላማ ማጋለጥ አይችልም። ካጋለጠ ከፓርቲው ይባረራል። ለዚህም ነው የህዝብ ተወካዮች ተብለው ፓርላማ ይገቡና የፓርቲው ተወካዮች ሁነው የሚቀሩ።
Arena-Tigray-logo
የህዝብ ወይም የህወሓት ተወካዮች ህዝብ ሲሰበስቡ ፈተና እያጋጠማቸው ነው። የሽረ ተወካይ ህዝቡ ሰድቦ አባሯታል። ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ በዓድዋ ህዝብ ተሰድባለች። የዓድዋ ህዝብ ለቅዱሳን “እናንተ ቤተሰቦቻቹ ለመርዳት እንጂ መቼ ለህዝብ ደህንነት ሰርታቹ ታውቃላቹ?” የሚል አስተያየት ሰጥቷል። በመቐለም አዲሳለም ባሌማ ህዝብ (ይቅርታ በመቐለ ህዝብ ተብለው የተሰበሰቡ ካድሬዎች ነበሩ) ሰብስቦ እርዱን ማለቱ ታውቋል። የመቐለ ዉሃ በ2007 ዓም ፕሮጀክት ቀርፀን እንፈተዋለን፤ ብቻ እኛን ምረጡ ብሎ ተማፅኗል። የመቐለ ነጋዴዎች ሰብስቦ ችግሮቻቹ ለመፍታት ተዘጋጅተናል ብሎዋል።

አጠቃላይ የህወሓት ስትራተጂ ህዝብን ለመሸወድ ያለመ ሲሆን የሚያጠነጥነውም “ህወሓት ካልተመረጠ የትግራይ ማንነት ይጠፋል” የሚል ነው። “ጠላቶቻችን እየመጡ ናቸው፤ ከህወሓት ጎን ተሰለፉ! ጦርነት ሊከፈትና ልጆቻችሁ አደጋ ላይ ሊወድቁ ይችላሉ” እያሉ ይገኛሉ።
ግን የትግራይ ማንነት በህወሓት ህልውና የተንጠለጠለ አይደለም። እንኳን የህዝብ ማንነት የአንድ ግለሰብ ማንነትም ሊጠፋ አይችልም። ምክንያቱም የህዝብ ማንነት ቀርቶ የአንድ ሰው ማንነት ከጠፋ የሰውየው መብትና ነፃነት ተጥሷል ማለት ነው። መብቱ ወይ ነፃነቱ ከተጣሰ ደግሞ አዲስ የመጣ ስርዓት ልክ እንደ ህወሓት አምባገነናዊ ስርዓት ነው ማለት ነው። የህውሓትን ያህል አምባገነን ስርዓት ከመሰረትን ደግሞ ህወሓት አልተቀየረም ማለት ነው። ህወሓት ካልተቀየረ የፖለቲካ ለውጥ አልመጣም ማለት ነው። የፖለቲካ ለውጥ ካልመጣ ደግሞ ትግላችን ይቀጥላል (ለውጥ እስኪመጣ ድረስ)። ስለዚህ እኛ የምንታገለው ከህወሓት የተሻለ ስርዓት ለመመስረት እንጂ ህወሓትን በሌላ አምባገነን ስርዓት ለመተካት አይደለም። ስለዚህ ላረጋግጥላቹ የምፈልገው ነገር ቢኖር የማንም ህዝብ ወይ ግለሰብ ማንነት ይከበራል እንጂ አይጠፋም።

“ጠላቶቻችን እየመጡ ነው” የሚለው ዉንጀላ ግዜው ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ ነው። የህዝብ ጠላት ጨቋኝ ስርዓት ነው። ህዝብ ከጨቋኝ ስርዓት ዉጭ ሌላ ጠላት የለውም። ጨቋኝ ስርዓት የህዝብ ጠላት እስከሆነ ድረስ እንታገለዋለን። ጨቋኝ ስርዓት ምን ግዜም አንቀበልም። ጨቋኝ ስርዓት ስለማንቀበል ነው አሁን ህወሓትን የምንቃወመው። ስለዚህ ዓላማችን የስርዓት ለውጥ ማምጣት እስከሆነ ድረስ ለጨቋኞች ቦታ የለንም፤ ህወሓትም ሌሎችም። እኛ የምንቀበለው ዴሞክራሲያዊ የህዝብ መንግስት ብቻ ነው።

(ከዚህ ቀደም የአረናን ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይሳተፉ የተከለከሉ የሽሬ ነዋሪዎች - ፎቶ ከአብርሃ ደስታ) - ፎቶ ፋይል

(ከዚህ ቀደም የአረናን ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይሳተፉ የተከለከሉ የሽሬ ነዋሪዎች – ፎቶ ከአብርሃ ደስታ) – ፎቶ ፋይል


ህወሓቶች በዓረና አጀንዳዎች በመስጋታቸው ምክንያት የዓረና ሐሳቦችን ለመቀበል እየተገደዱ ነው። በቅርቡ በህዝብ ፊት እየቀረቡ የመሬት ይዞታ ጉዳይ በዓረና እየቀረበ ያለውን ሐሳብ እንደሚደግፉ እየገለፁ ነው። (የዓረና ሐሳብ እንደግፋለን እያሉ ሳይሆን የህዝብን ፍላጎት ለማሟላት እንሞክራለን በሚል ነው። የህዝቡ ፍላጎት ደግሞ የዓረና የመሬት ፖሊሲ ነው)። የዓሰብ ወደብም በሰለማዊ መንገድ ለማስመለስ እንሞክራለን በማለት እየተመፃደቁ ነው። ለነጋዴዎችም ግብር እንቀንሳለን በሚል ምክንያት ለመጀንጀን እየሞከሩ ነው።

አሁን ግራ ሲገባቸው ስራ የሌላቸው ወጣቶች ለውትድርና ለመመልመል እየሞከሩ ሲሆን ማንም ወጣት ፍቃደኛ ሊሆን አልቻለም። በወጣቶቹ ዉሳኔ የተደናገጡ ህወሓቶች የጎዳና ተዳዳሪ የነበሩ ህፃናት ልጆች አታለው (ስራ እንሰጣቸዋለን በሚል ምክንያት) ለዉትድርና መመልመላቸው ታውቋል። ለምሳሌ በመቐለ ከተማ የነበሩ ብዙ የጎዳና ተዳዳሪ ህፃናት ተወስደዋል (ማረጋገጥ ይቻላል፤ አሁን በመቐለ ከነበሩ ህፃናት አንድ የቀረ የለም)። ግን አብዛኞቹ ህፃናት ከ16 ዓመት በታች ናቸው። ከ16 ዓመት በታች ህፃናት ለውትድርና የሚመለምል የቸኛ ሕገወጥ መንግስት ኢህአዴግ መሆኑ አይቀርም። ምክንያቱም በማንኛውም ሕግ ከ16 ዓመት በታች ህፃናት ለውትድርና መመልመል ሕጋዊ ሊሆን አይችልም። ጉዳዩ የሚከታተለው ካገኘ በዓለም አቀፍ ሕግ ወንጀል ሊሆን ይችላል።

በዓዲግራት የፈፀሙብንን ድብደባ በጣም አክስሮባቸዋል። የትግራይ ህዝብ ሙሉበሙሉ እንዲጠላቸው ሁነዋል። እናም በጣም ሰግተዋል። በቅርቡ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሊጀምሩ ይችላሉ። በወታድሩም ቢሆን ህወሓቶች ድጋፍ የላቸውም።

(ሰበር ዜና) ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ከሀገር እንዳይወጣ በኢሚግሬሽን ታገተ

$
0
0

Yilkal Getnet
ሰማያዊ ፓርቲ እንዳስታወቀው በአሜሪካን ሀገር ስቴት ዲፓርትመንት የተዘጋጀለትን ወጣት የአፍሪካ መሪ የሚል ሽልማት ለመውሰድ ዛሬ ሌሊት ወደ አሜሪካ ያቀና የነበረው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በቦሌ አየር መንገድ ከተገኘ በኋላ ከሀገር መውጣት አትችልም በሚል ታግቶ ይገኛል፡፡ በረራው 4 ሰአት ላይ የነበረ ሲሆን እስካሁን እስከሌሊቱ 8 ሰኣት ድረስ ታግቶ ይገኛል፡፡

ዝርዝር መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን።

የዋሸው ማን ነው? –ለመምህር ግርማ ከቤተክርስቲያን የተጻፉላቸው 14 ደብዳቤዎችና ምስክር ወረቀቶች እጃችን ገቡ

$
0
0

girma wendimu
“ለምንድ ነው የምትገፉኝ?” – መምህር ግርማ

(ዘ-ሐበሻ) ዘ-ሐበሻ የመምህር ግርማ ወንድሙን ጉዳይ ተከታትላ በመዘግብ ላይ ትገኛለች። አንባቢዎቻችን እውነታውን እስኪጨብጡ ድረስ ዘገባዎችን ማቅረቧ የሚቀጥል ይሆናል። በትናንትናው የዜና እወጃችን ቤተክርቲያን በአቡነ ገሪማ አማካኝነት የተጻፈን ደብዳቤ በመጥቀስ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን “መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ” በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡” በሚል የተጻፈውን ደብዳቤዎች አቅርበን ነበር።

ቤተክርስቲያን መምህር ግርማን በፎርጂድ ደብዳቤ ማሰራጨት የሚወነጅል ደብዳቤ ቢወጣም ዘ-ሐበሻ ለመምህር ግርማ ከቤተክርስቲያን የተጻፉ 14 ደብዳቤዎችና የምስክር ወረቀቶች ደርሰዋታል። ይህም ፎርጂድ ደብዳቤ ጽፈዋል በሚል የወነጀላቸውን አካል ወይም መምህር ግርማ ህጋዊ ደብዳቤ ተሰጥቶኛል ብለው ያሰራጩትን ደብዳቤ ለተመለከተ ማን ነው የዋሸው ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ሊሆን ይችላል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ። ያንብቡ ና የዋሸው ማን ነው ለሚለው ምላሽ ይስጡ።

“አንድ ሙዚቀኛ የሙዚቃ ትምህርት ቤት አንድ ሰርተፊኬት ብቻ ካለው ተቀባይነትና የታዋቂነት ክብር ይሰጠዋል፤ የሥራ መስኩም ይወደዳል፣ ይፈቀራል። ማንም የሚቃወመውም የለም፤ በሁሉም ዘርፍ ተፈላጊ ተወዳጅ ተሸላሚ ነው። በክፉ መንፈስ ከተጠቁት ጋር ለምውለው ለእኔ ግን የተገላቢጦሽ ነው። በሺህ የሚቆጠሩ የጥሪ አገልግሎትና የምስጋና ሰርተፊኬት አለኝ። ዛሬ ይህ ሁሉ ውሸት ሆኖ የመንደር አስማተኛ፤ የሱዳን ጠንቋይና የማይታወቅ አጭበራባሪ መለያ ስሜ ሆነ፤ ግን ለምን? ከጥቁር ፀጉር እስከ ነጭ ሽበት ያገለገልኩባት ቤተክርስቲያን ትምህርትና ፈውስ የሚፈልገው ሕዝብ ሲበዛ የፈውሱ ሂደት ከሃገር ውስጥና ከውጭ ዓለም ነጮችን ጨምሮ ሲከናወን የቤተክርስቲያን የወር ባጀት እና የዓመት ገቢ በእጥፍ ሲያድግ ለአባቶች እና በየአገረ ስበከቱ ላሉ አባቶች ሕዝቡ የፈውስና የትምህርት ፍላጎት ጥያቄ ሲበዛ ለምንድ ነው አስማተኛና ጠንቋይ የተባልኩት? ከነ ሙሉ መረጃው በሚቀጥለው… “አጥርቶም አየ… ከሩቅም ሳይቀር ሁሉን ተመለከተ” (ማር.23) መቆሚያና ማብቂያ የለውም ፈተና… ግን ለምን? ለምንድን ነው የምትገፉኝ?”

- መልአከ መንከራት ግርማ ወንድሙ

ደብዳቤዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Viewing all 2784 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>