Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all 2784 articles
Browse latest View live

የመንግስቱ ኃይለማርያም አጃቢ “የሌ/ኮ መንግስቱ ያልተነገሩ ሚስጢሮች”የተሰኘ መጽሐፍ አሳትመው በተኑ

$
0
0

mengistu haile mariam(ዘ-ሐበሻ) ዙምባብዌ በስደት የሚገኙት የቀድሞው ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም በስማቸው የሚወጣው መጽሐፍ ቁጥር በ10ሮች የሚቆጠሩ ሲሆኑ እርሳቸው ግን አንድ መጽሐፍ ብቻ አውጥተዋል። “የመንግስቱ ትዝታዎች”። ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባና በመላው ኢትዮጵያ የፕሬዚዳንቱ የቀድሞ አጃቢ ያሳተመውና “የሌ/ኮ መንግስቱ ምስጢሮች” የተሰኘ መጽሐፍ መሰራጨቱን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታውቀዋል።
በቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሃይለማርያም የቤተመንግስትና የሥራ ህይወት ዙሪያ እንደተጻፈ የሚነገርለት ይኸው “የሌ/ኮ መንግስቱ ያልተነገሩ ሚስጥሮች” የተሰኘው መፅሀፍ የተጻፈው የቀድሞው ልዩ ኃይል አባል እና የፕሬዝዳንት መንግስቱ አጃቢ በነበሩት እሸቱ ወንድሙ ወልደስላሴ እንደሆነ ታውቋል። ይህ መጽሐፍ ባለ 120 ገፅ እንደሆነ የገለጹት የዘሐበሻ ዘጋቢዎች የመጽሐፉ ደራሲ ለ14 ዓመታት በልዩ ጥበቃነት መስራታቸውን አስታውቀዋል። እኚሁ የቀድሞው የመንግስቱ ኃይለማርያም አጃቢ ካሁን ቀደም “ህይወት በመንግስቱ ቤተመንግስት” በሚል ርዕስ ሁለት ቅፅ መጻሕፍትን ያሳተሙ መሆኑ ይታወሳል።


ቅዱስ ጊዮርጊስ በቱኒዚያው ክለብ 3 ለ 1 ተሸነፈ

$
0
0

St George
(ዘ-ሐበሻ) በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እየተካፈለ የሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በደጋፊው ፊት በቱኒዚያዊ ክለብ ሲ ኤስ ሰፋክሲን 3ለ1 ተሸነፈ። በውድድሩ በከቱኒዚያና ማሊ ክለቦች ጋር ተድልድሎ በመጫወት ላይ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬ ኦገስት 18፣ 2013 በምድቡ መሪ ሲ ኤስ ሰፋክሲን 3ለ1 በመሸነፍ ደጋፊውን አንገቱን አስደፍቷል።

ሲ ኤስ ሰፋክሲን በምድቡ ያደረጋቸውን ሶስት ጨዋታዎች በማሸነፍ 9 ነጥብ እየመራ የሚገኝ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ ስታዲ ማሊን አሸንፎና በኢቶልዲ ሳህልና ሲ ኤስ ሰፋክሲ ተሸንፎ በ3 ነጥብ ይዟል፡፡ በደጋፊው ፊት የቱኒዚያውን ሲ ኤስ ሰፋክሲን የገጠመው ጊዮርጊስ ጨዋታው ከባድ እንደሚሆንበት የስፖርት ተንታኞች ይናገራሉ።

የድምጻዊ ኢዮብ መኮንን ቃለ ምልልስ ቪድዮ –ለትውስታ

$
0
0

ይህን ቃለ ምልልስ ያደረገው የቀድሞው የማህደር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና አሳታሚ ወርቅአፈራው አሰፋ ነው። ስለኢዮብ ግንዛቤ ሊሰጣችሁ ይችላልና ይመልከቱት።

“የሚያንጽ ካልሆነ በስተቀር ኔጊቲቭ የሆነ ዘፈን መዝፈን አልፈልግም”

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር ሊፈቱ ይሆን?

$
0
0

እስር ቤት የምትገኘው ጋዜጠኛ ሒሩት ክፍሌ

እስር ቤት የምትገኘው ጋዜጠኛ ሒሩት ክፍሌ

ዘጋቢ ጋዜጠኛ ስለሺ ሐጎስ

በእነ ኤልያስ ክፍሌ መዝገብ በሽብርተኝነት ክስ ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ከሚገኙት አራቱ ኢትዮጵያውያን መሀከል ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌና አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሄር በ2004 ዓ.ም ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን ምላሽ ሳያገኙ ለረዥም ጊዜ መቆየታቸው ሲያነጋግር ሰንብቷል፡፡ በተለይ ሲውዲናውያኑ ጋዜጠኞች ከኢትዮጵያውያኑ ጋር በተመሳሳይ ወቅት ይቅርታ ጠይቀው አፋጣኝ ምላሽ ማግኘታቸውና በአንጻሩ የእነውብሸት ይቅርታ ከአመት በላይ መዘግየቱ ተገቢ አለመሆኑ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡

ከአንድ አመት በላይ ቆይታ በኋላ ሐምሌ 25 2005 ዓ.ም የይቅርታ ቦርድ ጽ/ቤት ማህተም አርፎበት ለወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ በተላከ ደብዳቤ የይቅርታ ጥያቄያቸው ለፕሬዝዳንቱ ቀርቦ ውድቅ መደረጉ ተገልጾላቸዋል፡፡ ወ/ሮ ሂሩት ከእነ ውብሸት ጋር ባንድ መዝገብ ተከሰው 19 አመት የተፈረደባቸው ሲሆን የይቅርታ ጥያቄውንም ያቀረቡት በተመሳሳይ ወቅት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ወደ ህትመት እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ለጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ለአቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር የደረሳቸው ደብዳቤ አለመኖሩን አረጋግጠናል፡፡

የወ/ሮ ሂሩት ይቅርታ በፕሬዝዳንቱ ውድቅ መደረጉን አስመልክቶ ልጃቸው ፍጹም መሰለ እናቱ ከተፈረደባቸው በኋላ ይግባኝ ከማለት ይልቅ ይቅርታ መጠየቅ የወሰኑበት ምክኒያት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በፓርላማ ቀርበው “እንኳን ሀገር ውስጥ ያሉት ውጪ ያሉትም ቢሆኑ ዛሬ ይቅርታ ከጠየቁ ከነገ ጀምሮ ነጻ ናቸው” የሚል ቃል መግባታቸው እንደሆነ ገልጾ ይግባኝ የምንልበት አማራጭም አልፎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከገቡት ቃል በተቃራኒ ይቅርታው ውድቅ ተደርጓል መባሉ እንዳሳዘነው ተናግሯል፡፡ ፍጹም አክሎም “ለሲውዲናውያን የተሰጠው ዕድል ለኢትዮጵያውያን ጨርሶ ይከለከላል የሚል ዕምነት ስለሌለን የይቅርታ ጥያቄውን በድጋሚ በሽማግሌዎች በኩል እናቀርባለን” ብሏል፡፡

የአቶ መለስ ዜናዊን ሙታመት አስመልክቶ በርካታ እስረኞችን ለመፍታት መንግስት በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ያረጋገጡት ምንጮቻችን ጋዜጠኛ ውብሸትና አቶ ዘሪሁን ደብዳቤ ያልደረሳቸው ከሚፈተቱት እስረኞች ዝርዝር ውስጥ ገብተው ሳይሆን እንደማይቀር ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡

ድምጻዊ ኢዮብ መኮንን አረፈ

$
0
0

eyob
(ዘ-ሐበሻ) ትናንት ለሕክምና ወደ ናይሮቢ አምርቶ የነበረው ድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ማረፉ ተዘገበ። ድምፃዊው ዘወትር እንደሚያደርገው ሁሉ በብስክሌት ሰውነቱን አፍታቶ ወደቤቱ ሲመለስ (የእህቱን ልጅ ት/ቤት አድርሶ ከተመለሰ በኋላ የቤቱን መጥሪያ እንደተጫነ መውደቁ) ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ምክንያት እንደሆነውና በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታልም በተደረገለት ህክምና ሊነቃ ያልቻለው ድምፃዊው በኢትዮጵያውያን መዋጮ ወደ ናይሮቢ ለህክምና ትናንት ከተጓዘ በኋላ በጤናው ላይ መሻሻል ታይቶበት እንደነበር ዘገባዎች ጠቁመው ዛሬ ሕይወቱ ልታልፍ መብቃቷን ገልጸዋል።

በጅጅጋ ከተማ ተወልዶ ያደገውና “አንድ ቃል” በተሰኘው የመጀመሪያ አልበሙ ተወዳጅነትንና እውቅናን ያተረፈው ድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ለሞት ያበቃው “ስትሮክ” ተብሎ የሚታወቀው በሽታ እንደሆነ ዘገባዎች ጠቁመዋል። ባለቤቱ ወ/ርፕ ወ/ሮ ቲና ተአረ ትናንት በአዲስ አበባ ታትሞ ለወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ጤንነቱ እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጻ የነበረ ቢሆንም ለተጨማሪ ህክምና ወደ ኬንያ አምርቶ ሕይወቱ አልፋለች።

ዘ-ሐበሻ ለአርቲስቱ አድናቂዎች እና ቤተሰቦች መጽናናትን ትመኛለች። በ38 ዓመቱ ያረፈውን አርቲስትም አምላክ ሕይወቱን በገነት እንዲያቆያት እንመኛለን።

ኢዮብን ለሞት ስላበቃው ስትሮክ በሽታ ማወቅ ከፈለጉ ይህን ይጫኑ

Hiber Radio: ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ትናንት በቨርጂኒያ ስለተደረገው ሃገራዊ የውይይት መድረክ ተናገረ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ፕሮግራም

<<...የኢትዮጵያ ወዴት እያመራች ነው ምንስ መውጫ ቀዳዳ አላት ፓርቲዎች ምን ያስባሉ ? ሲቪክ ተቋማት ምን ያስባሉ በሚል ለምክክር የተጠራ ስብሰባ ነው። ...አሁን ያለውን የሁሉንም ሀሳብ ሰብስበን ለሕዝብ የምናቀርብበት ነው። ሕዝብ እያንዳንደን ነገር ይከታተልና ከዚያ በሁዋላ አንድ አቋም ወይ አንድ የትግል ስትራቴጂ የሚነደፍበትን መድረክ እናዘጋጃለን ይሄ አይን ገላጭ ነው። የአቋም መግለጫ ባይጠበቅም...>>

ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ኢሳት የጠራውን በአገር ውስጥና በውጭ ያሉ አብዛኞቹን የዲሞክራሲ ሀይሎች ያሳተፈውን አገራዊ የውይይት መድረክ አስመልክቶ ከህብር ሬዲዮ ተጠይቆ ከሰጠው ማብራሪያ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<<...ቤሄ ሃይማኖታዊና ባህላዊ መልክ አለው።ለመሆኑ የቡሄ ሀይማኖታዊ መሰረት ምንድነው? የሆያሆዬው ጭፈራስ? ለመሆኑ ችቦ ማብራቱስ? ...ቡሄን አስመልክቶ ከብጹ አቡነ ዮሴፍ የኔቫዳ፣የአሪዞናና የዩታ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ም/ዋና ጸሐፊ ጋር ተወያይተናል። ሙሉውን ያዳምጡ

<<...በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣የሲቪክ እና የፖለቲካ ድርጅቶች በግብጽ የምንገኝ ኢትዮጵያውያን ያለብንን ችግር አስመልክተው ድምጻችንን ጄኔቭ ለሚገኘው ለዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር ጽ/ቤት ሊያሳውቁልን ይገባል...አሁን መንቀሳቀስም አልቻልንም ከፍተኛ ስጋት አለን ትልቅ መድልዎም በዩ.ኤን በኩል ይደረግብናል...>>

አቶ አስናቀ ሞላ በግብጽ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ማህበር የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ

<<...አስቸጋሪ የሚሆነው መንግስት በሙስና ላይ ዘመቻ ይዟል የሚለው አይደለም።በተግባር በሚታይበት ጊዜ ማን የሙስና ወንጀል ይመለከተዋል? ከፍተኛ የፓርቲውና የመንግስት ባለስልጣኖችን ይመለከታል አይመለከትም? ቤተሰቦቻቸውን ይመለከታል አይመለከትም? የጦር ሀይሉን አዛዦች ይመለከታል አይመለከትም? የሚለውን ማየት ይኖርብናል ለፖለቲካ ተብሎ የሚወሰደው እርምጃ ዝቅተኛ ሙሰኞቹን እንጂ ከፍተኞቹን አይነካም...>>

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረጉት ቃለ ምልልስ(ክፍል አንድ የተወሰደ.) ሙሉውን ያዳምጡት (ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን)

ዜናዎቻችን
- የሙስሊሙ ትግል አስተባባሪዎች የአገዛዙን <<ሼህ ኑሩን ማን ገደላቸው ድራማ አወገዙ

- በሼሁ ሞት የመንግስት እጅ እንዳለበት ጥርጣሬ ማጫሩን ገለጹ

- ቦሌን ከፈንጂ አደጋ አዳንነው ሲሉ የአገዛዙ የጸጥታ ሰዎች ገለጹ

- ሕዝቡ ኢቲቪ ድራማውን ጀመረ እያለ ነው

- በሳዑዲ አጎቴን ገድያለሁ ያለው ኢትዮጵያዊ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ

- ድምጻዊ እዮብ መኮንን አረፈ

- የግብጽ የሽግግር መንግስት የሙስሊም ወንድማማቾችን በሕግ ለማገድ ማሰቡን ገለጸ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

የቁጫ ሕዝብ ጥያቄ ሕጋዊ ምላሽ እንዲያገኝ ጥሪ እናቀርባለን!!! አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

$
0
0

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ (አንድት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ 

 

ፓርቲያችን አንድነት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆኑ ከሚታገልላቸውና ገዥው ፓርቲ ከወረቀት በዘለለ ያልተገበራቸው ሀገራዊ ቁምነገሮች ውስጥ ዜጎች ሳይሸማቀቁ በነፃነት ሃሳባቸውን የመግለፅ፣ በነጻነት የመደራጀት፣ በገዛ ሀገራቸው በነጻነት የመንቀሳቀስ፣ በፈለጉበት አከባቢ የመኖር፣ ሀሳባቸውንና አመለካከታቸውን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደገፍ፣ የመቃወም፣ ስለመብታቸው ሳይሸማቀቁ የመጠየቅ ወ.ዘ.ተ እና በአጠቃላይ የሕግ በላይነት እንዲሰፍን፣ የሰብዓዊና ፖለቲካዊ መብቶች በኢትዮጵያ እንዲከበሩ፤ ከዚህም ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የዜጎች ዋስትና እንዲረጋገጥ ማድረግ ናቸው፡፡

የቁጫ ሕዝብም ያነሷቸውን የማንነት፣ የቋንቋ፣ የባህልና የአስተዳደር ጥያቄዎችን በሠላማዊ መንገድ፣ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ለመንግሥት ቢያቀርቡም የተሰጣቸው ምላሽ እስርና ማስፈራሪያ መሆኑ ፓርቲያችንን አሳዝኖታል፡፡ ግንቦት 28 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በደቡብ ክልል ጋሞ ጎፋ ዞን በቁጫ ወረዳ የሆነውም የዜጎችን ህጋዊ ጥያቄ በሕገ-ወጥነት መቀልበስ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡ መገለጫውም በጅምላ የታሰሩትና እስር ላይ የሚገኙት ዜጎች ናቸው፡፡ ፓርቲያችን ጉዳዩን በቅርበት ተከታትሎ እንዳጣራው በርካቶች በጅምላ የታሰሩበት ምክንያት ልጆቻችን አፋቸውን በፈቱበት ቋንቋ ይማሩ፣ በስማችን ልንጠራ ይገባናል፣ የማንነት ጥያቄያችን ምላሽ ያግኝ፣ ፍህና መልካም አስተዳደር ይረጋገጥ፣ የልማት ጥያቄያችን ምላሽ ያግኝ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ስርዓቱ አረጋግጫቸዋለሁ ከሚላቸውና በቁጥጥር ስር ባደረጋቸው ሚዲያዎቹ የሚለፍፋቸው ቢሆኑም ለቁጫዎች የተሰጣቸው ምላሽ ሰብዓዊ ክብራቸውን መጣስና ማሰር ነው፡፡ ፓርቲያችን ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር አጥብቆ ይቃወማል፡፡

መንግስትም የመብትና ማንነት ጥያቄ ስላነሱ ያሰራቸውን በአስቸኳይ እንዲፈታ፤ ያነሷቸውን ጥያቄዎች አግባብ ባለው መንገድ በፍጥነት እንዲመልስ እንጠይቃለን፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ
ሐምሌ 24 ቀን 2005 ዓ.ም
አዲስ አባባUDJ

አቶ እውነቱ ብላታ የሥልጣን ዕድገት አገኙ

$
0
0

እውነቱ ብላታየኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዳይሬክተር የነበሩት አቶ እውነቱ ብላታ ደበላ ከያዙት ኃላፊነት ተነስተው ከፍ ወዳለው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው መሾማቸውን ሰንደቅ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ ዘገበ። እንደጋዜጣው ዘገባ አቶ እውነቱ የተሾሙት ቦታ አቶ በከር ሻሌ በአሁኑ ወቅት የገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት የያዙት ቦታ ሲሆን አቶ በከር ከዚህ ኃላፊነታቸው ተነስተው የአዳማ ከንቲባ ሆነው ከተሾሙ በኋላም ከዘጠኝ ወራት በላይ ቦታው ክፍት ሆኖ መቆየቱ ታውቋል።
ጋዜጣው ዘገባውን ቀጥሎ አቶ እውነቱ ብላታ ቀደም ሲል በኦሮሚያ ክልል የፍትህና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው የሰሩ ሲሆን በኋላም በፌዴራል ጉዳዮች ጽ/ቤት በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ ሲሰሩ ከቆዩ በኋላ በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን ተሹመው ለአንድ ዓመት ሲሰሩ ቆይተዋል ብሏል።


የድምፃዊ ኢዮብ መኮንን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይፈፀማል

$
0
0

በአሸናፊ ደምሴeyob
ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበው በሬጌ የሙዚቃ ስልት አጨዋወቱ በበርካቶች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈው ድምጻዊ እዮብ መኮንን ባሳለፍነው ቅዳሜ ለህክምና በሄደበት ኬኒያ ናይሮቢ ውስጥ በሚገኝ አጋ-ካሃን የተሰኘ ሆስፒታል ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ ትናንት ማምሻውን ወደሀገሩ የተመለሰው አስክሬኑ፤ ዛሬ ከቀኑ በ9ሰዓት በቅዱስ ስላሴ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቀብሩ እንደሚፈፀም ምንጮች አስታወቁ።
“እንደቃል” በተሰኘው ብቸኛና የመጀመሪያ አልበሙ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፎ የነበረው ድምፃዊ እዮብ፤ ባሳለፍነው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት የእህቱን ልጅ ትምህርት ቤት አስመዝግቦ ከተመለሰ በኋላ የግቢውን በር በማንኳኳት ላይ ሳለ ራሱን ስቶ መውደቁ የታወቀ ሲሆን፤ ህመሙም የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ (stroke) መሆኑ ታውቋል።
ከድንገተኛ አደጋው በኋላ ራሱን ስቷል። በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል የህክምና እርዳታውን ሲያገኝ የቆየው ድምፃዊው፤ ለተሻለ የህክምና እርዳታ ወደኬኒያ፤ ናይሮቢ አምቡላንስ ባለው የግል አውሮፕላን ቅዳሜ ምሽት ከሀገሩ የወጣው እዮብ ጤናውን ይዞ መመለስ ሳይችል ቀርቷል።
በኬኒያ የሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች የወጣቱን ድምጻዊ ህይወት ለመታደግ የተቻላቸውን የጣሩ ቢሆንም፤ ድምጻዊ እዮብ መኮንን ግን በተወለደ በ38 ዓመቱ እሁድ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት 3፡45 አካባቢ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
ድምጻዊው ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ሲሆን፤”እንደቃል” በተሰኘው ተወዳጅ አልበሙ በተጨማሪም በቅርቡ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ የሙዚቃ ስራውን ከ70 በመቶ በላይ አጠናቆ እንደነበር ምንጮች ይጠቁማሉ።

ሰማያዊ ፓርቲ በመብራት ኃይል አዳራሽና በምኒልክ ት/ቤት ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳላደርግ በቢሮክራሲያዊ መንገድ ተከለከልኩ አለ

$
0
0

semayawi parti
(ዘ-ሐበሻ) ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ዝምታን ሰብሮ አደባባይ በመውጣት ስም ያተረፈው ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኙት የመብራት ኃይል አዳራሽና በምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አዳራሾች ውስጥ ሕዝባዊ ስብሰባ ለማካሄድ ባቅድም በቢሮክራሲያዊ መንገድ ተከለከልኩ አለ።
ሰማያዊ ፓርቲ በፌስቡክ ገጹ “በቃል እንጂ በተግባር የማይታየው ህገ-መንግስታዊ መብት” በሚል በበተነው መረጃ ነሀሴ 19 ቀን 2ዐዐ5 ዓ/ም. በመብራት ሀይል አዳራሽ በሰማያዊ ፓርቲ ሊካሄድ ታስቦ የነበረው ሕዝባዊ ስብሰባ በተለመደው የመንግሥት ቢሮክራሲና አፈና ተደናቀፈ ብሏል፡፡ ይኸውም የአዳራሹ ባለቤት የሆነው የኢ.መ.ኃ.ባ. ስብሰባው በአስተዳደሩ እውቅና ያለው መሆኑን የሚገልፅ ደብዳቤ ሲጠይቅ የአ.አ. መስተዳድር ደግሞ አዳራሹን እንድትከራዩ ባለስልጣን መ/ቤቱ የፈቀደላችሁ መሆኑን የሚገልፅ ደብዳቤ አምጡ በሚል ውስጣዊ መነጋገር ባለበት ግልፅ ቢሮክራሲ ስብሰባው እንዳይደረግ መሰናክል ፈጥሯል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰማያዊ ፓርቲ ነሀሴ 26 ቀን እንዲካሄድ ኘሮግራም የያዘለትን ሁለተኛ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ዝግጅት በተጠናከረ ሁኔታ ቀጥሏል፡፡ በዛሬው እለትም ለአ.አ. መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባ ማሣወቂያ ክፍል የማሣወቂያ ደብዳቤውን ያስገባ ሲሆን ይህ ክፍል ግን የእውቅና ደብዳቤውን ለመቀበል ፈቃደኛ ባይሆንም እንደተለመደው ደብዳቤውን በብዙ ምስክሮች ፊት በማሳወቂያ ክፍል ኦፊሠሩ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠው መጥተዋል፡፡
በሌላ በኩል የፓርቲው የህግ ጉዳይ ኃላፊ ወጣት ይድነቃቸው ከበደ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፀው ፓርቲው በመጪው እሁድ በመብራት ኃይል አዳራሽና በምኒልክ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አዳራሽ ጥያቄ አቅርቦ የአዳራሾቹ ባለቤቶች ፓርቲው ስብሰባ ለማካሄድ ከአዲስ አበባ አስተዳደር የፈቃድ ደብዳቤ እንዲያመጣ ሲጠይቁ የአዲስ አበባ አስተዳደር በበኩሉ ለአዳራሽ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ አምጡ በማለቱ ቢሮክራሲያዊ በሆነ መንገድ አዳራሾቹን መከልከሉን ተናግረዋል።
“ወደ አዳራሾቹ ባለቤት ሄደን ክፍያ ልንፈፅም ስንል ፈቃድ አምጡ ይሉናል። ከአዲስ አበባ አስተዳደር ደግሞ ፈቃድ ስንጠይቅ የተዋዋላችሁበትን ደረሰኝ አምጡ በማለት አጉላልተውናል” ያለው ወጣት ይድነቃቸው በግል የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ የሆኑትን አቶ አባተ ስጦታውን ቢያናግሩም ፈቃዱ ሊሳካ አልቻለም ብሏል።
በተያያዘ ፓርቲው ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የእውቅና ደብዳቤ ማስገባቱንና ሰልፉን ሊያደምቁ የሚችሉ ልዩ ልዩ ቅድመ ዝግጅቶች እያካሄዱ መሆኑን ከወጣት ይድነቃቸው ገለፃ መረዳት ተችሏል።
በሌላ በኩል ፓርቲው ቀበና በሚገኘው ጽ/ቤቱ በየሳምንቱ እሁድ ምሁራንን እየጋበዘ የሚያደርገውን ውይይት በመቀጠል በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መምህር የሆኑትን ዶ/ር በቃሉ አጥናፉ ታዬን በመጋበዝ “የግጭት አፈታት በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በቀጣይ እሁድ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ ፓርቲው ለተለያዩ ሚድያዎች በላከው መግለጫ ላይ አስታውቋል። ጋዜጣው በዘገባው ማጠናቀቂያ ላይ እንዳለው ዶ/ር በቃሉ በአሁኑ ወቅት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር ሲሆኑ በሳይኮሎጂና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሁለት ማስተርስ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን በትምህርት (Education) የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በቋንቋና ስነልቦና የፒኤች ዲግሪ አላቸው። ከአስር ዓመት በላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በማስተማር ላይ ይገኛሉ።

ወ/ሮ ሃዲያ መሀመድ ከ18 ቀን እስር በኋላ በ10ሺህ ብር ዋስ ተለቀዋል

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር የሆኑት ወ/ሮ ሃዲያመሀመድ ከ18 ቀን እስር በኋላ በ10,000 ብር ዋስ ተለቀዋል፡፡ አንድት በወላይታ ሶዶ  ሐምሌ 28 ቀን 2005 ዓ.ም ያካሄደው ህዝባዊ ስብሰባ እንዲጨናገፍ የተለያዩ የውንብድና ድርጊቶችን ሲፈፅም የነበረው የዞኑ የዞኑ አስተዳደር ወ/ሮ ሃዲያ መሀመድን  “አንድነት ፓርቲ ሙስሊሙን ህብረተሰብ ለአመፅ የሚቀሰቅስ በራሪ ወረቀት እንድበትን ተልዕኮ ሰጥቶኛል” ብለው እንዲመሰክሩ ጫና ቢያደርግባቸውም ባለመስማማታቸው ለ18 ቀናት በእስር እንዲማቅቁ አድርጓቸዋል፡፡

*ፎቶዎቹ ወ/ሮ ሃዲያ መሀመድ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት የተነሱ ናቸው፡፡

1187226

1001722_1174670_

ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 54 (PDF)

የኢዮብ መኮንን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ

$
0
0

eyob mekonen 1

eyob mekonen 2(ዘ-ሐበሻ) በሬጌ የሙዚቃ ስልት አጨዋወቱ በበርካቶች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈው ድምጻዊ እዮብ መኮንን ባሳለፍነው ቅዳሜ ለህክምና በሄደበት ኬኒያ ናይሮቢ ውስጥ በሚገኝ አጋ-ካሃን የተሰኘ ሆስፒታል ህይወቱ ማለፉን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ዛሬ ከቀኑ በ9ሰዓት በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቀብሩ በርከት ያሉ አድናቂዎቹ፣ የሙያ አጋሮቹ እና ቤተሰቦቹ በተገኙበት ተፈጽሟል።
“እንደቃል” በተሰኘው ብቸኛና የመጀመሪያ አልበሙ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፎ የነበረው ድምፃዊ እዮብ፤ ባሳለፍነው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት የእህቱን ልጅ ትምህርት ቤት አስመዝግቦ ከተመለሰ በኋላ የግቢውን በር በማንኳኳት ላይ ሳለ ራሱን ስቶ መውደቁና በዚህ የተነሳም በተገኘበት ስትሮክ ለሞት እንደበቃ በዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ ከታመመበት ጊዜ ጀምሮ ሲዘገብ ሰንብቷል። የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ (stroke) መሆኑ ታውቋል።
በተወለደ በ38 ዓመቱ እሁድ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት 3፡45 አካባቢ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ድምፃዊው ድምጻዊው ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነበር። በተጨማሪም በቅርቡ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ የሙዚቃ ስራውን ከ70 በመቶ በላይ አጠናቆ እንደነበር በተለያዩ ሚድያዎች የተዘገበ ሲሆን ለድምፃዊው መታሰቢያ ይሆን ዘንድ የተጠናቀቁትን ሙዚቃዎች ለማሳተም እቅድ እንዳለም ለዘ-ሐበሻ ከደረሰው መረጃ መረዳት ተችሏል።

የፍቼዉን የአንድነት ሰልፍ የሚያስተባብሩ ሁለት ኢትዮጵያዉያን ተደበደቡ

$
0
0

UDJ_ETHIOPIA-231x3001

 

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል መርህ የአንድነት ፓርቲ የሚያደርጋቸዉን፣  አገረ ሰፊ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎቹን በስፋት ገፍቶበታል። በኦሮሚያ በሚገኙ ሶስት ታላላቅ ከተሞች፣ አዳማ/ናዝሬት፣ ባሌ ሮቢና ፍቼ ሰላማዊ ሰልፎች እንደሚያደርግ፣  ለከተሞቹ ባለስልጣናት ያሳወቀ ሲሆን ፣ ቅስቀሳዎችንም በስፋት አያደረገ ነዉ።

 

ከጥቂት ሰዓታት በፊት ፣ ሰላማዊ ሰልፉን ለማስተባበር ወደ ፍቼ ያቀኑ ሁለት የአንድነት ፓርቲ አሰተባባሪዎች በአገዛዙ ካድሬዎች ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው ሲሆን፣ ከወዲሁ በሕገ መንግስቱ የተቀመጠዉን የዜጎች መብት ለመርገጥ ኢሕአዴግ እየሰራ መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ነዉ። የፓርቲዉ አመራር አባላት በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት መግለጫ እንደሚሰጡም ለማወቅ ችለናል።

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በደሴ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በአርባ ምንጭ፣ በጂንካ ሰላማዊ ሰልፎች በወላይታ ሶላማዊ ሰልፎችን፣ በአዲስ አበባና በወላይታ ሶዶ ደግሞ  የተሳኩ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ማድረጉ ይታወቃል።

ኢሕአፓ፣ እኔ እማውቀው፣

$
0
0

tower-in-the-sky-300x399(ባለፈው ሰሞን በሕይወት ተፈራ ተደርሶ ለንባብ ለበቀው፣ Tower In the Sky፣ ስለተባለው መጽሀፍ ውስጥ በተነሱ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ የቀረበ አስተያዬት፣)
ከሰላሙ ባላይ፣

ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ


ሕዝባዊ ስብሰባ በሲያትል በአካባቢው ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

በአዲስ አበባ ሕዝብን ሲቀሰቅሱ የነበሩ 5 ሰዎች ታሰሩ

$
0
0

“እኔ በአዋጅ ሳይሆን በትዕዛዝ ነው የምመራው፤ እሰር የሚል ትዕዛ ደርሶኝ አስሬያቸዋለሁ”

- የፖሊስ አዛዥ

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

(ዘ-ሐበሻ) የፊታችን እሁድ ነሐሴ 19 ቀን 2005 ዓ.ም (ኦገስት 25 ቀን 2013) በአዲስ አበባ በሚገኘው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት/መ.ኢ.አ.ድ/ ዋና ጽ/ቤት 33ቱ ፓርቲዎች ለጠሩት ህዝባዊ ውይይት የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የፓርቲዎቹ አባላት በህገወጥ መንገድ መታሰራቸውን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት አስታወቀ።

እንደ ዘገባው ከሆነ በቅስቀሳው ላይ ከነበሩት ወገኖች መካከል
1ኛ አቶ ደመላሽ፣
2ኛ. አቶ አብርሃም ፣
3ኛ. አቶ አታላይ በለው፣
4ኛ. አቶ እዮብዘር
5ኛ. አቶ መላኩ መሰለ
የተባሉት አባላት የቅስቀሳ መከናውን ከያዘው ሹፌርና ረዳት ጋር ታስረዋል፡፡
የፓርቲዎቹ አመራሮች አባሎቻቸው ወደታሰሩበት 1ኛ ፖሊስ ጣቢያ አቅንተው እስሩ ህጋዊ አለመሆኑን አዋጅ በመጥቀስ ቢያስረዱም በስፍራው የነበሩት የፖሊስ አዘዥም “እኔ በአዋጅ ሳይሆን በትዕዛዝ ነው የምመራው፤ እሰር የሚል ትዕዛ ደርሶኝ አስሬያቸዋለሁ” የሚል ምላሽ እንደሰጣቸው የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘገቧልል።

Breaking News: በሚኒሶታ ለአባይ ቦንድ ሽያጭ የተጠራው ስብሰባ ሳይጀመር ተበጠበጠ

$
0
0
ለተቃውሞ የተዘጋጀው ሕዝብ ከፖሊስ ጋር ሲነጋገር

ለተቃውሞ የተዘጋጀው ሕዝብ ከፖሊስ ጋር ሲነጋገር

በጠዋቱ ስብሰባው የሚደረግበትን ቦታ ሲጠብቁ የቆዩ ኢትዮጵያውያን

በጠዋቱ ስብሰባው የሚደረግበትን ቦታ ሲጠብቁ የቆዩ ኢትዮጵያውያን

ፖሊስ የአባይ ቦንድ ይሸጥበታል የተባለውን አዳራሽ ዘግቶ ስብሰባው እንደማይደረግ ከገለጸ በኋላ

ፖሊስ የአባይ ቦንድ ይሸጥበታል የተባለውን አዳራሽ ዘግቶ ስብሰባው እንደማይደረግ ከገለጸ በኋላ

(ዘ-ሐበሻ) በሴንት ፖል ሚኒሶታ የአባይን ቦንድ ለመሸጥ የኢትዮጵያ መንግስት አዳራሽ ተከራይቶ ለዛሬ ኦገስት 25 ቀን 2013 ዓ.ም ከ ቀኑ 2 ሰዓት እስከ ምሽቱ 8 ሰዓት ስብሰባ የጠራ ሲሆን ስብሰባው ከመጀመሩ አንድ ሰዓት በፊት ብጥብጥ ተነሳ።
በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን “ወያኔን አናምንም፤ 2 ሰዓት ብሎ ጠርቶ ስብሰውን ቀድሞ ሊጀምርና ሊነሳበት የታቀደውን ተቃውሞ ሊያከሽፍ ይችላል” በሚል ገና ከጠዋቱ ስብሰባው ይደረግበታል የተባለበት አዳራሽ በር ላይ ሲጠባበቁ ቆይተዋል። ልክ ስብሰባው ሊጀመር 1 ሰዓት ሲቀረው አንድ የስርዓቱ ደጋፊ የሆነ ሰው ካሜራ ይዞ “ከአባይ በፊት ሰብአዊ መብት ይከበር፤ የታሰሩት ይፈቱ” በሚል ለተቃውሞ የተሰባሰበውን ሕዝብ ሊቀርጽ ሲጠጋ ሕዝቡ “ሃገር ቤት ቪድዮ የቀረጻችሁት ሳያንስ እዚህ ልትቀርጹ ነው ወይ?” በሚል ልጁን ክፉኛ ከደበደቡት በኋላ ካሜራውን ሰባብረውበታል ያሉት የአይን እማኞች ወዲያውም ከ20 የሚበልጡ የሴንት ፖል ከተማ ፖሊስ መኪናዎች አካባቢውን በመክበብ ብጥብጡን አርግበውታል።
የሴንት ፖል ፖሊሶች መቃወም ትችላላችሁ፤ ሆኖም ግን ሰውን መደብደብ አግባብ አይደለም በሚል ለተቃውሞ የተዘጋጁትን ሲበትኑ ሕዝቡም “በአባይ ስም የሚደረገው ሕገወጥ ስብሰባ ነው” በሚል ለፖሊስ በማመልከታቸው ፖሊስም የቦንድ ሽያጩ አይደረግም ሲል ቃል ገብቷል።

ሕዝቡ ፖሊስ የቦንድ ሽያጩ ተሰርዟል ቢላቸውም ማረጋገጫ የለንም በሚል በአካባቢው የሚገኝ ሲሆን ብጥብጡን ተከትሎ በሴንት ፖል ፖሊስ ታስረው የነበሩት ኢትዮጵያውያን ወዲያው ተለቀዋል።

የኢሕአዴግ መንግስት በሚኒሶታ የአባይ ቀን በሚል ቦንድ ለመሸጥ የተከራየው የላኦ ኮምዩኒቲ አዳራሽ አድራሻ 320 University Ave W St Paul, MN 55103 ነው።

ዘ-ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎችን ከፎቶ ግራፍ እና ቪድዮዎች ጭምር ይዛ ትመለሳለች።

ይጠብቁን፤ ይመለሱና ይመልከቱን።

በሚኒሶታ ኢሕአዴግ ለቦንድ የተከራየውን አዳራሽ ፖሊስ ከቦታል

$
0
0

ፖሊስ የአባይ ቦንድ ይሸጥበታል የተባለውን አዳራሽ ዘግቶ እየጠበቀ

ፖሊስ የአባይ ቦንድ ይሸጥበታል የተባለውን አዳራሽ ዘግቶ እየጠበቀ

(ዘ-ሐበሻ) በሚኒሶታ የቦንድ ሽያጭ ለማከናወን ኢሕ አዴግ የጠራው ስብሰባ ሳይጀመር ብጥብጥ መነሳቱን ዘ-ሐበሻ ከጥቂት ሰዓታት በፊት መዘገቧ ይታወሳል። በስፍራው የሚገኘው የዘ-ሐበሻ ዘጋቢ እንዳለው ፖሊስ ቦንድ የሚሸጥበትን አዳራሽ ዘግቶ ማንም ሰው እንዳይገባ አድርጓል።
አካባቢው በከፍተኛ የፖሊስ ጥበቃ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፖሊስ ማንም ሰው ስብሰባ እንዳያደርግ ከልክሎ አዳራሹን እየጠበቀ ይገኛል። ኢሕ አዴግ በሚኒሶታ ቦንድ እሸጣለሁ በሚል የላኦ ኮምዩኒቲ አዳራሽን ከ2 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት ፒኤም የተከራየው ቢሆንም ከአባይ በፊት በኢትዮጵያ የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱ፤ የሰብአዊ መብት እንዲከበር፣ መንግስት በ እምነቶች ላይ ጣልቃ እንዳይገባ የሚጠይቁ ወገኖች ባደረሱት ተቃውሞ ፖሊስ አዳራሹን ዘግቶታል።
ኢሕ አዴግን ለመቃወም የመጡ ኢትዮጵያውያን አሁን ድረስ በአካባቢው የሚገኙ ሲሆን በኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ገንዘብ የተመደበላቸውና ወጪ ወጥቶባቸው ወደሚኒሶታ የመጡ ተወካዮች ከአካባቢው ተሰውረዋል።
(ኢትዮጵያውያኑ ከቦንድ መሸጫው አዳራሽ አካባቢ ተሰብስበው እየጠበቁ ነው)

(ኢትዮጵያውያኑ ከቦንድ መሸጫው አዳራሽ አካባቢ ተሰብስበው እየጠበቁ ነው)


ዘገባውን አሁንም እየተከታተልን እንዘግባለን ይጠብቁን።

የድምጽ ቃለምልልስ የሚኒሶታውን የአባይ ቦንድ ሽያጭ ካከሸፉት አክቲቪስቶች ጋር (Audio)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በሚኒሶታ የአባይ ቦንድን ለመሸጥ የተጠራው ስብሰባ ሳይጀመር በተነሳ ብጥብጥ ተቋርጦ የቦንድ ሽያጩ ሳይሳካ ቀርቷል። ለአዳራሽና ለአንዳንድ ወጪዎች በሺህዎች የሚቆጠር ዶላር ፈሶበት የተዘጋጀው ይህን ቦንድ ሽያጭ ያስተባበሩትን ወገኖች ዘ-ሐበሻ አግኝታ ለማነጋገር ያደረገችው ጥረት ባይሳካም፤ ካከሸፉት ኢትዮጵያውያን አክቲቪስቶች ጋር ዘ-ሐበሻ ቃል ተመላልሳለች። ግንዛቤ ያስጨብጣችኋልና ተከታተሉት፦

ቃለ ምልልስ ክፍል 1
[jwplayer mediaid="6706"]

ቃለ ምልልስ ክፍል 2
[jwplayer mediaid="6700"]

Viewing all 2784 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>