Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all 2784 articles
Browse latest View live

ግንቦት 7 የሕወሓት አስተዳደር በለቀቀው ‘አዲሱ’የአንዳርጋቸው ምስል ዙሪያ ምላሽ ሰጠ * “ሁላችንም አንዳርጋቸው እንሁን”

$
0
0

ግንቦት 7 ወቅታዊ አቋሙን በሚገልጽበት ርዕሰ አንቀጽ ባለፈው እሁድ የሕወሓት አስተዳደር ስለአንዳርጋቸው ጽጌ ስላስተላለፈው ዘገባ ምላሽ ሰጠ:: ሙሉ ር ዕሰ አንቀጹን ዘ-ሐበሻ እንደወረደ አስተናግዳዋለች::
Ginbot-7-Top-logo_4
ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን!!!

በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚገኘው የፌደራል ፓሊስ በእሁድ ታህሣሥ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ በግፍ እስር ላይ የሚገኘውን የግንቦት 7 ዋና ፀሐፊን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አቅርቦት ነበር። ይህ የ10 ደቂቃዎች ምስል ለቁጥር በሚያታክት ብዛት ተቆራርጦ የተቀጣጠለ በመሆኑ አቶ አንዳርጋቸው ምን ተጠይቆ ምን እንደመለሰ ማወቅ አይቻልም። ስለሆነም በንግግሩ ይዘት ላይ አስተያየት መስጠት ይናገረው አይናገረው በአልታወቀ ጉዳይ ማብራሪያ መስጠት ይሆናል። ስለዚህም፣ በንግግሩ ይዘት ላይ ጊዜ ከማጥፋት ህወሓት አንዳርጋቸው ጽጌን አሁን ማቅረብ ለምን እንደፈለገ መተንተን ይበልጥ ጠቀሜታ አለው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል።

አሁን ህወሓት በውስጥም በውጭም ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባበት ጊዜ ነው፤ በራሱ በድርጅቱ ውስጥም ሰላም የለም። ህወሓት የትግራይ ክልል ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሩ ስር እንደሆነ አድርጎ በመቁጠር መላዋን ኢትዮጵያን ለመዝረፍና ለማጥቃት እንደ መንደርደሪያ፤ በሌላኛው የኢትዮጵያ ክፍል ተቃውሞ ሲበዛበት ደግሞ እንደ መደበቂያ ዋሻ ሲጠቀምበት የነበረው ጊዜ አብቅቶ የትግራይ ሕዝብ በህወሓት ላይ ማመጹ በግልጽ በተግባር እየታየ ነው። በርካታ የትግራይ ልጆች በህወሓት ላይ ነፍጥ አንስተዋል፤ ከፊሎቹ ደግሞ በሰላማዊ ትግል ህወሓትን ማስወገድ ይቻላል ብለው በክልላቸውም ከክልላቸውም ውጭ ከህወሓት ጋር ፍልሚያ ገጥመዋል። ህወሓት መሠረቴ ነው ከሚለው የትግራይ ክልል ፈጽሞ ሊነቀል የሚችል መሆኑ ግልጽ ምልክቶች እየታዩ ነው። የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) ከትግራይና ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያገናኘው የአማርኛና የትግርኛ የቴሌቪዥን ፕሮግራም መጀመሩ የህወሓት ሹማምንትን ናላ ያዞረ እርምጃ ሆኗል።

የህወሓት ሌላው መተማመኛው የጦር ሠራዊቱ ነበር። ህወሓት፣ የኢትዮጵያን መከላከያ ጦር ሠራዊት ዘረኛ በሆነ መንገድ አደራጅቶ፤ ከፍተኛ አመራሩን በታማኝ አባላቱ ሞልቶ ተደላድሎ የተቀመጠ መስሎ ታይቶ ነበር። አሁን ግን ይህም ምስል አሳሳች እንደሆነ ግልጽ እየሆነ መጥቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት የኢትዮጵያ ጠላት የሆነውን ህወሓትን የማገልገል ፍላጎት የሌላቸው መሆኑን፤ እንዲያውም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን በመቆም የህወሓትን ውድቀት ለማፋጠን ያላቸውን ጉጉት በግልጽ እያሳዩ ነው። አየር ኃይል ውስጥ ያለው ተቃውሞ ገሀድ የወጣ ዜና ሆኗል። እንደ አየር ኃይል ገሀድ የወጣ ዜና አይሁን እንጂ በሌሎችም የሠራዊቱ ክንፎች ያለው አመጽ ተመሳሳይ የጡዘት ደረጃ ላይ ደርሷል።

andargacew Tsige ብአዴን እና ኦህዴድ ውስጥ ለአገራቸው ለኢትዮጵያ፣ እንወክለዋለን ለሚሉት ሕዝብ እና ለራሳቸው ክብር ያላቸው አባላት ብቅ ብቅ እያሉ ነው። ብአዴንንና ኦህዴድ እንደ ድሮ ፍጽም ታማኝ አገልጋዮች የመሆናቸው ጊዜ እያበቃ ነው። ደኢህዴንም ቢሆን ሙሉ በሙሉ የሚታመን አይደለም። ጊዜው ለህወሓት እጅግ የመክፋቱ ምልክት ደግሞ እራሱ ህወሓት ውስጥም ስምምነት የሌለ መሆኑ ነው። ህወሓት ይይዘው ይጨብጠው ጠፍቶታል።

ለዓመታት የዘለቀው የሙስሊም ወገኖቻችን ተቃውሞ እረፍት ነስቶት እያለ በባህርዳር የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ተቃውሞ ተጨመረበት። የአምቦውን ተቃውሞ አዳፈንኩ ሲል የጎንደር ተቀሰቀሰበት። ለጉራና ለሀብት ዘረፋ ሲል ያስጀመረው የአባይ ግድብ፣ ጥበቃው ብቻ እንኳን ፋታ የሚነሳ ሥራ ሆነበት። ጋምቤላ፣ አፋርና፣ ሶማሊ የግጭት ቀጠናዎች ከሆኑ ዓመታት አስቆጠሩ።

ከላይ የተዘረዘሩት ጉምጉምታዎች፣ ተቃውሞዎችና አመጾች ተቀናጅተው የመጡ ዕለት መድረሻ እንደሚያጣ የተገነዘበው ህወሓት ትኩረት ማስቀየሻ መፈለጉ ግድ ነበር። በግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እምነት በአሁኑ ሰዓት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ወደ ሚዲያ መቅረብ ምክንያቱ ይህ ነው። አንዳርጋቸውን ወደሚዲያ በማቅረብ ትኩረትን የማስቀየስ ስትራቴጂ!

ginbot 7የፊልሙ ማጀቢያዎች የነበሩት የሂውማን ራይትስ ዎች ሪፓርት፣ ስለእንግሊዝ ጋዜጣ የተነገረው፣ አሜሪካ ስለምትፈጽመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት የተዘከረው፣ ወዘተ … ወዘተ የሚያመላክቱት አንድ አቢይ ሀቅ አለ። ይህም ኢትዮጵያዊያን ፀሐይና ብርድ ሳይበግራቸው “እኔ አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ” እያሉ በእንግሊዝ መንግሥት የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት፣ በእንግሊዝ ኤምባሲዎች እና በአውሮፓ ኅብረት ሲያደርጓቸው የቆዩ ተቃውሞዎች ውጤታማ መሆናቸው ነው። በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የፈጠሩት ጫና ወያኔን ወደ ተከላካይነት አውርዶት “እኔ ንፁህ፣ አሜሪካ ርኩስ” እንዲል አድርጎታል። ወያኔ፣ ስለንፅህና ምስክርነትት ይሰጥልኛል ብሎ ተስፋ ያደረገው ደግሞ ራሱ ነፃነቱን ገፎ እስረኛው ያደረገው ሰው መሆኑ ጥረቱ እንደምን ውል አልባ እንደሆነበት ያሳያል። ንፅህናን ነፃ ባልሆነ ሰው ማስመስከር ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው? ይህ ክስተት፣ የኢትዮጵያዊያን ዘርፈ ብዙ ተቃውሞ የወያኔን የመከላከል አቅም ማዳከሙን በግልጽ ያሳያል። ይህ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ብሥራት ነው።

ከላይ የተዘረዘሩት ምክንያቶች ህወሓት አንዳርጋቸውን ወደሚዲያ ለማቅረብ ምክንያት ይሁኑ እንጂ የአንዳርጋቸው ለሶስተኛ ጊዜ በወያኔ ቴሌቬዥን መታየት በኢትዮጵያዊያን ላይ የፈጠረው ስሜት ህወሓት ከጠበቀው ፈጽሞ የተለየ ነው።

ኢትዮጵያዊያን አንዳርጋቸውን ሲያዩ የሚታያቸው ጽናት፣ አርበኝነትና አልበገር ባይነት ነው። የአንዳርጋቸው ምስል በታየ ቁጥር ኢትዮጵያዊያን ፀጉራቸው ይቆማል፤ ደማቸው ይፈላል። ወያኔዎች አንዳርጋቸውን የፈለጉትን ቢያናግሩት ችግር የለም። ለጊዜው በእጃቸው ውስጥ ስለሆነ ያላለውን ያለ ሊያስመስሉ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቃል። ወደፊት ደግሞ ሊናገር ያልፈለገውን ያናግሩት ይሆናል። ይህ ሁሉ የሚያመጣው ለውጥ የለም። አንዳርጋቸው ስለወያኔ ምንነትና ማንነት ማንም ሳያስገድደዉ በነፃነት አገር ዉስጥ በግልጽ ተናግሯል፣ አሁንም ወያኔዎች እራሳቸዉ በሰሩት ፊልም ዉስጥ እነሱ በማይገባቸው መንገድ ለኢትዮጵያን ሕዝብ ተናግሯል። እንኳንስ እነሱ እሱም ራሱ በማይገባው መንገድ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያዊያን ልብ ውስጥ ገብቷል። አንዳርጋቸውን ስናይ በህወሓት ፋሽስታዊ መዳፍ ውስጥ የወደቁብንን ጀግኖቻችንን ሁሉ ያስታውሰናል። በአስር ሺዎች ይቆጠራሉ። የአንዳርጋቸው ምስል ለግላጋ ወጣቶች፣ በሳል አዛውንት፣ ምርጥ ወንድሞችና እህቶች በወያኔ እስር ቤቶች ፍዳቸውን እያዩ መሆኑን ያስታውሰናል። ምስሉ ብቻውን ያናግረናል፣ ያነቃናል፣ ያነሳሳናል!!!

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አንዳርጋቸው ጽጌን፣ በርካታ ጀግኖቻችንን፣እራሳችንንና አገራችንን ከወያኔ እስር ነፃ ለማውጣት ክንዳችንን እናበርታ፤ ሁላችንም “እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነን” እንበል፤ ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!


የኢሳት ጋዜጠኞች መሳይ መኮንን እና ፋሲል የኔዓለም አስመራ ገቡ

$
0
0

የኢሳት ጋዜጠኞች መሳይ መኮንን እና ፋሲል የኔዓለም አስመራ ገቡ

(ዘ-ሐበሻ) ኢሳት በሰበር ዜና እንዳቀረበው ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ከዋሽንግተን ዲሲ እንዲሁም ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ከሆላንድ ኤርትራ ገቡ::

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም


ከኢሳት እንደተገኘው መረጃ ከሆነ ጋዜጠኞቹ አስመራ የገቡት ትናንት ሲሆን በኤርትራ ቆይታቸውም እዚያ ያለውን ሃይል እንደሚጎበኙና ዘገባም እንደሚያቀርቡ በተጨማሪም የኤርትራ ባለስልጣናትን እንደሚያነጋግሩ ይጠቁማል::

የቀድሞው የጀርመን ድምጽ ጋዜጠኛና የአሁኑ የኢሳት ራድዮ ከፍተኛ አዘጋጅ መሳይ መኮንን; እንዲሁም የቀድሞው የአዲስ ዜና ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የአሁኑ የኢሳት ቲቭ ኤዲተር ፋሲል የኔዓለም በአስመራ ለስንት ጊዜያት እንደሚቆዩ እስካሁን የተገኘ መረጃ የለም::

ከእናቷ ጋር አስፓልት እየተሻገረች መኪና የበላት የ19 ዓመቷ የነፋስ ላይ ሻማ የሜሪላንዷ ቤዛ አማረ

$
0
0

beza amare
ትናንት በዘ-ሐበሻ የዜና እወጃ ላይ ኢትዮጵያዊቷ በሜሪላንድ ከአውቶቡስ ወርዳ ወደ ቤቷ ስታመራ በመኪና ተገጭታ መሞቷን ዘግበን የሟቿን እህታችን ፎቶ ባለመለጠፋችን በርከት ያሉ አንባቢዎቻችን ፎቶዋን እንድናቀርብ ጠይቀውን ነበር::

የ19ኝ ዓመቷ ቤዛ ፎቶ ግራፍን አቅርበናል:: ቤዛ አማረ የተባለችው የ 19 ዓመት ወጣት የተገጨችው ሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ ሲሆን፣ ከአውቶቡስ ወርዳ ከ እናቷ ጋር ወደ ቤት ለመሄድ መንገድ እየተሻገሩ ሳለ ነበር። ፖሊስ እንደሚለው ሲሻገሩ የነበረው “ተሻገሩ” የሚለው የ እግረኞች ምልክት ሳይበራ ነበር። ገጪው የ 68 ዓመት ሰው ፣ ጥቂት ጉዳት ደርሶበት ታክሞ ከሃኪም ቤት ወጥቷል።

ለቤዛ የቀብር ስነ ስርዓት ማስፈጸሚያ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ በሜሪላንድ እየተደረገ ሲሆን ሁላችሁም እንድትሳተፉ ጥሪ ቀርቧል:: ነብስ ይማር::

ገንዘብ ለማዋጣት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ

ኢትዮጵያዊያን አንዳርጋቸውን ሲያዩ የሚታያቸው ጽናት፣ አርበኝነትና አልበገር ባይነት ነው። ሲል ግንቦት 7 ለፍትህ፣ ለዲሞክራሲና ለነፃነት ንቅናቄ ገለጸ።

$
0
0

g7-logoግንቦት 7 <<ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን!!!>> በሚል ርእስ ዛሬ ታህሳስ 29 ቀን ባስነበበው ርእሰ-አንቀጽ፤በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚገኘው የፌደራል ፖሊስ እሁድ እለት በቴሌቪዥን ፕሮግራሙ በግፍ እስር ላይ የሚገኘውን የግንቦት 7 ዋና ፀሐፊን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለ 10 ደቂቃ አቅርቦት እንደነበር በማውሳት፤ይህ የ10 ደቂቃዎች ምስል ለቁጥር በሚያታክት ሁኔታ ተቆራርጦ የተቀጣጠለ በመሆኑና አቶ አንዳርጋቸው በትክክል ምን እንዳለ የሚያስረዳ ባለመሆኑ፤ በይዘቱ ላይ አስተያዬት መስጠት አስፈላጊ እንዳልሆነ ገልጿል።
ከዚያ ይልቅ ህወሀት አንዳርጋቸውን ለምን አሁን ሊያቀርበው ፈለገ?የሚለውን ነጠብ ማዬት እንደሚያስፈልግ የጠቆመው ግንቦት 7፤ ህወሀት በውስጥም፣በውጪም በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባበት ወቅት በመሆኑ በተለይ ውስጣዊ ውጥረቱን ለማስተንፈስና አቅጣጫ ለማስቀየር አንዳርጋቸውን በተቆተራረጠ ምስልና ድምጽ አጅቦ ማቅረቡን ጠቅሷል። <<የህወሓት ሌላው መተማመኛው የጦር ሠራዊቱ ነበር።>>ያለው ግንቦት 7፤ ህወሓት፣ የኢትዮጵያን መከላከያ ጦር ሠራዊት ዘረኛ በሆነ መንገድ አደራጅና ከፍተኛ አመራሩን በታማኝ አባላቱ ሞልቶ ተደላድሎ የተቀመጠ መስሎ ቢቆይም አሁን ግን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት የኢትዮጵያ ጠላት የሆነውን ህወሓትን የማገልገል ፍላጎት እንደሌላቸውና ይልቁንም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን በመቆም የህወሓትን ውድቀት ለማፋጠን ያላቸውን ጉጉት በግልጽ እያሳዩ መሆናቸውን መረጃዎችን ዋቢ አድርጎ አብራርቷል።
እንደ አየር ኃይል ተቃውሞ ገሀድ የወጣ ዜና አይሁን እንጂ በሌሎችም የሠራዊቱ ክንፎች ያለው አመጽ ተመሳሳይ የጡዘት ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጸው ግንቦት 7፤ብአዴን እና ኦህዴድ ውስጥም ለአገራቸው ለኢትዮጵያ እና እንወክለዋለን ለሚሉት ሕዝብ እና ለራሳቸው ክብር ያላቸው አባላት ብቅ ብቅ እያሉ ነው ብሏል። እነኚህንና ሌሎችንም በመላ ሀገሪቱ የተቀጣጠሉትን የመብት ጥያቄዎችና አመጾች የተነተነው ግንቦት 7፤ <<ተቃውሞዎችና አመጾች ተቀናጅተው የመጡ ዕለት መድረሻ እንደሚያጣ የተገነዘበው ህወሓት ትኩረት ለማስቀየስ ሲል አቶ አንዳርጋቸውን እንዳቀረበው ገልጿል።
የፊልሙ ማጀቢያዎች የነበሩት የሂውማን ራይትስ ዎች ሪፓርት፣ ስለእንግሊዝ ጋዜጣ የተነገረው፣ አሜሪካ ስለምትፈጽመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት የተዘከረው ሁሉ የሚያመላክቱት አንድ አቢይ ሀቅ አለ።>>ያለው ንቅናቄው፤ ይህም ኢትዮጵያዊያን ፀሐይና ብርድ ሳይበግራቸው “እኔ አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ” እያሉ በእንግሊዝ መንግሥት የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት፣ በእንግሊዝ ኤምባሲዎች እና በአውሮፓ ኅብረት ሲያደርጓቸው የቆዩ ተቃውሞዎች ውጤታማ መሆናቸውን ነው ብሏል። <<ኢትዮጵያዊያን አንዳርጋቸውን ሲያዩ የሚታያቸው ጽናት፣ አርበኝነትና አልበገር ባይነት ነው። የአንዳርጋቸው ምስል በታየ ቁጥር ኢትዮጵያዊያን ፀጉራቸው ይቆማል፤ ደማቸው ይፈላል።>> ያለው ግንቦት 7፤ ወያኔዎች አንዳርጋቸውን ወደፊትም እንዲሁ ሊናገር ያልፈለገውን ቢያናግሩት የሚፈጠር ምንም ለውጥ እንደሌለ አስምሮበታል።
<< እንኳንስ እነሱ አሳሪዎቹ እሱም ራሱ በማይገባው መንገድ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያዊያን ልብ ውስጥ ገብቷል።>> ያለው ግንቦት 7፤<< አንዳርጋቸውን ስናይ በህወሓት ፋሽስታዊ መዳፍ ውስጥ የወደቁብንን በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ጀግኖቻችንን ሁሉ ያስታውሰናል። ያነቃናል፣ ያነሳሳናል!!!”ብሏል። ንቅናቄው በመጨረሻም _<<አንዳርጋቸው ጽጌን፣ በርካታ ጀግኖቻችንን፣እራሳችንንና አገራችንን ከወያኔ እስር ነፃ ለማውጣት ክንዳችንን እናበርታ፤ ሁላችንም “እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነን” እንበል፤ ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን >>ሲል ለ ኢት ጰያ ህዝብ ጥሪ አቅርቧል።

መታረም የሚገባዉ ማነዉ? ርዕዮት አለሙ ከቃሊቲ እስር ቤት

$
0
0

በግል የህትመት ዉጤቶች አማካኝነት በሀገሬ ዉስጥ የምመለከታቸዉን ችግሮች ለህዝብ ማቅረብና እንደዜጋም መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸዉን ሀሳቦች መጠቆም ከጀመርኩ አምስት አመታት አለፉ፡፡ የመጀመሪያ ፅሑፌን ያዘጋጀሁት ” “ስህተቶችን” ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶችና የስህተት ማረሚያ እርምጃዎች” በሚል ርዕስ እንደነበረ አስታዉሳለሁ፡፡ በዚህም ፅሑፍ የፕሬስ፣የፖለቲካፓርቲዎች ምዝገባና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተመለከቱ አዋጆች የወጡበት ምክንያትና እንደሀገር የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ለመዳሰስ ብሎም ኢህአዴግ ከስህተቶቹ እንዲታረም ለመምከር ሞክሬያለሁ፡፡
Ryotየኢህአዴግ ሰዎች በአንድ የገዢዉ ፓርቲ ልሳን በሆነ ድረገፅ አማካኝነት የማስጠንቀቂያ ይዘት ያለዉ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ከላይ ከጠቀስኩት የመጀመሪያ ፅሁፌ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በአዲስፕሬስ ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ተቀጥሬ መስራት ስጀምር ግን ሁኔታዉ እየባሰ መጣ፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም አዳማ ላይ ከተለያዩ ሚዲያዎች ለተዉጣጣን ጋዜጠኞች የሰጠዉን ስልጠና ከተካፈልኩ በኋል ከስልጠናዉ ጋር በተያያዘ ለህትመት ያበቃሁት ፅሁፍ ኢህአዴጎችን በእጅጉ አስቆጣቸዉ፡፡ በመሆኑም ወደቢሮአችን ተደዉሎ ከኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የተደወለ መሆኑ ከተገለፀ በኋላ ለጽሑፌ ምላሽ የላኩ በመሆኑ በፍጥነነት እንድናወጣዉ ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጠን፡፡ ምላሻቸዉን ለማዉጣት የእነሱ መደወልም ሆነ ትዕዛዝ አስፈላጊ አልነበረም፡፡ የዝግጅት ክፍላችን አንድ ጽሑፍ የቀረበበት አካል ምላሹን በዚያዉ በተፃፈበት የህትመት ዉጤት ላይ ማስነበብ እንደሚችል በህግ የተደነገገ መሆኑን ከማወቁም በላይ የትኛዉንም አይነት ሀሳብ ለማስተናገድ ክፍት ነበርና ምላሻቸዉን በጋዜጣችን ላይ ታተመ፡፡ በዚህ ብቻ ግን አልተገቱም፤ በወቅቱ የገዢዉ ፓርቲን ሀሳብ በማቀንቀን ይታወቁ የነበሩት እንደ ዳጉ ኢትዮጵያና ሰነድ ያሉ ጋዜጦች ሀሳቦቼን በሃሳብ መምታት ባለመቻላቸዉ ይሁን ባለመፈለጋቸዉ ተራ ዘለፋዎችን ያወርዱብኝ ጀመር፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የገዢዉ ፓርቲ ደህንነቶች ስልክ በመደወል፣ በዝግጅት ክፍላችን አድራሻ በስሜ ደብዳቤ በመላክና በአካልም በማግኘት ጭምር መንግስትን የሚተቹ ፅሑፎችን እንዳልፅፍ ሊያስፈራሩኝ ሞከሩ፡፡ “ማስፈራራት የሚቻለዉ የሚፈራ ሲኖር ነዉ” እንዲሉ ሙከራቸዉ ዋጋ አልነበረዉም፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪያ ፅሑፌን ለህትመት ከማብቃቴ በፊት ልከፍለዉ ስለምችለዉ መስዋዕትነት በሚገባ አስቤበታለሁ፡፡ የሀገሬን ጉዳይ በንቃት የምከታተል ዜጋ እንደመሆኔም ከገዢዉ ፓርቲ የተለየ ሀሳብ ያቀነቀኑ ሰዎች የደረሰባቸዉን በሚገባ አዉቃለሁ፡፡ በመሆኑም ከሁለት መጥፎ ምርጫዎች አንዱን ማለትም እነሱ የደረሰባቸዉን ግፍ እንዳይደርስብኝ የሀገሬን ጉዳይ በተመለከተ ፍዝ ተመልካች መሆንን ወይም በሙያዬ የምችለዉን አስተዋፅኦ አበርክቼ የሚመጣዉን መቀበል መምረጥ ነበረብኝ፡፡ ሁለተኛዉን የተሻለ መጥፎ ምርጫ ከመረጥኩ የሰነበትኩ በመሆኑም እየበረከቱ የመጡትን ማስፈራሪያዎች ከቁብ ሳልቆጥር የጋዜጠኝነት ስራዬን መቀጠል ቻልኩ፡፡ በዚሁ መሰረት ስራ ለመያዝ፣ የደረጃ እድገት ለማግኘትም ሆነ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከደህንነት ስጋት የፀዳ ኑሮ ለመኖር የኢህአዴግ አባል ካልሆነም ደጋፊ መሆን ከጊዜ ጊዜ ግድ እየሆነ መምጣቱን የሚያሳዩ፣ ገዢዉ ፓርቲ እንዳጎናፀፈን የሚገልፅልን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በተጨባጭ አለመኖሩን የሚሞግቱ፣ የኢህአዴግን እንደሀገር የማሰብ ችሎታ ወይም ፍቃደኝነት አናሳ መሆን የሚተቹና ሌሎችም መንግስት ቀናነት ቢኖረዉ ኖሮ ሊታረምበት የሚያስችሉትን በርካታ ፅሑፎች አቀረብኩ፡፡ አንድ ቀን ጧት ግን አምባገነኑ መንግስታችን ከጀመርኩት ጉዞ ገታኝ፡፡ ሰኔ10/2003 በወቅቱ እሰራባት በነበረችዉ ተወዳጇ ፍትህ ጋዜጣ ላይ የቀድሞዉን ጠቅላይ ሚኒስትር በተመለከተ ፅሑፍ ለህዝብ ማቅረቤን ተከትሎ ሰኔ14/2003 ዓ.ም ለእስር ተዳረግሁ፡፡
ማዕከላዊና ቃሊቲ ምንና ምን ናቸዉ?

ዉድ አንባብያን፤ ፊዘኛዉ መንግስታችን በሽብርተኝነት እንደሚጠረጥረኝ ገልፆ በእጆቼ ካቴና በማጥለቅ በቁጥጥር ስር አዋለኝ ካዋለኝ ከዚያ ቀን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለቁጥር የሚያታክቱ የመብት ጥሰቶችን እየፈፀመብኝ ይገኛል፡፡ ለአብነት ያህል እጅግ በጣም ጥቂቶቹን እነሆ!
ከህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ነዉ የሚባልለት ህገመንግስት በጥበቃ ስር ያሉ ሰዎች በጠበቆቻቸዉ የመጎብኘት መብት እንዳላቸዉ ቢገልፅም እኔና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ግን ይሄ መብታችን በማዕከላዊ አለቆች ተጥሷል፡፡ ጠበቃዬን ለማግኘት የተፈቀደልኝ ምርመራዉ ከተጠናቀቀና ቃል ከሰጠሁ በኋላ ወደቃሊቲ ለመዉረድ የአስርቀናት ዕድሜ ያህል ሲቀረኝ ነበር፡፡ በቤተሰብና በጓደኞቼ ለመጎብኘት የተፈቀደልኝም ሁለት ወር ከ3 ሳምንታት ክልከላ በኋላ ነበር፡፡ ከጠበቃዬ ጋር እንዳልገናኝ ተደርጎ የሚካሄደዉ ምርመራ የፃፍኳቸዉን ፅሑፎች ለምን እንደፃፍኩ፣ ከበስተኋላዬ ሆኖ የሚገፋኝ አካል ስለመኖር አለመኖሩና የመሳሰሉት ጥያቄዎች ላይ ያተኮረ ቢሆንም አልፎ አልፎ ደግሞ መልኩን ይቀይራል፡፡ አንዳንድ ቀን መርማሪዎቹ በማስተምርበት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በተካሄዱ ስብሰባዎች ላይ ያቀረብኳቸዉን ሀሳቦች እያነሱ ከመንግስት የደህንነት ሀይሎች የሚያመልጥ ምንም ነገር እንደሌለ በመግለፅ ቢጤ ያሰሙኝ እንደነበር ሳልጠቅስ ማለፍ አልፈልግም፡፡፡ እንዲህ አይነቱ ንግግራቸዉ አሰልቺዉን ምርመራ ዘና እልበት ዘንድ የሚረዳኝ የእፎይታ ጊዜ ሰጥቶኛል፡፡ በአደባባይ ስብሰባዎች ላይ የተናገርኩትንና ደህንነት ሊሰልለዉ የማያስፈልገዉን ግልፅ ነገር እንደ ትልቅ የደህንነቶች የስራ ዉጤት ተደርጎ ሲገለፅ ከመስማት በላይ ምን የሚያዝናና ነገር ይገኛል? የት/ቤት ርዕሰ መምህራኖች በሙሉ የኢህአዴግ አባል እንዲሆኑ የተደረገበት ምክንያት መንግስት እንደሚለዉ የትምህርት ፖሊሲዉን ለማስፈፀም ሳይሆን የመምህራንንና የተማሪዎችን የፖለቲካ አቋም ለማወቅና ይህንኑ ሪፖርት ለማድረግ መሆኑን የማይረዳ መምህር ይኖራል? ይህንን ለማድረግ ፍቃደኛ ያልሆኑ ርዕሰ መምህራኖች ሰበብ እየተፈለገላቸዉ ከቦታቸዉ እንዲነሱ ሲደረግስ ስንታዘብ አልኖርንም? “ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል” አለ ያገሬ ሰዉ! ሆዴ ባዶ እንዳይቀር ሁሉን መተንፈሴን ትቼ የጀመርኩትን የማዕከላዊ ምርመራ ጉዳይ ልቀጥል፡፡
የምርመራዉ ይዘት ከጥቂት ሳምንታት በኋላ መልኩን እየቀየረ መጣ፡፡ በሪፖርተርነት እሰራበት የነበረዉ የኢትዮጵያ ሪቪዉ ድረገፅ አዘጋጅ ኤልያስ ክፍሌ የሽብር ተልዕኮ እንደሰጠኝ በሀሰት እንድናገርና ተከሳሽነቴ ቀርቶ ምስክር ሆኜ እንድፈታ ለማድረግ የተለያዩ ጫናዎቸው ይደርሱብኝ ጀመር፡፡ ለአምስት ደቂቃ ያህል ጧትና ማታ ወደመፀዳጃ ቤት ለመሄድ ከሚከፍቱልኝ በስተቀር ለአስራሶስት ቀናት ያህል ብቻዬን አንድ መጥፎ ሽታ ያለዉ ክፍል ዉስጥ ተዘግቶብኝ ከረምኩ፡፡ በዚህ ወቅት ጉዳዬን የያዘዉ ዐቃቤህግ ማዕከላዊ በመምጣት እያስጠራኝ ሀሳቤን የማልለዉጥ ከሆነ እድሜ ልክ ወይም ሞት እንደሚያስፈርድብኝ ይዝትብኝ ነበር፡፡ ሀሰን ሽፋ በበኩሉ በሀሳባቸዉ የማልስማማ ከሆነ የያዘኝን የወጣት ጀብደኝነት ማስተንፈስ ለነሱ ከባድ ስራ አለመሆኑን ነግሮኛል፡፡ በኔ በኩል ደግሞ ከተጠረጠርኩበት ወንጀል ንፁህ መሆኔ እንጂ ኤልያስ ላይ በሀሰት መመስከሬ ሊያስፈታኝ እንደማይገባ ስለማምን ይህንኑ በተደጋጋሚ አስታዉቄ ተከሳሽ መሆንን መረጥኩ፡፡ ኢህአዴግ እስካለ ድረስ የተሻለዉን መጥፎ እየመረጡ መኖር ዕጣፋንታችን ከሆነ ቆየ አይደል?
ማዕከላዊ እያለሁ ከተፈፀሙብኝ የመብት ረገጣዎች ዉስጥ አንዱ የሆነዉ በአንድ ፖሊስ የተሰጠኝ ጥፊና ከግድግዳ ጋር ማጋጨት በተለይ ወንድ የፖለቲካ እስረኞች ከሚፈፀምባቸዉ ለዘላቂ የአካል ጉዳት የሚዳርግ ከባድ ድብደባ አንፃር ሳስተያየዉ የማዕከላዊ መርማሪዎች እንደሚሉት “ቁንጥጫ” ተብሎ ከመግለፅ የሚያልፍ ባለመሆኑ ብዙ ልልበት አልፈልግም፡፡ በወቅቱ የነበርነዉ ሴት እስረኞች ላይ ያን ያህል የከፋ አካላዊ ድብደባ አልተፈፀመም ማለት ግን የማዕከላዊ መርማሪዎች ለሴቶች ይሳሳሉ ማለት አይደለም፡፡ ለማሳያነት እስካሁን ድረስ ማዕከላዊ በተፈፀመባት ከባድ ድብደባ የተነሳ በህመም የምትሰቃየዋን የፖለቲካ እስረኛ እማዋይሽ አለሙን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አይ ማዕከላዊ! ማዕከላዊ ዘና ብለዉ የሚራመዱ ኩሩ የኢትዮጵያ ልጆች በገቡ ሳምንት በማይሞላ ጊዜ ዉስጥ በቃሬዛና በሰዎች ድጋፍ በሸክም ሲያሳልፉና የድረሱልኝ ዋይታ ሲያቀርቡ የሰማሁበት አሰቃቂ ቦታ ነዉ፡፡ ምስላቸዉ ከአይኔ ላይ፣ ጩኸታቸዉ ከጆሮዬ ተጣብቆ የሚኖረዉ እነዚህ ወገኖቼን እያሰብኩ መናደድ መቆጨት የዕለት ተዕለት የኑሮዬ አካል ሆኗል፡፡
የማዕከላዊዉን የመብት ረገጣ እዚህጋ ገታ ላድርገዉና በተለይ የፖለቲካ እስረኞችን ሰብአዊ መብት ከመጨፍለቅ አንፃር አምሳያዉ ወደ ሆነዉ የቃሊቲ እስር ቤት ልለፍ፡፡ ጳጉሜ3/2003 ዓ.ም ቃሊቲ እንደገባሁ በኋላ ላይ የጥበቃ ክፍል ሀላፊ እንደሆነች በተገነዘብኩት ሀላፊ አማካኝነት ጋዜጠኝነቴ ከታሰርኩ በኋላ የቀረ በመሆኑ ግቢዉ ዉስጥ በሚኖረኝ ቆይታ አርፌ መቀመጥ እንደሚኖርብኝ ተነገረኝ፡፡ አልጋ እስከሚለቀቅ ተብሎም እኔና በአንድ መዝገብ የተከሰስነዉ ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ ምንም እንኳን ሁለታችንም የሳይነስ በሽታ ያለብን ቢሆንም ሽንት ቤት አጠገብ መሬት ላይ ፍራሽ አንጥፈን እንድንተኛ ተደረገ፡፡ ዉድ አንባቢያን ስለቃሊቲ ስታስቡ ወደ አዕምሮአችሁ የሚመጡት ያማሩ ግንብ ቤቶችና የተዋቡ አልጋዎች ከሆኑ ኢቲቪ እንደሸወዳችሁ ልነግራችሁ እወዳለሁ፡፡ የፓስተር ዳንኤል ገ/ስላሴ ፕሪዝን ፌሎሽፕ የተባለ ድርጅት እንዳሰራቸዉ የሚናገሩት እነዚህ ያማሩ ግንብ ቤቶች ሁለት ክፍሎችና መፀዳጃ ቤት ብቻ ያሏቸዉ ሲሆኑ የተቀሩት በሴቶች ዞን ዉስጥ ያሉ ክፍሎች ከሁለት ያረጁ ግንብ ቤቶች በስተቀር በቆርቆሮ የተሰሩና እስረኞች በተጨናነቀ ሁኔታ የሚኖሩባቸዉ ናቸዉ፡፡ የቃሊቲ ምቾት አልባነት የሚሰማዉ አካልን ብቻ አይደለም፡፡ ቃሊቲ ከአካል በከፋ ሁኔታ ለነፍስና ለመንፈስ ይጎረብጣል፡፡ እንዴት ቢሉ እንዲህ እልዎታለሁ፡፡ የቃሊቲ የሴቶች ዞን ቤተመፃሕፍት ከጥቂት ወራት ጀምሮ በመፅሐፍቱ አይነትም ሆነ ቁጥር መሻሻልን ቢያሳይም እኔ ቃሊቲ ከገባሁ ጀምሮ እስከቅርብ ጊዜያት ድረስ ግን ከመኖር በማይቆጠር ደረጃ የሚገኝ ነበር፡፡ ይህንን ክፍተት ቤተሰብና ጓደኞቼ በሚያስገቡልኝ መፀሐፍት ለመሙላት ባስብም ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የሚመጡልኝ መፅሐፍት የቃሊቲን ሳንሱር እንደወደቁ ተገልፆ እኔጋ ሳይደርሱ ይመለሳሉ፡፡ ከነዚህ መፅሐፍት ዉስጥ አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የሚሳትማቸዉ የታሪክ መፅሐፍት ሳይቀር ይገኙበታል፡፡ ቃሊቲ ለመንፈስም አይመችም ያልኳችሁ በዚህ ብቻ አይደለም፡፡ በራሴ ወጪ ኢንድራ ጋኒዲ ናሽናል ኦፕን ዩኒቨርስቲ በርቀት ፖለቲካል ሳይንስ ለማጥናት ከብዙ ዉጣዉረድ በኋላ ተፈቅዶልኝ የተበዘገብኩ ቢሆንም የመማሪያ ሞጁሎቹን ለማስገባት ግን የቃሊቲ አለቆች ፍቃደኛ አልነበሩም፡፡ ከብዙ ደጅጥናት በኋላ ሞጁሎቹ ሲገቡ ደግሞ በትምህርቱ ዙሪያ ላነባቸዉ የሚገቡኝ አጋዥ መፅሐፍት ስለፖለቲካ የሚያወሩ በመሆናቸዉ በፍጹም ሊገቡ እንደማይችሉ የመፅሐፍት ገምጋሚዎቹ አረዱኝ፡፡ ይባስ ብሎ በዚያን ወቅት ከሌላዉ ጊዜ በተለየ ሁኔታ ምንም አይነት መፅሐፍት እንዳይገቡልኝ በመደረጉ ለጠቅላላ ዕዉቀት ያህል ሞጁሎቹን ማንበቤን ብቀጥልም ትምህርቱ ግን በዚህና በሌሎች ምክንያት ለማቋረጥ ተገደድኩ፡፡
በቃሊቲ የኔ ብቻ ሳይሆን ከእኔ ጋር የተቀራረቡ ወይም ደግሞ ሰላምታ ያቀረቡልኝ ሰዎች ሳይቀር መብታቸዉ ተጥሷል፡፡ ከሁለት አመታት በላይ የሚሆነዉን ጊዜ በርካታ እስረኞች በነበሩበት ክፍል ያሳለፍኩ ቢሆንም እኔን እንደሌላዉ እስረኛ ለመቅረብ የሞከሩ በሙሉ ስሜትን የሚጎዳ ወከባ፣ዘለፋና ለየት ያሉ ፍተሻዎችን አስተናግደዋል፡፡

በህክምና ጉዳይ የነበሩብኝን ችግሮች በተመለከተ ቤተሰቦቼ ደጋግመዉ የገለፁት መሠረታዊ ችግር በመሆኑ በዚህ ፅሑፍ ነካ አድርጌዉ ብቻ አልፋለሁ፡፡ ጡቴ ዉስጥ በበቀለዉ እጢ ምክንያት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የህክምና ክትትል በማደርግበት ወቅት በቀጠሮዬ ቀን ወደ ሆስፒታሉ ከምወሰድባቸዉ ይልቅ የማልወሰድባቸዉ ጊዜያት ይበዙ ነበር፡፡ የግራ ጡቴ ቀዶጥገና ከተደረገለት በኋላ በወቅቱ ክትትል ታደርግልኝ የነበረችዉ ዶክተር በሶስተኛ ቀን የቁስሉ ፕላስትር መቀየር እንዳለበትና በሳምንቱ ደግሞ ክሩ መዉጣት እንዳለበት ገለፀችልኝ፡፡ አብረዉኝ የሚሄዱት አጃቢ ፖሊሶች ከዶክተሬም ጋር ስነጋገር እዛዉ ነዉና የሚቆሙት እንዲህ አይነቱን ነገር ለማድረግ የሚችል ጤናጣቢያ ማረሚያቤቱ እንዳለዉ ተናገሩ፡፡ እኔም ቀጠሮ ቢሰጠኝ እንኳ በዚህ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ወደሆስፒታሉ ተመልሼ መሄድ አዳጋች መሆኑን ስለማዉቅ የተባሉት ነገሮች ቃሊቲ መፈፀማቸዉን አልጠላሁትም፡፡ በመሆኑም ለህክምና ክትትል የሶስት ወራት ቀጠሮ ተሰጠኝ፡፡ ክሩ መዉጣት ባለበት ቀን ስለጉዳዩ ለጥበቃ ክፍሉ አስታወቅኩ፡፡ እነሱም አሁን ደቡብ ሱዳን ከሚገኝዉ ጦር ጋር አብራ ከተጓዘች አንዲት የህወሐት ታጋይ የነበረች ነርስ ጋር አገናኙኝ፡፡ እሷም እዛዉ ጨርሼ መምጣት እንደነበረብኝና እዚህ ክሩን ማዉጣት እንደማይችሉ ነገረችኝ፡፡ የምታሳየኝ ጥላቻ በሷ እጅ የህክምና አገልግሎት ከማግኘት ቢቀር የሚሻል መሆኑን የሚጠቁም በመሆኑ ብዙም ልከራከራት አልፈለኩም፡፡ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ ሌሎች ሀላፊዎች ወደጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንዲወስዱኝ ብጠይቅም “ቀጠሮ የለሽም” በሚል ሰበብ ሳይወስዱብኝ ቀሩ፡፡ በአሁኑ ወቅት የቀኝ ጡቴም ተመሳሳይ እጢ ያለበት በመሆኑ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ምኒሊክ ሆስፒታል ቀዶጥገና አደርግ ዘንድ የላከኝ ቢሆንም (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በእድሳት ላይ በመሆኑ)እጅግ የከፋ ህመም ካልታመምኩ በቀር ቃሊቲ ሆኜ ቀዶጥገና ማድረጉን አልፈለኩም፡፡ በመሆኑም አልፎ አልፎ የሚሰማኝን ህመም በህመም ማስታገሻ መድሀኒቶች በማቃለል የቃሊቲን አስቀያሚ ቀኖች በመግፋት ላይ እገኛለሁ፡፡

ሌላዉ የቃሊቲ ቆይታዬን በተመለከተ ልጠቅሰዉ የምፈልገዉ ጉዳይ ከመንግስት አካላትና ከተለጣፊዎቻቸዉ ጋር ካለፍላጎቴ እንድንገናኝ እየተደረገ የሚፈፀምብኝ የሰብአዊ መብት ረገጣ ነዉ፡፡ ለምሳሌ ያህልአንዱን ብቻ ልጥቀስ፡፡ አምና መጋቢት ወር ዉስጥ አምባሳደር ጥሩነህ ዜናን ጨምሮ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን መምጣታቸዉን የገለፁ ሌሎች አስር ሰዎች ከአመት በፊት ወደገባሁበትና ከሌሎች ከአራት ሰዎች ጋር ብቻ ወደምኖርበት ክፍል መጡ፡፡ እኔም ኮሚሽኑ በተለይም ደግሞ አምባሳደሩ የሰብአዊ መብት አከባበርን አስመልክቶ የሚሰጧቸዉ ከእዉነት የራቁ መግለጫዎች የሚያሳዝኑኝ በመሆኑ ለመነጋገር ፍቃደኛ አለመሆኔን በማስታወቅ ከክፍሉ ወጥቼ በሩ ላይ ቆምኩ፡፡ ከሰዎች አንዱ የምኖርበትን ክፍልና አልጋዎቻችንን ፎቶ ሲያነሳ ተመለከትኩ፡፡ ገረመኝ፤ መሬት አንጥፌ ስተኛ፣በተደራራቢ አልጋ የላኛዉ ክፍል ላይ ከጡት ህመም ጋር እየታገልኩ ስተኛና በተፋፈገ ክፍል ዉስጥ ስኖር ለምን የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ፎቶ አላነሳም? ማረሚያ ቤቱ በጥሩ ሁኔታ እስረኞቹን የያዘ መሆኑን ማሳያ ለማድረግ እንደተፈለገ ገመትኩ፡፡ እዉነታዉ ግን ይቺ ያለሁባት በቆርቆሮ የተሰራች ክፍልና ጠባቧ ግቢ አምና መስከረም ላይ በጠያቂዎች የመጎብኘት መብቴ መጣሱን ተከትሎ በጥድፊያ የተዘጋጀች ማግለያ ቦታ መሆኗ ነዉ፡፡ ክፍሉን ብቻ ፎቶ አንስተዉ መሄዳቸዉ ያላረካቸዉ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰዎች በማግስቱ አራት ሆነዉ መጡ፡፡ ሁለቱ ወደግቢዉ ዉስጥ ሲገቡ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ በሩጋ ቆሙ፡፡ ግቢዉ ዉስጥ ከገቡት አንዱ ትላንት ለምን ላናግራቸዉ እንዳልፈለኩ ጠይቆኝ በድጋሚ ከነሱ ጋር መነጋገር ያልፈለኩበትን ምክንያት እያስረዳኋቸዉ እያለ የግቢዉ በር ክፍት ስለነበር ግቢዉ በርጋ ከቆሙት አንዱ ፎቶ ሊያነሳኝ ሲሞክር ለመመልከት ቻልኩ፡፡ ምስሌን አንስቶ ቢሆንና ስለኔ አንዳች አይነት ዉሽት ሲናገሩ ብሰማ ጉዳዩን በዝምታ እነደማላልፈዉ ነገርኩትና ወደቤት ዉስጥ ገብቼ በሩን ዘጋሁት፡፡

ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ከክፍሉ ወጥቼ ኢህአዴግ ማሰሩ ሳይበቃዉ ሰብአዊ መብትን ለማስከበር እንዳቋቋማቸዉ በሚናገረዉ ተለጣፊ ድርጅቶቹ ሳይቀር ሰብአዊ መብቴን ለምን እንደሚጥስ ከሀላፊዎቹ አንዷን በማስጠራት ጥያቄ አቀረብኩላት እሷም ሰዎቹ ካሜራ መያዛቸዉን እንደማታዉቅ ነገረችኝ፡፡ በ2005ዓ.ም ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች የህዝብ ግኑኝነት ክፍል እኔን ለማናገር እንደመጣ የገለፀልኝ ሰዉ ኮቱ ዉስጥ ደብቆ በያዘዉ ሪከርደር ድምፄን ለመቅረፅ ሲሞክር ደርሼበት ይህንን ማድረግ የሚችለዉ የግል ፕሬስም ተገኝቶ ንግግራችንን የሚቀርፅ ከሆነ ብቻ መሆኑን ነግሬዉ ነበር፡፡ ይሄንን ያልኩበት ምክንያት የግል ፕሬሱ ባልተገኘበት ለመንግስት ሚዲያዎች ብቻ አስተያየታቸዉን የሰጡ ግለሰቦች ሀሳባቸዉ ተቆርጦና ተቀጥሎ ለማለት ያልፈለጉት ይዘት ይዞ እንደሚቀርብ አዉቅ ስለነበር ነዉ፡፡ የተናገርኩትን ሙሉዉን ነገር ቀርፀዉ ሊያወጡልኝ የሚችሉ አካላት በሌሉበት ለሰዉዬዉ አስተያየቴን መስጠት ያለፈለኩትም ይኸዉ እንዳይደርስብኝ በመስጋት ነበር፡፡ አስገራሚዉ ነገር ይቺ የኮሚሽኑ ሰዎች ካሜራ መያዛቸዉን እንደማይታወቅ የገለፀችልኝ ሀላፊ ያኔም የሰዉየዉን የድምፅ ሪከርደር መያዝ በተመለከተ ላቀረብኩላት ጥያቄ የሰጠችኝ ተመሳሳይ መልስ ነበር፡፡
የቃሊቲ ጉድ ማብቂያ ስለሌለዉ አንድ የመጨረሻ ጉዳይ ላንሳና የፅሁፌ መነሻ ወደሆነዉ የአመክሮ ጉዳይ አልፋለሁ፡፡ ዉድ አንባቢያን በሀገሪቱ ዉስጥ ያሉ የትኞቹንም እስረኞች አያያዝ የተመለከቱ ህጎችን፣ አዋጆችን፣ ደንቦችንም ሆኑ መመሪያዎችን በጣሰ ሁኔታ ከወላጆቼ በቀር ጠበቃን ጨምሮ በሌላ በማንም ሰዉ የመጎብኘት መብቴን ከተነጠቅኩ አመት ከኣራት ወራት አልፎኛል፡፡ አዛዉንት እናትና አባቴም ከእርጅና፣ ህመምና ድካም ጋር እየታገሉ የቃሊቲን ፈታኝ መንገድ መዉጣትና መዉረዳቸዉን ቀጥለዋል፡፡
ነገረ አመክሮ

ያለፈዉ አመት ነሐሴ ስምንት ቀን ከሰአት በኋላ ወደ ጠበቃ ክፍል ሃላፊዋ ቢሮ በአንዲት ፖሊስ ተጠርቼ ተወሰድኩ፡፡ እዚያም ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ዋናዉ መስሪያ ቤት የይቅርታና የአመክሮ ጉዳይ ክፍል እንደመጣና ኮማንደር አስቻላዉ እንደሚባል ከነገረኝ ሰዉ ጋር ተገናኘሁ፡፡ ኮማንደሩ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ያቀረበልኝ የመጀመሪያዉ ጥቃቄ “ይቅርታ ለምን አልጠየቅሽም? ይቅርታ በመጠየቅ ላይ ያለሽ ሀሳብስ አልተቀየረም ወይ?” የሚል ነበር፡፡ ይቅርታ ያልጠየኩት ስላላጠፋሁና የተፀፀትኩበት ጉዳይ ስለሌለ በመሆኑና አሁንም ምንም የተቀየረ አቋም እንደሌለኝ አስረዳሁተ፡፡ “ይሄ የፍርድቤት ጉዳይ ነዉ፡፡ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ እስካለሽ ድረስ ወደዚያ መመለስ አይኖርብንም” አለኝ፡፡ እኔም አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት እንዳሻዉ የሚያሽከረክረዉ ፍርድቤት በንፁሃን ላይ የጥፋተኝነት ዉሳኔና ፍርድ ማስተላለፉን አሜን ብዬ ይቅርታ የምጠይቅበት ምንም አይነት ምክንያት እንደሌለ ገለፅኩለት፡፡ ጥቂት ደቂቃዎች ያህል ስለጤንነቴና በጊቢዉ ዉስጥ ስለሚያጋጥሙኝ ችግሮች በተመለከተ ጥያዎችን ስያቀርብልኝ ቆየና ወደ መጣበት ሌላዉ ዋና ጉዳይ ተመለሰ፡፡
“ቅድም ይቅርታ የማልጠይቀዉ ስላልተፀፀትኩ ነዉ ብለሻል፡፡ አመክሮ እኮ የሚሰጠዉ ለተፀፀተ ሰዉ ነዉና እንዴት ልታደርጊ ነዉ?” በማለት ስለ በአመክሮ የመፈታት አካሄድ አንዳንድ የሚኒስተሮች ምክር ቤት ደንቦችን ጭምር በመጥቀስ ሊያብራራልኝ ሞከረ፡፡ “ታዲያ እንዲህ ከሆነ በይቅርታና በአመክሮ መሀል ምንም አይነት መሰረታዊ ልዩነት የለም ማለት ነዋ?” ለሚለዉ ጥያቄ ቀጥታ መልስ ሊሰጠኝ አልፈለገም ይልቁኑ ሁሉም ታራሚ 2/3ኛዉን የእስር ቅጣቱን ለመፈፀም ሁለት ወራት ገደማ ሲቀሩት እንደታረመና እንደተፀፀተ የሚገልፅ ፎርም መሙላት ስለሚኖርበት እኔም ለመፈታት ከፈለኩ ይህንኑ ማድረግ እንደሚጠበቅብኝ አስረግጦ ነገረኝ፡፡ የፃፍኩት የማምንበትንና መቼም ልቆምለት የምችለዉ እዉነት መሆኑን፣ በዚህ የተነሳ አሸባሪ መባሌ ደግሞ የበለጠ ኢህአዴግን እንድታገለዉ የሚየደርገኝ እንጂ የሚያፀፅተኝ ባለመሆኑ እንዲህ አይነቱን ከማንነቴ ጋር የሚቃረን ፎርም እንደማልሞላ አስረግጬ ነገርኩት፡፡ ኮማንደሩም ላልታረመና ለልተፀፀተ ሰዉ አመክሮ መስጠት ለእነሱም እንደሚከብዳቸዉ ከገለጸልኝ በኋላ “እኛ ፎርሙን ብንሞላልሽስ?” የሚል አስገራሚ ጥያቄ አቀረበልኝ፡፡ እኔ “ታርሜያለሁ” እንዳልኩ ተደርጎ ምንም አይነት ነገር ቢደረግ ሀሰት መሆኑን ከማጋለጥ ወደኋላ እንደማልል አስታወቅኩት፡፡ በዚህ አይነት ተመሳሳይ ሀሳቦች ላይ እየተሸከረከርን ጥቂት ጊዜ ከፈጀን በኋላ እንዳሰብበት አሳስቦኝ ተለያየን፡፡
ይህ ከሆነ ሀሁለት ወራት በኋላ የመፈቻዬ ቀን የነበረዉ ጥቅምት 14/2007 ማለፊን ተከትሎ “የአመክሮ ፎርሙን ለምን አትሞይም?” የሚል ጥያቄ ከተለያዩ ሀላፊዎች ይቀርብልኝ ጀመረ፡፡ ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ ደግሞ ጥያቄዉ እየጨመረ መጣ፡፡ በተለይ በመጨረሻዎቹ የህዳር ወር ቀናት በአንዱ አራት ሆነዉ ክፍሌ ድረስ በመምጣት አነጋገሩኝ፡፡ ለኮማንደሩ የሰጠሁትን ምላሽ ሰጠኋቸዉ፡፡ የሃለፊዎቹ ሁኔታ ከሁለት አመት በፊት የሆነዉን አስታወሰኝ፡፡ ያኔም የይቅርታ ፎርም ለመሙላት ፍቃደኛ ሳልሆን በመቅረቴ እንዳሁኑ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ፎርሙን እሞላ ዘንድ ይጠይቁኝ ነበር፡፡ በእንቢታዬ ስፀና ግን የተለያዩና አብዛኛዎቹም እስከዛሬ የዘለቁ የመብት ጥሰቶችን ይፈፅመብኝ ጀመር፡፡ ያሁኑስ እምቢታዬ ምን ያስከትል ይሆን? አላዉቅም፡፡ አንድ ነገር ግን አዉቃለሁ፡፡ መታረምና መፀፀት ያለብን ኢህአዴግ በሀገር ላይ የሚያደርሰዉን ጥፋት በመቃወማችን ምክንያት የታሰርን እኛ ሳንሆን አምባገነኑ መንግስት መሆኑን!

ዉድ አንባቢያን በመጨረሻ ሰብአዊ መብቶች የተከበሩባት ኢትዮጰያን ለማየት እንዲያበቃን እየተመኘሁ፣ ለተግባራዊነቱም የምችለዉን ሁሉ እንደማደርግና እንደምከፍል ቃል እየገባሁ እሰናበታችኋለሁ፡፡ “ምን ልታደርጊ ትችያለሽ?” የምትሉኝ ካላችሁ መልሴ የሚሆነዉ ማን እንደተናገረዉ ባላስታዉስም “የፍቅር አብዮት” የተሰኘ መጸሀፍ ሳነብ ያገኘሁት አንድ አባባል ነዉ ፡፡
” ሁሉን ማድረግ አልችልም ሁሉን ማድረግ አለመቻሌ ግን የምችለዉን ከማድረግ ወደ ኋላ አያስቀረኝም”

ርዕዮት አለሙ
ከቃሊቲ እስር ቤት

ባለቤት የሌለው መሬት –ቤጌምድር! (የመከላከያ ሰራዊት በትግራይ እና አማራ ተዋጊዎች መካከል ሰፈረ (ከዚያስ?))

$
0
0

begemedeir

(ዳዊት ከበደ ወየሳ)

ሉም ኢትዮጵያዊ ስለዚህ አካባቢ እኩል ግንዛቤ ላይኖረው ይችላል:: በመሆኑም ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ስለዚህ አካባቢ ታሪካዊ ዳራ ማሳየት አስፈላጊ ሆኗል:: እናም በታሪክ መንኮራኩር ትንሽ ወደኋላ መሄድ ሊኖርብን ነው::
 ይህ የሰሜን አውራጃ ከጥንት ጀምሮ ቤጌምድር ተብሎ የሚታወቅ ሲሆን በራሱ መሪዎች ይተዳደር የነበረ ስፍራ ነው:: በደርግ ዘመን ስሙ ተቀይሮ ስሜን ጎንደር ሲባል በወቅቱ ከፍተኛ ክርክር የተደረገ ቢሆንም; ቀስ በቀስ ቤጌምድር መባሉ ቀርቶ ስሜን ጎንደር የሚለውን ስያሜ ይዞ ዘልቋል:: ይህ የቤጌ ምድር ክልል በሰሜን ከኤርትራ ጋር በመረብ ወንዝ, ከትግራይ ጋር ደግሞ በተከዜ ወንዝ ተፈጥሮአዊ ድንበር ሰርቶ ይተዳደር ነበር:: 

መሳይና ፋሲል ታገቱ ( ሄኖክ የሺጥላ)

$
0
0

አገቱኒ የምትለውን የግዕዝ ቃል በመጀመሪያ በመዝሙረ ዳዊት ላይ ነው ያየሁዋት ፣ መዝሙር (3)፣ እንዲህ ነበር ሰንጠር ብላ የገባችው ።

ወተንሳእኩ እስመ እግዚያብሔር አንስአኒ
አይፈርህ እመ አእላፍ ሕዝብ
ዕለ አገቱኒ ወቆሙ ላዕሌየ ።

ትርጉሙም ….

እግዚያብሔር አንቅቶኛልና እና ነቃሁ
ከአእላፍ ሕዝብ ከከበቡኝም አልፈራም ።

ስለዚህ ( አገቱኒ =ከከበቡኝም ) ማለት ይሆናል ። መያዝም አቻ ቃል ነው ።

ከዚያ ወዲያ ታዋቂው ቦጠሊቀኛ ፣ መምህር ፣ ተመራማሪ ፣ እኔ ደሞ ነብሴ እስኪጠፋ የምወዳቸው ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ለ መጽሃፋቸው አርዕስት አድርገውት ። አዎ አገቱኒ እና መታገት መንፈሳቸውን አንድ ያደረጉልኝ መሳይ መኮንንና ፋሲል የኔ-ዓለም ናቸው ። በመታገት !

መስይና ፋሲል ግን ዛሬ መታገታቸውን አብስረዋል ። መሳይና ፋሲልን ያገታቸው ግን አንዳርጋቸውን የመን ላይ አፍኖ የወሰደው ስርዓት ፣ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን ቃሊቲ አፍኖ የገደለው ስርዓት ፣ እስክንድርን ፣ ተመስገንን ፣ አንዷለምን ፣ ር’ዮትን ፣ በቀለን ፣ ኦልባናን ፣ ናትናዔልን ፣ የሽዋስን እና ሌሎችንም በውሸት አዋጅ እና ክስ ያሰረው ስርዓት አይደለም ፣ ወይም ደሞ አምነውት የተጠጉት ፣ በብዙ ሀሜት እና ጥርጣሬ ስር ያለው የዔርትራ መንግስትም አይደለም ፣ ወይም ደሞ የሚኖሩባት አማሪካ እና አምስተርዳም መንግስታቶች በአሸባሪ ክስ ከሰዋቸው ፣ የመንቀሳቀስ መብታቸውን ነፍገው ይዘዋቸውም አይደልም ። ይልቁንስ መሳይንና ፋሲልን ያገተው ስለ ኢትዮጵያ የሚያስበው ህሊናቸው ፣ ጠንካራ ፍቅራቸው ፣ እምነታቸው ነው ። በፊትም ይሁን በጉዋሮ በር የሞት ቀጠና እየተባለ የሚጠራውን የኤርትራ አየር ሰንጥቀው እንዲገቡ ያደረጋቸው ለሀገራቸው ያላቸው እምነት ፣ በይበልጥም ለጋዜጠኝነት ( ለሙያው )ያላቸው ክብርም ነው ። እርግጥ ነው ጋዜጠኝነት አድርባይነት ፣ ጸጉርን ከምክሞ ፣ ባዝሊን ለድፎ ፣ በከረባት እና በኮት ተቆልፎ ፣ ጀምር ! ሲባል ውሸት ማውራት በሚጀምር ህሊና ቢስ ጋዜጠኞች ፣ ሆድ አምላኩ ፣ ምቾት ልኩ በበዙበት ፣ እንዲህ ባለ ሁናቴ ለፍቅር እና ለእውነት መገዛት ፣ ለማኝነት እና በማንነት መታገት መታደል ነው ።

10423279_741972125884099_8834539761347632678_n

ዘርኝነት በተንሰራፋበት ፣ እውነት እንደ ውሃ በተደፋበት ፣ ገዳይ በሚደነፋበት ፣ ተበዳይ አንገቱን በደፋበት ስርዓት ውስጥ ተለማማጭ ስብእና ፣ ተገዢ ልቦና የለኝም ብለው ህውሃትን ሌት ተቀን እየተታገሉት ፣ እየተቃወሙት ፣ እየተፋጩት ያሉ ጥቂቶች አይደሉም ። ያም ሆኑ መስዋትነት ልክ አለውና ፣ የመሳይና የሲሳይ መስዋትነት ፣ ከጥቂቶቹ ከባድ እና ፈታኝ ድፍረቶች እና ቆራጥነቶች ውስጥ አንዱ ነው ። ስለዚህም እነሱን ያገታቸው ፍቅር እኔንም በነካ እጁ ይዳብሰኝ ዘንድ ምኞቴ ነው ። በርቱ ! ከ ጨለማው ልንወጣ ነው ፣ የብርሃኑ ጫፍ ከ ዋሻው ጫፍ ላይ ይታየኛል ። ልናሸንፍ ነው ምክንያቱም ልቤ አልፈራም ፣ አልሸሽም ይለኛል ።

አምላኬ ያቺን ቀን ፣ ያቺን ቀን አምጣት ። ጠላቴን ” ያዝልቅልሽ እስከሚያልቅልሽ !” ብያታለሁና ። ያቺ ቀን ። ትታየኛለች ። እንደ ሰመመን ሳይሆን ፍንትው ብላ !

በጎንደር አርማጭሆ የተቀሰቀሰው ግጭት ሊበርድ አልቻለም

$
0
0

10923573_1560615314186107_7573440129440943485_nኢሳት ዜና :-ባለፈው ሳምንት ታጣቂዎች በከባድ መሳሪያዎች በመታጀብ በጎንደር አርማጭሆ ውስጥ <<ሶረቃ>> የሚባለውን አካባቢ ወደ ትግራይ ለማካለል በወሰዱት እርምጃ የተነሳው ግጭት እስካሁን ሊበርድ እንዳልቻለ በስፍራው የሚገኘው የኢሳት ወኪል ያጠናቀረው ሪፖርት ያመለክታል።
ወኪላችን እንዳለው ታጣቂዎቹ፤ አርሶ አደሮችን በኃይልና በማን አለብኝነት አስነስተው ቦታውን ለማካለል ያደረጉትን ጥረት የአካባቢው ህዝብ ከዳር እስከዳር በመንቀሳቀስና ውጊያ ጭምር በመግጠም ነበር ያከሸፈው።በወቅቱ የታጣቂዎቹን እርምጃ ተከትሎ በተቀሰቀሰው ግጭት ከሁለቱም በኩል ጉዳት መድረሱ ታውቋል።
ውጥረቱ እስካሁን ያልበረደ ከመሆኑም ባሻገር የ አካባቢው ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር እየተጠራራ ንብረቱን ለማስጠበቅ በአንድ ተሰባስቦ መዘጋጀቱ፤ ሌላ ዙር የከፋ ግጭት ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት አሳደሯል።


ለጥምቀት ሰማያዊ ቲሸርት እንዳይለበስ ተከለከለ • ህዝብን ያነቃቃሉ የተባሉ መንፈሳዊ ጥቅሶች መጠቀም አይቻልም ተብሏል

$
0
0

semayawi(ነገረ ኢትዮጵያ) የክርስትና እምነት ተከታይ ወጣቶች ጥምቀት በዓል ላይ ሰማያዊ ቲሸርቶችን እንዳይለብሱ መከልከላቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን ጀምሮ እስከ ጃንሜዳ አካባቢ የሚኖሩ ወጣቶች በተለያዩ ማህበራት ስር ለጥምቀት በዓል ዝግጅት እያደረጉ እንደሚገኙ የገለጹት ምንጮቹ ከዝግጅታቸው መካከል ቲሸርት አሳትሞ መልበስ አንዱ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ሆኖም ወጣቶቹ ለጥምቀት በዓል የተለያዩ የመጽሀፍ ቅዱስ ጥቅሶች የታተሙበት ሰማያዊ ቲሸርት ማሳተማቸውም ተከትሎም ደህንነትና ሲቪል የለበሱ ፖሊሶች በየ ቤታቸው እየዞሩ ‹‹ጥምቅት በዓል ላይ ሰማያዊ ቲሸርት መልበስ አይቻልም፡፡›› እያሉ እያስጠነቀቁ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በነገው ዕለትም ካድሬዎች ከፈረንሳይ ሌጋሲዮን እስከ ጃን ሜዳ አካባቢ የሚገኙ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር ስብሰባ መጥራታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ህዝብን ያነቃቃሉ ከሚል ስጋት አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በቲሸርት ላይም ሆነ ሌላ ለጥምቀት በዓል ላይ በማድመቂያነት በሚውል ነገር ላይ ማተም እንደማይቻል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ወጣቶቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ለጥምቀት በዓል ማድመቂያነት እንዳይውሉ ከተከለከሉት ጥቅሶች መካከል ‹‹የጌታ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን፣ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚያብሄር ትዘረጋለች፣ የአባቶቻችን ርስት አንሰጥም….›› የመሳሰሉት ይገኙበታል ተብሏል፡፡ እነዚህን መንፈሳዊ ጥቅሶች መጠቀም እንደሚያስቀጣም ደህንነትና ፖሊሶች የበዓሉ አዘጋጅ ወጣቶችን አስጠንቅቀዋል፡፡

ወጣቶቹ ሰማያዊ ቲሸርትም ሆነ የተከለከሉትን መንፈሳዊ ጥቅሶችን በሐይማኖታዊ ፋይዳቸው ምክንያት ባለፉት የጥምቀት በዓላት ላይ ሲጠቀሙባቸው እንደቆዩ፣ አሁን ደህንነቶች እነሱ ካላሰቡት ፖለቲካ ጋር ማገናኘታቸው እንዳሳዘናቸውና ከሐይማኖታዊ ፋይዳቸው ውጭ ምንም አይነት ትርጉም እንዲኖራቸው ታስበው የተሰሩ ባለመሆናቸው በበዓሉ ላይ እንደሚጠቀሙባቸው ገልጸዋል፡፡

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ እሁድ ጥር 3 ቀን ጠቅላላ ጉባኤው ለማድረግ በዝግጅት ላይ ነው።

$
0
0

UDJየአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ እሁድ ጥር 3 ቀን ጠቅላላ ጉባኤው ለማድረግ በዝግጅት ላይ ነው። የጠቅላላ ጉባዔ መደበኛ ስብሰባ በየሶስት አመቱ ሲሆን አስቸኳይ ወይንም ልዩ የጠቅላላ ጉባኤ መጥራት እንደሚቻል የአንድነት ደንብ በግልጽ ያስቀምጣል፡ በአንድነት ደንብ መሰረት አስቸኳይ ወይም ልዩ ጠቅላላ ጉባዔ መጥራት የሚቻለው ከጠቅላላ ጉባኤ አባላት አንድ ሶስተኛው ሲጠይቁ ወይንም ምክር ቤቱ ሲወስን ብቻ ነው። የጠቅልላ ጉባኤ አባላት በፓርቲው የተመዘገቡ፣ የድርጅቱ አባልነት መታወቂያ ያላቸው ናቸው። የድርጅቱ የሥር አስፈጻሚ ኮሚቴ ፣ የቀድሞ ሊቀመንበር ሆነ የአሁኑ ሊቀመንበር ጠቅላል ጉባኤ የመጥራት ስልጣን በደንቡ መሰረት የላቸውም።
በዚህ መሰረት ከጠቅላላ ጉባኤ ቀጥሎ የድርጅቱ የበላይ አካል የሆነው ብሄራዊ ምክር ቤቱ፣ ሐሙስ ታህሳስ 30 ቀን ባደረገው ስብሰባ ነበር እሁድ የሚደረገዉን ጠቅላላ ጉባኤዉ የጠራው። በምክር ቤቱ ስብሰባ፣ “ቅሬታ አለን” ባለው አሁን ባለው አመራር ላይ ችግር ያላቸውና ምርጫ ቦርድ በመሄድ ከምርጫ ቦርድ ጋር አብረው ሲሰሩ ከነበሩት መካከል፣ ሶስት የምክር ቤት አባላት ( 5 %) ፣ ሐሳባቸውን እና ታቋዉሟቸውን ለማሰማት እድል ተከፍቶላችው የነበረ ቢሆንም፣ ዝምታን መርጠዋል። በስብሰባው የተገኙ ሌሎች 39 (78%) የምክር ቤት አባላት ግን የጋራ አቋም በመያዝ፣ በምርጫ ቦርድ እየተደረገ ያለውን ኢ-ሕገመንስግታዊ እንቅስቃሴ በማውገዝ አንድነት በፊቱ የተደቀነበትን መሰናክል ያልፍ ዘንድ ጠቅላላ ጉባዔዉ በተሎ እንዲጠራ የወሰነው።
መኢአድ እና አንድነት የዉህደት ስምምነት በሚፈርሙበት ጊዜ ኢሕአዴግ ዱርዬዎች ልኮ ስብሰባዉን ለመረበሽ ሞክሮ እንደነበረ ይታወቃል። በዚህም ምክንያት ተመሳሳይ ነገር እንዳይፈጠር፣ ፖሊስ ለምን አስቀድማችሁ አልነገራችሁኝ ነበር እንዳለይ፣ ፖሊሲ አስፈላጊዉን ጥበቃ እንዲያደርግ ከወዲሁ የማሳወቅ ሥራም ተሰርቷል። ምርጫ ቦርድ ሕጉ እንደሚጥይቀው ታዛቢዎች እንዲልክም ደብዳቤ እንዲደርሰው ተደርጓል።
– See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/3418#sthash.jqJccZ66.dpuf

የሕዝባችን አንድነት እና የአገራችን ታሪካዊ መልካአ-ምድር ለመጠበቅ ታሪካዊ ሃላፊነት ለሚሰማችሁ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፦

$
0
0

Gondor Hibretእንደሚታወቀው የጎንደር ክ/ሀገር፤ የጋራ መመኪያችን ለሆነችው ኢትዮጵያችን የአንድነት መሰረት የታሪክ እምብርት በመሆን ትታወቃለች። በመሆኑም፤ ለሁላችንም ኩራት እና መመኪያ የሆነችውን ኢትዮጵያ አገራችን ለማጥፋት መሰሪ አላማን ይዘው የተነሱ አገር አጥፊዎች ሁሉ የመጀመሪያ የጥፋት ክንዳቸውን የሚሰነዝሩት፤ ጦራቸውን የሚወረውሩት አላማቸው በቀላሉ ይሳካ ዘንድ በቅድሚያ በጎንደር ላይ ነው። እንደምሳሌ የውጭ ወራሪዎችን ብንጠቅሥ፤ በእጅ አዙር ቱርኮች ከግብፃዊያን ጋር በመተባበር የሀገር ውስጡን ግራኝ መሃመድን በመሳርያነት በመጠቀም ከ1519-1535 ዓ. ም፤ እንዲሁም ድርቡሾች በ1880-81 ዓ. ም. በቀጥታ፤ በማዝመት፤ ስፍር ቁጥር የሌለው ወገኖቻችን ጨፍጭፈዋል፤ የታሪክ ቅርሶችን መዝብረው፤ ቀሪውን ለማሥረጃ እንዳይተርፍ ለቃቅመው አቃጥለዋል። —

ሙሉውን ጋዜጣ በፒ.ዲ.ኤፍ ለማንበብ ይህንን ይጫኑ—-

ሰበር ዜና –አንድነትን ፓርቲ ምርጫዉን መሳትፍ የለበትም የሚል የፖለቲካ ዉሳኔ እንደተወሰነ ፣ ከሕወሃት አመራሮች ቅርበት ያላቸው ምንጮቻችን ገለጹ

$
0
0

ሰበር ዜና – አንድነትን ፓርቲ ምርጫዉን መሳትፍ የለበትም የሚል የፖለቲካ ዉሳኔ እንደተወሰነ ፣ ከሕወሃት አመራሮች ቅርበት ያላቸው ምንጮቻችን ገለጹ

UDJ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ የበረራ ቁጥር ET -AQV አይሮፕላን በጋና አክራ ተከሰከሰ

$
0
0

ethiopian airlines 2

ethiopian airlines
Minilik Salsawi

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ አይሮፕላን በኮቶካ ኢንተርናሽናል ኤርፖርት ሜከስከሱ ከጋና አክራ የወጡ ዜናዎች አመለከቱ::

የመከስከስ አደጋው የተከሰተው ካርጎ አይሮፕላኑ በኤርፕርቱ ለማረፍ ሲንደረደር በነበረው መጥፎ አየር ምክንያት መሆኑን የአየር መንገዱ ባለስልጣናት ተናግረዋል::አደጋው የተከሰተው ጠዋት ሶን የጋና አየር መንገድ ባለስልጣናት ዘግይተው መረጃ መስጠታቸው ታውቋል::

የበረራ ቁጥሩ ET -AQV የሆነው አይሮፕላን ከቶጎ ሎሜ ተነስቶ አክራ ለማረፍ ሲሞክር አደጋው መድረሱን ባለስልጣናቱ ተናግረዋል::በአይሮፕላኑ ጋር የነበሩ 3 ሰዎች የተረፉ ሲሆን በአሁን ሰአት በወታደራዊ ሆስፒታል ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል::

ከመላው አገሪቷ በአንድ ቀን፣ በአንድ ፊሽካ ጥሪ፣  የአንድነት ጉባኤተኞች ተሰባስበዋል

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) “አንድነትን ለመታደግ ከየአቅጣጫው እየተመመ ያለው የአንድነት የሰላማዊ ትግል ሰራዊት፣ በጊዜ በዋናው ጽ/ቤት ከትመዋል፤ ይሄው ታሪክ ሊሰራ፣ የምርጫ ቦርዱ አሳፋሪነት፣ የስርዓቱ ሽፍትነት ሊመሰክር፤ ይህን የአንድነት ልጆች ተጋድሎ ለልጅ ልጅ ሊነግር ታድመዋል።

unnamed (1)ይህ ትልቅ ታሪክ ሲፈፀም በቦታው ተገኝቼ ለመመልከት በመቻል ኩራት ነው የሚሰማኝ”  ሲሉ አስተያየታቸዉን የሰጡት የአንድነት ተጠባባቂ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቶ አስራት አብራሃ፣   ነገ እሁድ በሚደረገው ጠቅላላ ጉባኤ፣  አባላት፣  በአራት ቀናት ጥሪ ፣ በቁጭትና በቁርጠኝነት፣  በልባቸው የነጻነትን ደዉል እያቃጨሉ መምጣታቸው እንዳኮራቸው ይናገራሉ።

 

“በአሁኑ ሰዓት ከመላ ሀገሪቱ በአንድ ቀን፤ በአንድ ፊሽካ ጥሪ የአንድነት ጉባኤተኛ አንድነት ፓርቲን በኢህአዲግ ከሚመራው ምርጫ ቦርድና ተላላኪ ወንበዴዎች ሴራ ለመታደግ ብሎም ቀጣይ የትግሉ ምእራፎች ላይ ለመምከር በአሁኑ ሰዓት በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት ከተን ገብተናል” ሲሉ አንድ የአንድነት አባል አስተያየት ሲሰጡ ፣ ሌላው አባል ደግሞ  “ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ አንድም ነፃና ፍትሀዊ ምርጫ አስፈፅሞ የማያውቀው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ፣ ኢህአዴግ ምርጫ እንዲያጭበረብር በመፍቀዱ ሳቢያ ምርጫን ተከትሎ በሚነሱ አለመግባባቶች በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ደማቸው በየመንገዱ ፈሷል፡፡ ምርጫ ቦርድ ከገዳዮቹ ባልተናነሰ የእነዚህ ውድ ኢትዮጵያውያ የደም እዳ አለበት፡፡ ያለጥርጥር የምርጫ ቦርድ ሀላፊዎችም ከገዢው ቡድን ሹማምንት እኩል የደም ዕዳቸውን የሚያወራርዱበት ቀን ሩቅ አይሆንም፡፡” ሲሉ ምርጫ ቦርድ እያደረገ ባለው ነገር በታሪክ ተጠይቂ እንደሚሆን ገልጸዋል።

unnamed

“ምርጫ ቦርድ እየተባለ የሚጠራው የኢህአዴግ ተቀፅላ ተቋም አጅግ አስደማሚ ጠቅላላ ጉባኤ ባካሄድን ማግስት በአራት ቀናት ውስጥ ሌላ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ጠርታችሁ እንደገና ፕሬዚደንቱ ካላስመረጣችሁ የመጨረሻ እርምጃ እወስዳለሁ በማለት ሱሪ በአንገት በሆነ ሁኔታ በድጋሚ ሌላ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ እንድንጠራ ተገደናል፤ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ከየቦታው ከአራቱም የሀገሪቱ አቅጣጫዎች ክተት ብለው ሌሊትና ቀን ተጉዘው ፓርቲያቸው ለማዳን በጊዜ ደርሰናል” ሲሉ አንድ ሶስተኛ አባል ይናገራሉ።

 

ምርጫ ቦርድ ሕግ በሚጠይቀው መሰረት ታዛቢዎች እንዲልክ ደብዳቤ ቢደርሰውም፣ ራሱ ባደራጃቸው በነአየለ ስምኔህ፣ ዘለቀ ረዲ ቡድን “ሌላ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቷል” በሚል እንደማይገኝ በደብዳቤ አሳውቋል። ሆኖም የአንድነት አመራር አባላት “ምርጫ ቦርድ ተገኝም፣ አልተገኝም፣ ጠቅላላ ጉባዬያችንን እናደርጋለን።  በድጋሚ እንደገና ከቀበና ጽ/ቤታችን የዲሞክራሲ፣ የለወጥና የነጻነት ደዉል እንደዉላለን” ሲሉ በአገር እና ከአገር ዉጭ ያለው ኢትዮጵይዊ ሁሉ በዚህ ወሳኝ ወቅት ከጎናቸው እንዲሁን ጥሪ አቅርበዋል።

 

“በዚህ ስርዓት ስር ለአንድ ሌሊት እንኳ ቢሆን በሰላም ተኝቼ ካደርኩኝ ቀኜ ይረሳኝ፤ የረገጠኩት መሬት ይክዳኝ” እንዳሉት የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቲ አስራት አብርሃ፣ በአንድነት አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ዘንድ ትልቅ ቁርርጠኝነትና ወኔ እየተያ እንደሆነ የሚደርሰን ዘገባ ያመለክታል።

 

እሁድ ለሚደረገው የጠቅላላ ጉባኤ ከመላው አገሪቱ እየተመሙ የመጡ የአንድነት ተወካዮች በአንድነት ጽ/ቤት

 

 

 

የአንድነት ጥር 3 ቀን ጠቅላላ ጉባኤ ላይቭ ዘገባ

$
0
0

የአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ በጥሩ ሁኔተ እየቀጠለ ነው። ምርጫ ቦርድ ሕጉ በሚጠይቀው መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ ለመታዘብ አልተገኘም።
አቶ አለነ ማጸንቱ አቶ በላይ ፍቃዱን ኢንዶርስ አደርገው ራሳቸው ከ እጩነት አወጥተዋል። ምርጫዉ በአቶ ዳግማዊ ተሰማና በአቶ በላይ ፍቃዱ መሃከል ነው የሚደረገው።

10394814_759966304088306_449840067842230969_n 10428627_759966307421639_3753389504227116176_n 10906498_759966310754972_3457821015692444450_n

የአንድነት ፓርቲ ዛሬ ጥር 3 ቀን ጠቅላላ ጉባኤዉን ያደርጋል።  ምርጫ ቢቦርድ ከሕግ ዉጭ አንድነት ፓርቲ የሚወዳደርበትን የምርጫ ምልክት አልሰጥም በሚል፣ አንድነትን ከምርጫዉ ለማስወጣት ደፋ ቀና እያለ ነው። የአንድነት ፓርቲ ግን ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠውን መሰናክል ለማለፍና ለምርጫ ቦርድ ቀዳዳዎችን ሁሉ ለመዝጋት በሚል ነው ስብሰባው የተጠራው። በዚህ ጠቅላላ ጉባኤ ምርጫ ቦርድ እንዲገኝ ጥሪ የቀረበለት ቢሆንም ሌሎች ግለሰቦች ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቷልና በሁለት ስብሰባዎች መገኝት አንችልም በሚል  ታዛቢ እንደማይልኩ በደብዳቤ ገልጸዋል። ሆኖም የአንድነት ፓርቲ ምርጫ ቦርድ ኖረም አልኖረም ጠቅላላ ጉባኤዉን እንደሚያደርግ በመግለጽ ለምርጫ ቦርድ ምላሽ ሰጥቷል።

12፡30 PM  አዲስ አበባ ሰዓት

በአንድነት የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ምርቭጫ ቦርድ በሕግ ታዛቢ የመላክ ግዴታ ነበረበት። ሆኖም ምርጫ ቦርድ ታዛቢ አላከም።  በሕወሃት የተሰተዉን አንድነትን የ”ማገድ” የፖለቲክ ዉሳኔ ለማስፈጸም የቆረጠ ይመስላል።

12፡00 PM  አዲስ አበባ ሰዓት

አቶ ዳግማዊ ተሰማ፣ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ሰብሳቢ የነበሩ ሲሆን፣ ከሰብሳቢነታቸው ሪዛይን አደርገው ራሳቸውን ለሊቀመንበርነት ራሳቸው እጩ አድርገው አቅርበዋል። “እኔን ብትነርጡኝ አንድነት የበለጠ ትልቅ ደረጃ እንዲደርስ ለማድረግ እሰራለሁ።ኔን ብትመርጡኝ “በተሻለ አደረጃጀት ከተፎካካሪ በተሻለ ሁኔት ልመራ እችላለሁ” ሲሉ ጉባዬተኞች ድምጽ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።  ሶስት እጩዎች ቀረበው  ፣ አንዱ አቶ አለነ አቶ በላይን ኢንዶርስ በማድረጋቸው፣ የቀሩት ተወዳዳሪዎች አቶ ዳግማዊ ተሰማና አቶ በላይ ፍቃዱ ናቸው።

dagi

11፡30 AM አዲስ አበባ ሰዓት

አቶ አለነ ማጸነቱ ንግግር እያደረጉ ነው። አንድነት ከሌሎች ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመተባበር ትግሉን እንደሚያሳድጉ ተናግረዋል። ምሁራን ወደ ትግሉ እንዲመጡ ትልቅ የማግባባት ሥራ እንደሚሰሩ  ተናግረዋል።  አቶ አለነ ስለ አት በላይ እየተናገሩ ነው። አቶ በላይ ያደረጉት አስተዋጾ  በመጠቀስ ፣ “እኔን ለመምረጥ ያሰባችሁ አባላት በላይ በፍቃዱን እንድትመርጡ እርሳቸውን ኢንዶርስ አድርጊያለሁ” ብለው አቶ በላይን ኢንዶርስ አድርገዋል። አስመራጭ ኮሚቴ ሌላ እጩ ካለ መቅረብ እንደሚችል በገለጹት መሰረት አንድ አባል “የድርጅት ጉዳይ ማምለካ አሰገብቼ ነበር። ” በሚል አቤቱታ አቅርበው፣ የ እጩነት ፎርም እየሞሉ ናቸው።

alene3

11፡30 AM አዲስ አበባ ሰዓት

የአንድነት ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ሊደረግ ነው። አስመራጭ ኮሚቴ ተመርጦ ቦታዉን ይዟል።  አስመራጭ ኮሚቴው ለፕሬዘዳነት ምርጫ በብሄራዊ ምርጫ   የተቀመጡ መመስፈርቶችን አነበቡ። በመስፈርቱ መሰረት ማንኛውም አባል ራሱን እጩ ማድረግ እንደሚችል አስመራጭ ኮሚቴ ለጠቅላላ ጉባኤ ራሱን እጩ አድርጎ እያቀረበ ነው። ሁለቱ አባላት ራሳቸውን እጩ አድርገው አቅርበዋል። አቶ በላይ ፍቃዱ እና አቶ አለነ ማጸንቱ እጩ ሆነው ቀርበዋል።

አቶ በላይ ፍቃዱ ንግግር እንዲያደረጉ በመርጫ ቦርድ ተጠይቀው መናገር ጀምረዋል። አንድነት ባለፊት ሲስት ወራት በ   ከ15 ብቢሮዎች በላይ እንደተከፈቱ፣ በአጠቃላይ አሁን ወደ 30 ቢሮዎች እንዳሉት ገልጸዋል።  የትግሉ ንቅናቄ በቢሮውች እንዲመሩ እናደርጋለን ብለዋል አቶ በላይ። “ምርጫ 2007 ፖለቲክ ለዉጥ ካልመጠ መቼም አይመጣም፣ ለዉጥ እንዲመጣ ከናንተ ሆነ መደረግ ያለበት እናደርጋለን” ሲሊ ለጉባየተኞቹ አስረድተዋል።

5 (5) - Copy

11:00 AM አዲስ አበባ ሰዓት

ዲፕሎማቶች አንድነት በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ተገኝተዋል።  “የአንድነት አባል በአንድ ፌሽካ በአንድ ቀን መገኘት ይችላሉ!” የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ

10897929_1561877107393238_227374864912635223_n 1441466_1561877010726581_7637902554378791076_n

10፡30 AM   አዲስ አበባ ሰዓት 

ተወካዮች ቦታቸውን ይዘዋል። የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ በላይ ፍቃዱ መቀመጫቸዉን ይዘዋል። ከክፍለ ሃገር የመጡ በርካታ የጠቅላላ ጉባኤ ተወካዮች የተወሰኑቱ በዚህ መልክ ነበር  በአንድነት ጽ/ቤት ውጁስጥ ያደሩት።

 

የኢትዮጵያውያን ነፃነት ለማስመለስ እስከደም ጠብታ ለመክፈል የተዘጋጀ የአንድነት አባል ውርጭና ብርድ አይበግረውም!!!

ለነዚህ የኢትዮጵያ ልጆች ክብር ይገባቸዋል!!

እነዚህ በፎቶው ላይ የምትመለከቷቸው የአንድነት ጉባኤተኞች ከመላው የኢትዮጵያ ክልሎች በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ላይ በገዢው የኢህአዲግ መንግስትና በማደጎ ልጁ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም ህሊናቸውን በገንዘብ ሽጠው አንድነትን ለመፈረካከስ ከተነሱ ጥቂት ሆድ አደር የማፊያ ቡድኖች እየተሰነዘረበት ያለውን ተከታታይና እልህ አስጨራሽ ደባ ለማክሸፍ በ24 ሰዓት ጥሪ ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው፤…… በአንድነት ፅ/ቤት በ03/05/07 ዓ.ም የሚካሄደውን ጉባኤ ለመታደም የአንድነት የክተት ጥሪ ቆራጥ ታጋዮች ናቸው፡፡ ….በፎቶዎቹ ላይ እንደምታዩት እነዚህ የኢትዮጵያን እጣ ፈንታ ለመወሰን በመታገል ላይ ያሉ ሰላማዊ ታጋዮች፤ ……ቁርጥራጭ ወረቀትና ማዳበሪያ አንጥፈው፤…… ድንኳንና ማዳበሪያ ለብሰው፤….በቀዝቃዛው የአድስ አበባ አየር የሲሚንቶ ወለል ላይ በብርድ የሚጠበሱ ቆራጥ፤ለለውጥ የተነሱና ለኢትዮጵያውያን ክብር ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው ውርጭ የሚጠጡ፤……ኢህአዲግን እንቅልፍ አሳጥተው የሚያቃዡ ጀግኖቻችን ናቸው!!! ……በእውነት ሁሉም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ክብር ሊሰጣቸው ይገባል፡፡
==================
በኢትዮጵያውያን ህዝቦች ገንዘብ የኢህአዲግ ካድሬዎች በሊሙዚን መኪና እየተንፈላሰሱ፤……በአለም ላይ እጅግ የቅንጦት ሂወት በሚባል አኳኋን እየኖሩ፡፡ ……ውስኪና ቮድካ ጨብጠው ለቅጥረኞቻቸው በሚያስተላልፉት ቀጭን ትእዛዝ እልፍ የነፃነት አርበኞችን እያስገደሉ፤እያሳሰሩ፤እያሰደቱ…… በህዝብ ሀብት በሚንቀሳቀሰው የህዝብ ሚዲያዎች በቅንጦት ብቅ እያሉ የፍትህና ዴሞክራሲ ተረጋግጧል፤….ሀገሪቱ በሁለት ዲጂት አደገች….ምናምን እያሉ የሚደሰኩሩ አንባገነን የኢህአዲግ ባለስልጣናት ባሉበትና የኢትዮጵያውያንን ነፃነት በጠብ መንጃቸው ቁጥጥር ስር ያረጉትን ኢህአዲጋውያን፤…..ለመታገል ክብርና ነፃነታችንን ከአፈሙዛችሁ ስር ፈልቅቀን እናወጣለን ብለው በውርጭ ለሚጠበሱት የአንድነት አባላትና አመራሮች ስለእውነት የሚያስብ ሁሉ ክብርና አድናቆት ሊሰጣቸው ይገባል!!! ……ውድ የኢትዮጵያ እውነተኛ ልጆች!!! ….እመኑኝ አንድነትን ሊያቆመው የሚችል ሀይል የለም፡፡ ….የምንታገለው ምርጫን የመጨረሻ የትግል ሂደት አድርገን አይደለም፤…. በመሆኑም በነዚህ ብርቅዬ ታጋዮች ስም አንድነት ፓርቲ በተከታታይ ለሚወስናቸው ፖለቲካዊ ውሳኔዎችና የትግል ጥሪዎች አጋርነታችሁን እንድታረጋግጡ መልእክቴን አስተላልፋለሁ፡፡ ……በ2007 ኢህአዲግ የፈራው ለውጥ አይቀሬ ነው፤….ድል የህዝብ ይሆናል!!! ….ለለውጥ እንነሳ!!!

udjj1 udjj2 udjj3 udjj4 udjj5 udjj6


Video- ማን ያርዳ የቀበረ ማን ይናገር የነበረ

$
0
0

ማን ያርዳ የቀበረ ማን ይናገር የነበረ

 

Andualem

በቂሊንጦ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን አስታወቁ

$
0
0

በቂሊንጦ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን ገለፁ፡፡

Jailበቂሊንጦ ከሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች መሃል የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው እና የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ለአዲሱ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ በላይ ፍቃዱ ድጋፋቸውን መስጠታቸውን ተከትሎ በወህኒ ቤት ውስጥ ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

አመራሮቹ ስቃይ እየደረሰባቸው የሚገኘው ለአቶ በላይ ፍቃዱ እውቅና ሰተው በሌላ በኩል በአንድነት ስም በተጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለተመረጡት የፓርቲው ሰዎች እውቅና መንፈጋቸውን ተከትሎ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአንድነት ፓርቲ አመራር የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከሃምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡

Source –

Millions of voices for freedom – UDJ

ሰሚ ያጣ ጮኸት ከካርቱም –አጥናፉ መሸሻ

$
0
0

751sudan1   በመላው አለም ለምትገኙ ኢትዮጽያዊያኖች ሁሉ    ፤ በተለያዩ ግዜያት  ሰብአዊ  መብታችን  ይከበር ዘንድ ፤  ከምድር ሱዳን የሲቃ ጮኸታን ሰምታችሁ  በተቻላችሁ መጠን ትታደጉን ዘንድ ደጋግመን በፁሁፍ አሰምተናል ፤ እንሆ  በአሁኑ ሰአት ወያኔ ከምንግዜውም በላይ በከፋ መልኩ  ፤ ካርቱም ውስጥ  ስደተኛውን አንደተለመደው እያሳፈሰ ፤ ወዳልታወቀ እስር ቤት እያሳወሰደ ይገኛል ፤ በተለይ ጀዋዛት እየተባለ በሚገኘው እስር ቤት ውስጥ ፤ በሸህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ታጉሮው ይገኛሉ ፤ ከእነዚህም ውስጥ ለልደት ደሮ ለመግዛት ገበያ የሔዱ እህቶቻችን ከነደሮቸው ፤ ልደትን መድሀኒአለም ቤተክርስትያን አክብረው የሚመለሱ ነጭ የለበሱ ወገኖች  እስር ቤቱን ሞልተውታል ፤ በተጨማሪ ዴም እየተባለ ከሚጣረው ሰፈር ውስጥ አንድ ወጣት ሀለፎም አዲሱ ተካልኝ የተባለ የአንገት መስቀሉን በጥሰው መኪና ላይ ጭነው እስር ቤት አጎረውት ይገኛል ፤ መታወቂያ ለማውጣት እድሜው የማይፈቅድ ወጣት ሳይቀር  ያለ አንዳች እርህራሔ አስር ቤት ይገኛል ፤ ይህን ወጣት እንደምሳሌ ተጠቀምንበት እንጅ በርካታ ወጣቶች መኖራቸውን አናሳስባለን;;

ዛሬ አንባገነኑ ወያኔ ፤ በከፍተኛ መረበሸ ውስጥ አንዳለ ፤ እድሜው እያጠረ ፤ የቆመበት መሬት እየከዳው መሆኑን  እንገነዘባለን ፤ ለዚህም ሱዳን ሀገር የሚኖረውን ስደተኛ ፤ ከኤርትራ በኩል ከሚንቀሳቀሱትና ከሌሎች በነፍጥ ከሚታገሉት ጋር ግንኙነት አላቸው ብለው ስለሚየምኑና ፤  እንዲሁም ሰሞኑን በሱዳን አጎራባች አርማጭሆ አካባቢ በተፈጠረው ሁኔታ በመስጋት ፤ ካርቱም የሚኖረውን ስደተኛ ሕጋዊ የሰደተኛ መታወቂያ ፤ በየሶስት ወር የሱዳን መንግስት ሲያድስ የነበረውን፤ ኢትዮጽያዊ ስደተኛ የለም በማስባል ፤ መታወቂያችን ወያኔ ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል መታወቂያ እንዳይታደስ አስደርጎል ፤ ይህም ማለት ፤ የሚፈልጉትን ስደተኛ   በአፈሳ መልክ አፍነው እንዲወስዱ ያስችላቸዋል ፤ ባሳለፈነው ወር የወያኔ ምክር ቤት ያፀደቀወን  በአሸባሪና ወንጀለኛን ስም ስደተኛውን አሳልፍ በመስጠት የተደረገውን የትብብርን ውል ልብ ይሎል ፤ በተጨማሪ ጀዋዛት እየተባለ በሚገኘው እስር ቤት ውስጥ   የታጎሩትን የስደተኛ መታወቂያ የያዙትን እያሳነጠቁ ፤  ወያኔ ከሱዳን መንግስት ጋር በመመሳጠር ፤ አለማአቀፍ የስደተኞችን ህግ በመጣስ ፤ ስደተኛ መብትን በመንፈግ  ሕገ ወጥ በሆነ  አሰራር መታወቂያ አስር ቤት ውስጥ አስገድደው ፎቶ እያስነሱ ስደተኝነትን የማይገልፅ መታወቂያ በመሰጠት ላይ  መሆናቸውን አጥብቀን እንናስገነዝባለን ;;

ባሳለፍነው ወር የወያኔን መሰሪ ተንኮል ማጋለጣችን ይታወቃል ፤ ይኸውም ስደተኛውን ማህበረሰብ ቅጥ ባጣ አፈሳ በማስመረር በወያኔ ሰላዮች አማካኝነት የወያኔ ኢንባሲ ካርቱም ውስጥ በ28/11/2014 ሰላማዊ ሰልፍ አስደርገውል ፤ የሰልፉም አላማ   የኢሳትን ሚዲያ በመጠቀም ፤ ወደ ሀገራች አንግባ የሚለውን መልእክት ለማስተላለፍ የታቀደ ነበር ፤ እነዚህ ሰብአዊ ክብር ያልፈጠረባቸው ቅጥረኞች  በግፍአን እንባ አንዳላገጡ እንረዳል ፤ በተጨመማሪ እነዚህ በደል የበዛባቸው ወገኖቻችን ፤ለጥያቂቸው መልስ የሚያገኙ መስሎችው ተመልሰው ወያኔ ኢንባሲ በሳምንቱ ሔደው ማንም ሳያናግራቸው በመጡበት አኾሖን ተመልሰዋል;;

ውድ ወገኖቻችን ፤ ሱዳን ሀገር ውስጥ የሚደረሰውን በዝምታ የማይታለፍ በደል ከከፈ ደረጀ ከመድረሱ  በፊት ፤ በመላው ዓለም የምትገኙ ለሰብአዊ መብት መከበር የምትታገሉ   አለም አቀፍ ትብብር የፈጠራችሁ ወገኖች ሁሉ ፤ዛሬም ጨኻታችን ጣራ አልባ እንዳይሆን ፤ ለሱዳን መንግስትና ለዩ ኤን ኤች ስ አር በተቀነባበረ መልኩ ሰብአዊ መብታች ይከበር ዘንድ ፤  በሱዳን ሀገር የምንገኝ ኢትዮጽያዊያን ልሳን ትሆኑን ዘንድ  በአክብሮት እንማፀናለን ;;       ባሳለፍነው ወር 2000 ወገኖቻችን  የ ኤች አይቭ ና የሀቢታይትስ በሸተኞች ናቸው ተብለው ፤ ገንዘብ ንብረታቸውን ሳይውሰዱ ከሱዳን ሲባረሩ  አንድም ተቆርቆሪ ዜጋ የነዚህ ግፍአን     ልሳን ሳይሆን በመቅረቱ  ልብን ያደማል ፤   አሁንም ፤ አሁንም ፤ ይኽ የወያኔ ተንኮል በሰፊው ሳይደገም አፋጣኝ ወገናዊ ትብብራችሁን አንጠይቃለን;;

አጥናፉ መሸሻ

“አንዱ ቡድን ሌላዉን ጥሎ ለማለፍ የሚያደርገዉ ግብግብ ዉጤታማ ሊሆን አይችልም”ትንሳኤ ኢህአፓ

$
0
0

Tensaye
ድር ቢያብር አንበሳ ያስር!

እኛ የትንሳኤ ስብስብ በተለያዩ ጊዜያት በጽሁፍ፤ በሬዲዮ ብሎም በቴለቪዥን መስኮትያለንን አላማ ለኢህአፓ አባላቶችና በተለያዬ ምክንያት ከድርጅቱ ለወጡ እንዲሁም በድርጅቱ ዉስጥ ለመታገል ለሚፈልጉ ታጋይ ኢትዮጵያዉያን ሁሉ በተደጋጋሚ አሳዉቀናል፤ ዛሬም እንደገና ወደፊት ድርጅቱን ለማጠናከር ተገቢ ናቸዉ ብለን ለምንመኛቸዉና አጥብቀን ስለምንታገልለት ዴሞክራሲያዊ አካሄድ መተንተኑ ተገቢ ነዉ እንላለን፤፤

አሁንም ቢሆን የኢህአፓ ከሁለት መከፈል እጅጉን አሳዝኖናል፤ አበሳጭቶናልም፤ ይህነዉ የሚባል ወይም መሰረታዊ የሆነ የአላማ፤ የርእዩተ አለምና የራእይ ልዩነት ሳይኖር፤ ብዙ ጓዶች ዉድ ህይወታቸዉን የገበሩበት፤ የቆሰሉለትና የደሙለትን ድርጅት፤ ሃላፊነት በጎደለዉና ከምክንያት ይልቅ በስሜት ተገፋፍቶ፤ በግብር ይዉጣ መልክ ድርጅቱን መከፋፈልና ትግሉን አደጋ ላይ መጣሉ፤ በትንሳኤ ስር የተሰባሰብነዉን ጓዶች አንገብግቦናል አሳስቦናልም፤ ለዚህም ነዉ እራሳችንን አሰባስበንና አጠናክረን በዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነት የሚመራና፤ ከሁላም በላይ ለሰፊዉ ህዝብ የበላይነት የሚታገል የጋራ አአንድ ኢህአፓ ለማሰባሰብ ያለምነዉ፤፤
ትንሳኤ የኢህአፓ ልጆች ሲል ከሳሾቻችን እንደሚሉት ለወያኔ ያደረዉን፤ ወይንምየኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅም አሳልፎ የሰጠዉን፤ አሊያም መስዋትነት የተከፈለበትን የመብትጥያቄ የረገጠዉን ሳይሆን፤ የህዝብን ችግር የራሱ አድርጎ የተነሳዉን፤ በሃገር ፍቅር ስሜትየተቃጠለዉንና፤ የሰማእታትን የትግል አርማ ለመሸከም የሚፈልገዉን፤ አላማ ጽኑ ታጋይ ማለታችን ነዉ፥ ኢህአፓ ይጠናከር፤ ከዉስጥም ሆነ ከዉጭ ያሉትን እናሰባስብ ስንል፤ እነዚያን ለህይወታቸዉ ሳይሳሱ ከጠላት ጋር በመተናነቅ አኩሪ ታሪክ ያስመዘገቡትን፤ በደማቸዉ ታሪክ የጻፉትን፤ በአጥንታቸዉ የኢህአፓን ሰንደቅ ከፍ አድርጎ ለመስቀል ሲሉእንደወጡ የቀሩትን፤ እሬሳቸዉ በየመንገዱ የተጣለዉን፤ በጅምላ በአንድ ጉድጓድ የተቀበሩትንና ፤የአዉሬ እራት የሆኑትን ጓዶች በማሰብ ነዉ፤፤
ኢህአፓ ተጠናክሮአል፤ አባላቶችም እየበዙ ነዉ፤ በህዝብ ዘንድም ሰርጾ እየገባ ነዉ፤ለምትሉን መልሳችን፤ ቤታችን ኢህአፓ ሲሞቅና፤ ሲቀዘቅዝ የትግል እሳቱም ሲጋይና፤ ሲዳፈን ነበርንበትና፤ በደንብ እናዉቀዋለን፤ በአሁኑ ሰአት ኢህአፓ መከፋፈልና መዳከም ብቻ ሳይሆን፤ በህዝባዊ ትግሉ ይህ ነዉ ሊባል የሚችል አወንታዊ ዉጤት ባለማሳየቱ፤ እታገልለታለሁ ከሚለዉ ህዝብ ጋር መራራቅ ብቻ ሳይሆን፤ ህዝቡም የኢህአፓን እንደ ድርጅት መኖርና መንቀሳቀሱን በመርሳት፤ ኢህአፓ በተባለ ቁጥር ኢህአፓ ደግሞ አለ ብለዉ የሚጠይቁ ብዙዎች ናቸዉ፤ ስለዚህ ያልተደረገዉን እንደተደረገ በማስመሰል፤ የህልም ዳቦ መግመጡን ትተን፤ ድርጅቱን እናጠናክረዉ እናጎልበተዉ ነዉ የኛ ምክር አላማም፤፤
እንዲያዉም እራሱን ኢህአፓ ነን በሚለዉ ቡድንና፤ ተገንጥሎ ወጥቶ እራሱን ኢህአፓ-ዴ ብሎ በሰየመዉ ቡድን፤ እርቅ ሰላም ለማዉረድ በቅርቡ የተሞከረዉ ጥረት ፍሬ ሳያሳይ በመቅረቱ፤ በጉጉት የጠበቅነዉም የአንድነት ትግል መጀመር በመጨናገፉ ቁጭታችን ከፍ ያለ ነዉ፤ ይህ ሙከራ ግዜ የፈጀ ዉጣ ዉረድ የነበረበት ስለነበረ፤ ዉድ ጊዜያቸዉን አጥፍተዉ ድርጅቱን ለማዳን የደከሙትን፤ ከወዲሁ እያመሰገን ይህን ቀና ሃሳብ የደገፉትን አበጃችሁ ስንል፤ ጀርባቸዉን የሰጡትን ግለኞች ደግሞ ሌላ ምንም ማለት አንችልም፤ የሰማእታት አጽም ይፋረዳችሁ ከማለት በስተቀር፤ ይህ እርቀ ሰላም ቢሳካ ኖሮ ኢህአፓን እንደ ድርጅት ከማጠናከሩም በላይ፤ በአሁኑ ሰአት የኢትዮጵያ ህዝብለሚያደርገዉ ጸረ ወያኔ ትግል፤ አጋዥም አበረታችም ይሆን ነበር፤ አለመታደል ነዉ እንዲሉ፤ በአመራር ቦታ ያሉትና፤ እርቅ ሰላሙን የተሳተፉት ጓዶች ቅራኔን ከማርገብ ይልቅ ማፋፋምን፤ ልዩነትን አጥብቦ በጋራ ከመቆም ይልቅ ቃላትን በመሰነጣጠቅ ልዩነትንአስፍቶ በተናጠል መቆማና፤ እንደጠላት መተያየትን መርጠዋል፤ ይህ ከድርጅትና ከጋራ ጥቅም ይልቅ ተክለ ሰዉነትን መገንባት የተጠናወተዉ በሽታ፤ ለድርጅቱ ዉድቀት ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ህዝባዊ ትግል ላይም የማይሽር ጠባሳ እንደሚያሳርፍም ጥርጥር የለነም፤፤

የዛሬን አያድርገዉና፤ ትናንትና በኢድሕቅ የትግል ሂደት ዉስጥ መኢሶን ጎን የተሰለፈዉ ኢህአፓ ዘንድሮ በዉስጡ የተፈጠሩ ችግሮችን በዲሞክራሲያዉ ሁኔታ መፍታት፤ ለኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ሲባልም ይቅር ተባብሎና፤ ተቻችሎ ትግሉን መቀጠል አለምቻሉ ሁላችንም ያስገረመ ሚስጥር ብቻ ሳይሆን፤ ድርጅቱ ምን ያህል ከዲሞክራሲያዊ አሰራርና ከምንክንያት ጋር እንደተጣላም ያመላክታል፤ ድርጅቱ የራስ ንብረት ይመስል፤ ሌሎችን ድንጋይ ተሸክመዉ ይቅርታ ካላሉ፤ አይናች ሁን ላፈር ማለት፤ አዋቂነትን ሳይሆን አምባገነናዊ ባህሪን የሚያሳይ ነዉ፤ ስለዚህ ኢህአፓ አብቦና አፍርቶ ለማየት የምንፈልግ ሁሉ ነገሩን በአንክሮ ተመልክተን መወያየትና ለችግሮችም መልስ መሻት ተገቢ ነዉ እንላለን፤፤
ለነገሩማ በአመራር ቦታ ብዙ ጊዜ መቆየት ድርጅትን የግል ንብረት አድሮጎ የማየትንአባዜ ያስከትላል፤ ተመክሮአችን ሁሉ የሶሻሊስት ፍልስፍና ሆነና፤ ሁላችንም ከድርጅት የስልጣን ኮረቻ መዉረድን ወይም ለሚገባዉ ሰዉ ስልጣን መልቀቅ ተገቢ ስርአት አድሮጎ መቀበል ተስኖን፤ እንደወያኔዉ አምባገነን መሪ ሞት ካልወሰድን በስተቀር የሙጥኝ ማለቱን ተያይዘነዋል፥ ድርጅቱን የግል ንብረት አድርጎ መቁጠር ብቻ ሳይሆን አንዳንዶቻችን የድርጅት አባላትም ጭምር የመለኮትን ያህል እንዲያመልኩን እንሻለን፤ በቅርቡ ከወያኔ አገዛዝ በራሱ ፈቃድ ጥሎ የወጣዉ አቶ ኤርሚያስ ለገሰ፤ የመለሰ ቱርፋቶች በሚለዉ መጣጥፉ፤ ምን ያህል የወያኔዉ ድርጅት የአቶ መለሰ ዜናዊ የግል ንበረት እንደሆነና፤ አቶ መለሰም በድርጅቱ ላይ የነበራቸዉን ያልተገደበ ፍጹማዊ ስልጣን አመላክቷል፤ ስለዚህ እንደዚህ አይነት በድርጅት ዉስጥ የሚፈጠሩ ግለሰብ አምላኪነትና ያልተገደበ ስልጣን መኖርን፤ ሁላችንም ለዲሞክርሲ፤ ለፍትሕና ለእኩልነት የምንታገል ሁሉ ልናወግዘዉ ይገባል፥ በአመራር ቦታ የሚቀመጡ መሪዎች የስልጣን ጊዜያትና ገደብም እንዲኖራቸዉ የግድ ይላል፤ ድርጅቶችም ይህን በተመለከት ህግ ማዉጣት ብቻ ሳይሆን ለተግባራዊነት መታገል አለባቸዉ፤በድርጅት ዉስጥ የታቀፉ አባላትም፤ ከግለሰብ አምላኪነትና ከቡድንነኝት ነጻ በሆነ መንፈስ ሃላፊነታቸዉን መወጣት ይኖርባቸዋል፤ ማንኛዉን አይነት አምባገነናዊ ባህል ማስወገድና በምትኩ የተለያዩ ሀሳቦች ሊሸራሸሩበትና አባላት ያለምን ስጋት ያላቸዉን ልዩነት ሊያሰሙበት የሚችል መድረክ መፍጠር ተገቢ ነዉ፤፤

የአምባገነን ባህል አሜን ብሎ የተቀበለ፤ ስልጣንን ከሃላፊነትና ከተጠያቂነት ማጣመርየተሳነዉና፤ መመረጥንም ሆነ ስልጣን መልቀቅን ማቀናጀት የማይችል ድርጅት እንኳን ህዝብንና አገርን ነጻ ሊያወጣ ይቅርና እራሱንም ነጻ ማዉጣት አይችልም፤ አጋጣሚ ሰጥቶትም ስልጣን ላይ ቢቆናጠጥ ለህዝብ ነቀርሳ እንጅ መፍትሔ እንደማይሆን ወያኔ በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ህዝብ የሚያደርሰዉ ግፍ በቂ ምስክር ሊሆነን ይገባል፤ ስለዚህ የአባላቶች ንቁ ተሳትፎ፤ አዙሮ መመልከትን ብሎም ተላምጦ የተሰጠን ብቻ ከመዋጥ ይልቅ እራስም ማኘክን መልመድ፤ ድርጅትንም ሆነ አገርን ከጥፋት ያድናል፤ አለበለዚያ ግን እነዚያ እንደመልኮት ሲታዩ የነበሩ አመራሮች መምራት ሲያቅታቸዉ ወይም በሞት ሲለዩ ድርጅቱ ሞተሩ እንደተበላሸ ተሽከርካሪ መቆሙ የማይቀር ይሆናል፤፤

ከዚህ ባሻገር በቅርቡ ስለወጣዉ የኢህአፓ-ዴ እና እርማት እንቅስቃሴ ስለ ተባለዉ ቡድን የጋራ መግለጫ በኢንተርኔት ድረገጽ ተመልክተናል፤ በጥቅሉ ጅማሬዉንና፤ ጽንሰ ሃሳቡን የምንደግፈዉ ቢሆንም በ አሰራሩ ላይ ግን ልዩነት አለን፤ በቅድሚያ በጥሪዉ ሆነ በመሰናዶዉ የኢህአፓ ጉዳይ ይመለከታቸዋል የተባሉትን ሁሉ ማሳተፍ ተገቢ ነዉ፤ በተለይም በአሁኑ ሰአት የተለያዩ ቡድኖችም ሆነ ግለሰቦች ኢህአፓን አንድ ለማድረግ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ከወዲሁ እነሱን ማማከርና በሂደቱ እንዲሳተፉ መጋበዙ ተገቢ ሆኖ እያለ፤ አንዱ ቡድን ሌላዉን ጥሎ ለማለፍ የሚያደርገዉ ግብግብ ዉጤታማ ሊሆን አይችልም፤ ትንሳኤም የተነሳለት አላማ ግብግቡ ቀርቶ ሁሉም ጓዶች በሰከነና አስተዋይነትበተሞላበት ሁኔታ ችግሩን በአንክሮ ተመልክተዉ መፍትሔ ላይ እንዲደርሱና አንድ ኢህአፓን ይዘዉ እንዲወጡ ስለሆነ አላማችን፤ ከወዲሁ አሰራሩ ሁሉንም እንዲያቅፍ እናሳስባለን፤፤
ኢህአፓ በተባበረ ክንዳችን ይጠናከራል፦
የኢትዮጵያ ህዝብ ያቸንፈል፦

ሳዲቅ አህመድ ለዛ ባለው አነጋገሩ ያላደረግናቸዉ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን ይጠቁመናል

$
0
0

ዳላስ ላይ በተደረገ የኢሳት ገቢማሰባሰብ ዝግጅት ላይ ጋዜጠኛና አክቲቭስት ሳዲቅ አህመድ ለዛ ባለው አነጋገሩ በትግሉ ያላደረግናቸዉ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን ይጠቁመናል:: ያድምጡት – ያተርፉበታል::

ሳዲቅ አህመድ ለዛ ባለው ንግግሩ ያላደረግናቸዉ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን ይጠቁመናል

Viewing all 2784 articles
Browse latest View live