Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2784

አቶ ብርሃኑ አዴሎ ከሥልጣናቸው ተነሱ

$
0
0

Berehanu Adelo

(ዘ-ሐበሻ) ከጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በአንድ ላይ የደህዴን ፖሊት ቢሮ አባል የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክኒያት ድንገት ከስልጣናቸው መነሳታቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገለጹ::

የኢትዮጵያ አዕምሮአዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ ሆነው ይሰሩ የነበረ ሲሆን ከዚያም ቀደም ብሎ የደቡብ ክልል ምክትል የፍትህ ቢሮ ሃላፊ ሆነው ሰርተዋል:: በሌላም በኩል በርከት ያሉ የስርዓቱ ተላላኪዎች ሃገርን በመልካም ሁኔታ የሚመራ ትምህርት ሳይሆን ተንኮል ይማሩበታል በሚባልበት የሲቭል ሰርቭስ ኮሌጅ አስተማሪ ሆነው ያገለግሉ ነበር::

የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት ብርሃኑ አዴሎ በሃይለማርያም ደሳለኝ የተፈረመ ደብዳቤ በደረሳቸውና ከስልጣናቸው በተነሱበት ዕለት በርሳቸው ምትክ አቶ ግርማ በጅጋ ተሹመዋል::


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2784

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>