Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2784

የሕወሓት አስተዳደር በአዲስ አበባ ዙሪያ በአዳማ እና ደብረዘይት ማስተር ፕላኑን በሚቃወም ቅስቀሳ ተረብሿል

$
0
0

መላው ኢትዮጵያውያን ለሚደረገው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ከጎናችን እንዲቆሙ ሲሉ አስተባባሪዎች ጠይቀዋል::

(ምንሊክ ሳልሳዊ) ከመሃል ሃገር ከሚገኙ የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎች የደረሱን መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በወጣቶች ማህበር አስተባባሪነት በአዲስ አበባ ዙሪያ በናዝሬት/አዳማ እና ደብረዘይት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም እንዲሁም የወያኔው ጀሌ አባይ ጸሃዬ የሚባለው የተናገረውን ጸረ ሕዝብ አፍራሽ አነጋገር በመቃወም ከፍተኛ የሆነ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ለማድረግ ቅስቀሳ እየተካሄደ መሆኑ ተጠቁሟል::ይህ ቅስቀሳ ወያኔን አስጨንቆ የያዘው ሲሆን ሊያስቆመው የማይችል ከፍተኛ የሆነ ህዝባዊ አመጽ ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት አስከትሏል::
oromia land grap
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ክልሎች ላይ በተደረገ ተቃውሞ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን የተቹ የተቃወሙ እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ስለገበሬዎች መብት አቤት ያሉ ወጣቶች ተገለዋል ታስረዋል ተደብድበዋል በአፋኝ ሃይሎች ተሰውረዋል::ይህ ቁስል ሳይጠገን የሕወሓት ጀሌዎች በሃዋሳ በተደረገ ስብሰባ ላይ ባደረጉት እብሪት የተሞላ ንግግር ልክ እናስገባለን ብለው መዛታቸው በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል::ይህንን ቁጣ ተከትሎ በአዲስ አበባ ዙሪያ ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለማድረግ ህዝብን የማስተባበር ስራ እና የቅስቀሳ ስራ እየተሰራ በመሆኑ መላው ኢትዮጵያውያን ከአስተባባሪዎች ጎን እንዲቆም ጥሪዎች አስተባባሪዎቹ ጠይቀዋል::

The post የሕወሓት አስተዳደር በአዲስ አበባ ዙሪያ በአዳማ እና ደብረዘይት ማስተር ፕላኑን በሚቃወም ቅስቀሳ ተረብሿል appeared first on Zehabesha Amharic.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2784

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>