(ዘ-ሐበሻ) የፌደራሉ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ ሰበር ውሳኔ ለማስተላለፍ ለዛሬ ሐምሌ 29, 200 ዓ.ም ቀጠሮ ይዞ የነበረ ሲሆን አሁንም በተልካሻ ምክንያት ለ3ኛ ጊዜ ቀጠሮው ተላልፎ ለነሐሴ 12 ተቀጥሯል::
የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ሰበር አቤቱታ የሰማው ችሎቱ ውሳኔ ለመስጠት ከዚህ በፊት ሁለት ቀጠሮዎችን ሰጥቶ በተልካሻ ምክንያት ጋዜጠኛውን በማጉላላት የሚገኘው ሰበር ሰሚ ችሎቱ ለ3ኛ ጊዜ ተመሳሳይ የቀጠሮ ማራዘም ተግባሩን ቀጥሎበታል::
እንዲህ ያለው በተልካሻ ምክኒያት ፍርድን የማጓተት ተግባር የጋዜጠኛውን ስነልቡና ሆን ተብሎ በሕወሓት መንግስት የሚደረግ መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች ያምናሉ::