Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » News
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2784

ፍቃዱ በቀለ ዛሬ ከእስር ተፈታ * አበበ ቁምላቸውም በዋስ እንዲወጣ ታዟል

$
0
0

elias 1

elias

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እንደዘገበው:- የቀድሞ አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ፣ የአዲስ አበባ ወጣቶች ም/ሰብሳቢ የነበረው እና የዛሬ 20 ቀን በሽብር ወንጀል ተርጥሮ፣ ‹‹ሰዎችን ለግንቦት ሰባት በመመልመል ወደኤርትራ ትልክ ነበር›› የተባለው ፍቃዱ በቀለ ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ገደማ በዋስ ከታሰረበት ካሳንችስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ተፈታ፡፡ በተጨማሪም በተመሳሳይ ክስ ተጠርጥሮ ከ25 ቀናት በላይ በዚሁ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ የነበረው የቀድሞ አንድነት እና በአሁን ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አበበ ቁምልቸውም በዋስ እንዲወጣ መታዘዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ዜናም፣ ‹‹የአልሸባብ ህዋስ ነህ፤ ባራክ ኦማባ በሚገኙበት ስብሰባ ወቅት የሽብር ወንጀል ልትፈጽም አሲረሃል›› ተብሎ ለ28 ቀናት፣ መገናኛ አሚቼ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ የነበረው የ‹‹ቀዳሚ ገጽ›› ጋዜጣ ሥራ አስኪያጅና የቀድሞ የ‹‹ሚሊየኖች ድምጽ›› ጋዜጣ ሪፖርተር ሀብታሙ ምናለ ከትናንት በስትያ ምሽት 2፡30 ገደማ ከእስር መውጣቱ ይታወሳል፡፡


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2784

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>